"Purpose on mistake" ኤልያስ ሽታኹን (የመጨረሻው መንደርደሪያ) ~ ~ ~ ~ ~ ከኔ ይልቅ የሄድኩት መንገድ ዋጋው ከበረ? የረገጠኩትን "እናውቃለን" ባዩች ሚዛን ይዘው አሰቃዩኝ:: በሰው ለመወደድ የምንደክመው ሁሉ ፍሬው ከድካሙ ያንሳል:: ስንት አዋጣለሁ? ገመናዬን ተርኬ ክብር ፈልጌ ይሆን? በሚስጥሬ ሀዘን ሰብስቤ እግዜርን ልገጥመው ይሆን? መንገዴ መንገድ እንዳልነበረ ይታወቅልኝ ዘንድ ወሰንኩ:: ስዋሸው እያወቀ ዝም ያለኝ ጏደኛዬ ላድነቀው ልርገመው? ለምን ውሽታም አላለኝም? ለምን? ፈርቶኝ አይደል ወይስ ሳስቶልኝ? የዋሸዋቸው ለምን ተዋሹሉኝ:: "ለመኖር ምን ያስፈልጋል?" "በሰዎች መወደድ" ነው መልሴ:: "ባትወደድስ?" "እዋሻለሁ" "ለመወደድ ውሽት?" "እውነት ሆኜ ትወድኛለህ?" "አዎ" "ውሸታም:: ይሄም እኔ እንደወድህ ውሸት ነው" እነዚህ ሁሉ ለምን? እንጃ? ለምን ዋሸሁ? ምን ለማግኘት? ምን ላለማጣት? ለምን ለመዋሸት ሰዎች ተደላደሉልኝ:: አንቺ ግን ከውደድሽኝ መርቂኝ "ያየህ ይርገምህ" በይኝ መርቂኝ "ውሸትህን ትደበቅበት ቀዳዳ ባጣህ" ብለሽ:: ያኔ እምሆነው ሳጣ ምን እንደምሆን ይገባኝ ይሆን? ዋጋ ፍለጋ የተሰደድኩብት በርሀ ውጦ አስቀረኝ:: "ስንት አወጣለሁ?" ክርክሬ ላይ ችሎት ቆምኩ:: ተሸነፍኩ:: ያውም በዝረራ:: 356 views18:58