"ምፃጉ ነፍሴ....."ውሸት" አልጋህን ተሽክመህ ሂድ" ኤልያስ ሽታኹን (የልደት ዳር ጨዋታ) ~ ~ ~ ~ ~ ጭብጨባው ነው ጠላቴ ድምፄን ያስመለከኝ ፅሁፌን መስመር የመረጠልኝ በጎደለ ሞላ ተጫወትኩ:: ሴቶች ተባብረው የወደዱትን ህዝቡ የተቀበለውን "ኤልያስ አደባባይ" በምኔ ልጠረው:: በቆርቆሮ በግምብ ብሸምበቆ:: ያሬድ ደደብ ካለው መመህሩ ይልቅ ከትል መማሩ ምንይሉታል? ከራሴ ሸሽቼ ትል ከሆነ ወሸቴ ምን ጠብቄ ነው የማንጋጠው? ሁሉም ጏደኞቼ ስልክ ይዘው እኔ ቀረሁ:: ነገርኩት:: አንድ ጏደኛዬን "ቤት አይገዙልኝ የላቸውም" አልኩት:: ገዛልኝ Techno :: እቤት ስሮጥ ደረስኩ:: "በትወና ትምህርትቤት ተሸለምኩ" ሳውጠነጥናት የነበርች ውሸት ጥያቄ አመጣች:: "ምስክር ወረቀት የለውም ስንተኛ ወጥተህ ነው?" "ትቼው መጥቼ ነው" ቢሮ "በል እሺ" እቤት እሱን ለማረሳሳት ብዙ ውሸት ተሰራ:: አርብ ለት ስሰግድ ሴት ካየሁ ላብ እስኪፈልቀኝ እሰግዳለሁ:: ሰንበት ትምህርትቤት ድምፁ የሚያምር ልጅ ሲዘምር በጉራ መልክ አጨበጭባለሁ:: አንድ ቦታ የሚያውቀኝ ሰው እንዳለ ካወቅኩ ውስጤ ይርመጠመጣል:: የሰውነቴ መደንዘዝ የተረጋጋ ሰው ያስመስልኛል:: ውሸታም ነኝ:: እግኝበት ክብር ካለ ከመዋሸት የሚያግደኝ ነገር አለበረም:: እንደቀልድ "እወድሻለሁ" ብዬ የሰው ተስፋ እሆናለሁ:: "እንደወዶቹ አይደለህም" ለመባል ያለፈጠርኩት የለም:: Room ውስጥ ፀጥ ብሎ እስከመትኛት:: (ዋጥ አርጌ አምሮቴን) "እደወላለሁ" ከዛ እንደምጠበቅ እያወቅኩ መተው:: "እመጣለሁ" ብዬ መቅረት:: ከዛ በሷ ኩርፊያ ውስጥ "ምን ያህል እንደምፈለግ ማረጋገጥ":: ስንቱን ተስፋ ያስቆርጥኩ ስንቱን የዋሸሁ ሀኪም ቤት ያስገባሁ እኔ በካድኩት ወንድ በቃኝ ያስባልኩ ዋሾ መልኬን አሳምሬ የምኖር የገዛ እባቤ የነደፈኝ ነኝ:: በሰዎች መሐል የተረሳሁ ከመሰለኝ ሽንቴ ሳይመጣ እንሳለሁ:: አልጋህን ይዘህ ሂድ እንደተባለ ምፃግዑ ውሽቴን የት ይዤ ልሂድ ተሸክሜ:: ረጅም ዘመን ያኖረኝን ወሸቴን:: 960 views20:07