Get Mystery Box with random crypto!

የኤልያስ ሽታሁን ግጥሞች እና እይታዎች 💚💛❤

የቴሌግራም ቻናል አርማ eliasshitahun — የኤልያስ ሽታሁን ግጥሞች እና እይታዎች 💚💛❤
የቴሌግራም ቻናል አርማ eliasshitahun — የኤልያስ ሽታሁን ግጥሞች እና እይታዎች 💚💛❤
የሰርጥ አድራሻ: @eliasshitahun
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.54K
የሰርጥ መግለጫ

ግጥም በድምጽ በጽሑፍ
ምርጥ አንድ ገፅ
በሰው የተነበቡ ግጥሞች
የአሪፍ መጽሐፍ ጥቁምታ
አጫጭር ታሪኮች
የሀሳብ ንሸጣዎችን ከሁሉም እንቃርማለን፡፡ፈጠራዎችን እንደመምባቸዋለን፡፡የኤልያስንም የሌሎችንም ከያነያንን ስራ እንታደማለን፡፡ ስለሀሳብ እንሰማለን፡፡ እናሰላስላለን፡፡ ሰክረን ሳይሆን ሰክነን፡፡ሀሳብን እናስበዋለን፡፡
ዘላለም የሚቆየው ሀሳብ ነው፡፡
ለማንኛውም አስተያየት 👉 @Elias2127

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-27 15:24:09 "የማርያም ማጀት"
ኤልያስ ሽታኹን
~ ~ ~ ~ ~
እንዴት አባበልች መለኮትን አቅፋው?
ይነግራት ነበረ እግዜርም ሲከፋው?
ማርያም
ቅሩብ ለትሁታን
ማርያም
ተስፋቸው ለሙታን

ልጅ ሰጪ ለመሃን
ማርያም እመብርሃን::

መጽሐፉማ ይላል
"እንቅልፍ የለው ከቶ"
እግዜር ግን ተገኘ ድንግል ስር ተኝቶ::
እንቅልፉን ወሰደው መለኮት በስጋ
ያርፍባት የለም ወይ እጇን የተጠጋ::

ማነው የጎበኘው የማርያምን ማጀት?
ለራበው ታዝናለች እንደልጇ ካንጀት::
በምን አቦካችው የለት ዱቄት መና
ውኃ ቀድታ ነበር? ወይ ወርዶ ደመና?

አይባልም ለርሷ
እንጀራና ዳቦ እንዴት ጋገረችው
እሳት አይደለም ወይ የተሸከመችው?
1.1K views12:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 01:03:54 " Filter ያልነካቸው "
ኤልያስ ሽታኹን
(የልደት ዳር ጨዋታ)
~ ~ ~ ~ ~
እንደክርቶስ ሐሙሴ ይመጣል::
"ይቺ ነገር ትለፈኝ "የምልበት ::
ደመም ላብም ብቻዬን የማፈስበት::
የአትክልት ስፍራው ከኤርታሌ ብሶ የሚያቃጥለኝ ቀን አለኝ::

እስከዛው ትርካ ....

አምዳምነቴ ልክ አልነበረውም::

እንዚህ ቀናቶች ለሰው የገረጡ ለኔ ግን ያጌጡ ናቸው::
አራት ኪሎ
- የሰካራም ልጅ የተባልኩበት
- የድሀ ልጅነቴ ስታይ የማስታውቅ እኔ
- ጉልበተኛ ሀብታም ጎረቤት
- ዉኃ የሚነጠባጠበት ቤት
- የልጅነት ፀብ (አንዳንዶች አርጀተውም እኔን ለማሳፈር ይመዙልኛል)"እንዲህ ብለህ ነበር"ይላሉ
- ፅዋ ማህበር (አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ)
- ውድድር
- ትልቅ ህልም ትንሽ አቅም
- መጨረሻቸው ለሊት የሆኑ ወኮች
- የክበብ ሽኩቻዎች
- ጅንጅና ስልት ንድፎች
- ያወቁትን ቤት መጥቶ ማውራት (ጥሩ ቦታ ነው የሚውለው እንዲባል)
- ከእኩዮች ጋር አንድ አይነት ፋሽን መስራት....

ይሄ ሁሉ በህሊናና በልብ የቀሩ ማስታወሻዎች ናቸው::
ዛሬ ደሞ ለሰው ውብ ለራስ ግን ኮሽኳሻ ናቸው::

- ገላዬ ቆሽሾ በድንጋይ እህቴ ታላቅ እህቴ (ደርግ በሏት) ብረት ምጣድ ላይ እያጋጨች ፈተገችኝ::

"ማንን ለማሰድብ ነው" እያለች::
ጎረቤት አይሰማት ሰደበችኝ::
"ሰፈሩ እንደሆነ ቡዳ ነው"
"እኔ እኮ..."ላስረዳ ስሞክር ወኃውን ሳየው ጠቁሯል:: እድፌ ጭቃ ያህል ወፍራም:: ዝም ::

“ደሞ ባንተ እንሰድብ ወይ”
(“ድው” ከብረት ምጣድ ጋር ታላትመኛለች)
እልህ ዕንባ ነበራት:: አሁን ሳስባት ታሳዝነኛለች::

ምንበላው አልነበረንም ግን ስማችን አሳሰባት እና ጉልበቴ እስኪላጥ አሸችኝ::

ልክ እንደነዚህ ወዝም ደርዝም የሌለው የሚመስል እልፍ ቀን አለኝ
1.1K views22:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 18:03:40 እኛ ቀጋ
ኤልያስ ሽታኹን
~ ~ ~ ~ ~
ቀጋ ጊዜን ተደግፌ
እሾህ ዘመን ተቃቅፌ
ሳቅ መፈለግ " አይ ወፈፌ::"

አልዋጥ እያለ የላመ የጣመ
ምቹ መንገድ የለም እግር ከጠመመ
ስርዝ ማገር
ድልዝ ሀገር

ባቢሎን
ደልድሎን
እስከሰማይ ደርሶ
ይፈርሳል መልሶ::
ግንባችን
ይደረምሰናል ውል አልባው ግባችን::

እኛ ቀጋ
አንመችም ለተጠጋ::
(ብቻ እንዋጋ)

ኑ ርግብ እናርግፍ
ኑ እምቡጥ እንቅጠፍ
ኑ ላንተልቅ እንግዘፍ
ኑ ላንሄድ እንለፍ
ኑ ላንወድ እንቀፍ


እኛ ቀጋ
አንመችም ለተጠጋ::
(ብቻ እንዋጋ)

ስርዝ ነፍስ
ድልዝ መንፈስ
ዓይን ያጡ ህፃናት
ደረት የማያጡ ቃላህ ቃላት
አሉን በየሰርጡ
"ለኢየሱስ" ህፃን ባሩድ የሚያጠጡ::

ውሸት ድርሳን
እጅ ነሳን
ዜጋ ሆንን ሀሜት ሀገር
ቤት ብለን ጠራነው ፍርስርሱን ማገር::

እኛ ቀጋ
1.2K views15:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 22:52:16 በቂ ልምድ አለኝ
ኤልያስ ሽታኹን
~ ~ ~ ~ ~
የተረፈኝ ቢኖር
ካንቺ ጋ በመኖር
በጥንዶች መሳቅ ነው ጥርሴን አሳምሬ
ሞኞች ናቸው ብዬ
ጅሎች ናቸው ብዬ
ልጆች ናቸው ብዬ፡፡

ካንቺ ጋ ከርሜ
ካንቺ ጋ ታምሜ
ካንቺ ጋ አድሜ
ካንቺ ጋ ወጥቼ
ካንቺ ጋ ገብቼ
የተረፈኝ ነገር
"የሚፀና የለም ካለመፅናት በቀር፡፡"
(የሚል ጥቅስ ነበር)

የተቃቃፈ ክንድ
አንድ ቀን
ፍቅርን እንደሚንድ
(አላውቅም ነበረ)
የተሳሳሙት ሰው
አንድ ቀን
ስሜት እንደሚያንሰው
(አላውቅም ነበረ)

አወቅኹኝ መለየት
አየኹኝ መስታየት
ዳሰስኹኝ መሞኘት
ሸተትኝ መሸኘት
ቀመስኹኝ እንባዬን
መረረኝ ተራዬን፡፡

ደክሞ እስከሚላላ ወገባችን ስሩ
ተራራ ነው ያልነው ፍቅራችን ጠጠሩ
ቃልኪዳን ነው ያልነው
ሲያልበን የማልነው
መዛበቻ ሆነ ለሰውና ሰይጣን
እግዜር ሲፈልገን ከቤታችን አጣን፡፡

ፍቅርም
አሽሙርም
አንድ ናቸው አይደል ችለው ካራቀቁት
ለተባለለት ነው በውል የሚዘልቁት፡፡

ካንቺ የከረምኩት በሰው ያስቀኛል
"አይዘልቁም አይቆዩም ጅሎች" ያሰኘኛል፡፡
1.3K views19:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 10:15:15 "ሶምሶማ ጦርነት"
ኤልያስ ሽታኹን
~ ~ ~ ~ ~

ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ከነጮች ጋር እየተማረ ቁጭ ብለው እየተጨዋወቱ ሳለ "በልጅነቴ ጫማ አላውቅም ነበር" ሲላቸው ነጮቹ ደነገጡ::

"ረጅሙን የትምህርት ዘመኔን በባዶ እግር ነው ያሳለፍኩት" አለ ::
ምን ቢሉት ጥሩ ነው "ለምን አትፅፈውም? ይሄ እኮ የሚደንቅ ነው ለብዙ ሰው::"
ለነርሱ የደነቃቸው ክስተት ለጌታቸው ኃይሌ ሀገር ግን የተለመደ ህይወት ነበር::

ለብዙ የሚደንቀው ነገር ለኛ ኑሮ መሆኑ ስላቅ ነው:: በዓመት ሦስቴ የምናከብረው ብቸኛ ብዓል ነው ውጊያ::

ለምንሰማው ከደከመን እዳው ላይ ላሉት ዳፋው ዳይ ለወደቁት ምንኛ ስቃይ ይሆን?

ዛሬም ተስፋ አለን እንባባል ይሆናል:: ግን ዋሾ ነን:: እንደሀገር ሁለት ስሜት አለቀቀንም
ያልወጣልን ብሶት እና
የማንወጣው እልህ::

እንደህዝብ ቁጡ እና ሆደ ባሻ ሆነናል::
ታክሲ ውስጥ ብሶት
ኪዎስክ ውስጥ ጠርሙስ መስበር ቱግ ባይ::
ሳንነካ ሁሉም የሚያጠቃን የሚመስለን
ሁሉም የሚንቀን የሚመስለን
ሳንጠየቅ ገና የይሆናል መልስ የምናዘጋጅ ደንባሮች ሆነናል::

እንደህዝብ ተቀያይመናል::
እንደግለሰብ ተጠላልተናል::

በየሶሻል ሚዲያው ላይ ያሉት ነገሮች ድምፃቸው ቤተስኪያን ደጅ ከሚጮህ የመዝሙር ሞንታርቦ በላይ ይሰማል:: (ለሁለት ደቂቃ Tiktokህን ስክሮል አርገህ ሞክረው::) ሁሉም እየጮኸ ነው::
-ዳንሱ በጩኸት
-ስብከቱ በጩኸት
-ሞቲቬሽኑ በጩኸት
-ምክሩ በጩኸት

እልህ+ብሶት = ( )

እንደሀገር ልጅነቴ በሀገሬ ቅያሜ ካለኝ ቆየሁ:: ተኳርፍናል::

በየቦታው ሄጄ ያየሁት ህዝብ የራሱ ብሶት የራሱን እልህ ሳይ ያስፈራል እላለሁ::

"....አስርጪብኝ የምነት ቀንጃ
ለስጋቴ አጣማጅ አቻ
ለጭንቀቴ መቀንቻ ....."
እንዳለ ጸጋዬ

እኛስ
አይደክምም ወይ እያስታመሙ መግደል?
አይደክምም ወይ እየገረፉ ማባበል?
አይደክምም ወይ እየሳቁ ምስጋት?
አይደክምም ወይ እያረፉ መዋጋት?
አይደክምም ወይ?
አይደክምም?
አይደክምም?
1.4K views07:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 22:35:46 ኑዛዜ አዘል ነዛዜ.....
(የሚነበብ ብቻ)

ምን አልባት የመጨረሻው መጨርሻ ቢሆንስ?

አውቃለሁ "አለቀ"ን አንወድም::
ግን ማለቂያው ላይ ብንሆንስ?
ይሄ የመጨረሻው ቃል ሊሆን ይችላል:::

ምን አልባት ጉሮሮ ከመናገር ቢከለከል
እጅም ከመፃፍ?
ምን አልባት ለመፍራትም ለመድፈርም እስትንፋስ ካጣን....
ምን አልባት የምንወዳቸውን ለማቀፍ ....
የምንጠላቸውንም ለመንቀፍ
ይሄ ቅጽበት የመጨረሻው ቢሆንስ?

የሚውዱን ሳይነግሩን የሚነቅፉን ሀቃቸውን ሳንስማላቸው ልናመልጣቸው ቢሆንስ?

ምን አልባት

- የተስፋዬ ገሠሠን "ዑመርኻያም" ገፅ 167 ላይ እንዳጠፍኩት
- ያቺን የመሰለች ልጅ እንዳልኩ
- ለራሴ ኪሴ 10ብር ሳይኖረኝ ተማርሬ ሳለ "ናፈቅኽኛል" ስትለኝ"ከዚህ ቡኃላ እንዳትድወይልኝ" እንዳልኳት
- አመታት የራቅኩትን ኪዳን ሰዓታት ነገ እሄዳለሁ እንዳልኩ
- ድሮ ክበብ የተጣላዋቸውን መች አጊንቻቸው እንዳልኩ

- እማዬን ግሸን አቁርቤያት እንዳልኩ
- በየፊናው የወረወርኩት ካልሲ ፓንት ፀሀይ ሲወጣ አጥበዋለሁ እንዳልኩ
- መዝሙር የሞላሁት ስልኬን non-stop ሙዚቃ ከፍቼበት እንዳለሁ

- ያን ሹራብ የሆነ ቀንማ ገዝቼ እለብሰዋለሁ እንዳልኩ
- ቤቴ ያለውን ቆሻሻ እጠለዋለሁ እንዳልኩ
- ያለቁብኝ የማልፈልጋቸውን በፌስታል ያሉትን ሰልባጅ ልብሶቼን ለደሀ እሰጠዋለሁ እንዳልኩ

- ያቺ ምስኪን በኦርቶዶክስና በጴንጤ መሐል ነፍሷ የምተሰቃይባት ፕንኤል "ማሀትብ ገዝተህ ስጠኝ" እንዳለችኝ

- ድምጿን ለመስማት ስል "ይቅር ብዬሻለሁ" ብዬ የውሸቴን እንደታረቅኳት
- የሚፈልጉኝን ሁሉ “busy” ነው ብለው እንዲያስብኝ እንዳደረኩኝ

- ግንቦት መጨረሻ በዘነበው ዝናብ ወደጥቁርነት የተቀየረው ስሙን የማላውቀው “ብራንድ” ጫማዬ አጠበዋለሁ እንዳልኩ

- "ትንሽ ሳንቲም ከያዝን እንጋባለን?" ስባል ዝም እንዳልኩኝ
- የድሮ ፍቅረኛዬን ፎቶ "በፍቅር ስም" መጽሐፍ ውስጥ እንደከተትኩት
- የታሰረ ጎደኛዬን ሰላሙን ባሰማኝ እንዳልኩ

-"ኢትዮጵያን እንደርገጥኩ አንተን ነው ማየት የምፈልገው" እንደተባልኩ

-"ምን ላርግልህ አስበህበት ንገረኝ" እንደተባልኩ

-“ ካንተ አንድ ልጅ ብቻ እኮ ነው ምፈልገው"
"ከዛስ?"
"ከዛ ከፈልክ መጠተህ ታያታለህ"
"ሳታርግዢ ስሟን ጾታዋን ጨርሰሽኛላ"
"አትቀልድ"
"የምርሽን ነው?"
"አዎን ጀርመን ሳልሄድ በፊት እርግጠኛ እንድሆን ሰሞኑን ብናደርገው ምን ይመስልሀል?"እንደተባልኩ

-“ቤተልሔም መጽሐፌን አነበብከው” እንደተባልኩ

- ወገቤን የሚያመኝን ነገር "ፍልውኃ ግብቼ በውኃ ተመትቼ" እንዳልኩ

ይሄ ሰዓት
ይሄ ቅፅበት
ይሄ
ይሄ
ይሄ
የመጨረሻው መጨርሻው ቢሆንስ?
ያስፈራል?...
1.5K views19:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 11:18:59 ልጇን የጠረጠረ
የእናቱን አበሰረ"
ኤልያስ ሽታኹን
~ ~ ~ ~ ~
ነፍሴና ጉልበቴ ይሉልሻል በርከክ
ውዳሴሀ ለእግዝትነ ማርያም
ዘይትነብብ በ'ለተ ሰርክ::

ሰኞ
ቶማስን ያየ
ከንቱ ነፍሴ ያስብሻል በሰመመን
ልጅሽን የጠረጠረ ባንቺ የተዘጋ ማመን::

ኦ ማርያም
ናፍቆት የመላዕክት
ኦ ማርያም
የአዳም ምልክት

ማክሰኞ
ብልህ ነው እግዜሩ ብቻ ሁሌ ጥሩት
በእናት ይመልሳል ልጅ ቢጠረጥሩት::

ኦ ማርያም
መነሳት በቅድስና
ኦ ማርያም
እንበለ ሙስና::

ረዕቡ
እንደሚከተለው የክፉ ቀን ወጥመድ
ከቀጭን ሽቦ ላይ ፈርቶ እንደሚራመድ
እንደዚያ ሰው አለሁ::

ኦ ማርያም
ፀጋ ትምክህቱ
ኦ ማርያም
ሚካኤል እህቱ::

ሐሙስ
እንደዚያ ሰው አለሁ
ጨለማ ባቅሙ ደፍሮ ሚያስጨንቀኝ
መቀነትሽ ታጥቆ ማንስ ባጠመቀኝ?

ኦ ማርያም
ብሳሳት ነፍሴን
ነፍስሽ ታንሳት::
ኦ ድንግል ሆይ
ማርያምን ብረሳት
ነፍሴን ቀኜ ትርሳት::

አርብ(ስቅላት)
አትሂጅ ትተሽኝ አኑሪኝ በግርግም
ግድ ሆኖብኝ እንጂ መኖር አልፈልግም ::
ግድ ሆኖብኝ እንጂ የምመላለሰው
ግድ ሆኖብኝ እንጂ አፈር የምልሰው
ያነጫንጨኛል
የእናቱን መዳፍ ከእጁ እንደቀሙት
ልረፍና ጥሪኝ ከጥላሽ ስር ልሙት::

ቅዳሜ
ፍቅርሽ የለው ጠረፍ
መንገዴ ይቅናና ጥሪኝ ልቤ ይረፍ::

እሁድ
ደከመኝ እኮ ጌታዬ ደከመኝ እኮ የኔ አምላክ
ወይ እንደሰው አይደለሁ? ወይም እንደመልአክ?
ደከመኝ እኮ ማርያም - ደከመኝ እኮ እማምላክ

ደከመኝ እኮ

(16-12-14)
1.9K views08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 20:03:53 ብቻ ካንቺ ይሁን....
ኤልያስ ሽታኹን
~ ~ ~ ~ ~
ሁሉን እየቸረኝ
እግዜር አስቸገረኝ
ግን አንችስ?

ጠልተሽም እንደሆን አስተምሪኝ ልጥላ
ይከዳ የለም ወይ?
እንኳን የወደዱት የገዛ አካል ጥላ፡፡

ብቻ ካንቺ ይሁን....

ወደሽም እንደሆን አስተምሪኝ ልውደድ
ስንት ይለመድ የለ ወይ? ከመኖር ከመልመድ፡፡

ብቻ ካንቺ ይሁን....

አስተምሪኝና ልሁን እንደማንም
አንቺን ብዬ አይደለ የሆንኩኝ ሁሉንም፡፡
ብቻ ካንቺ ይሁን - መነሻ እትብቴ
ብቻ ካንቺ ይሁን - ቀዳሚት ሰንበቴ
ብቻ ካንቺ ይሁን - በጋና ክርምቴ
ብቻ ካንቺ ይሁን - ህይወትና ሞቴ
ብቻ ካንቺ ይሁን - ስስቱም ልገሳም
ብቻ ካንቺ ይሁን - መነከስ ወይ መሳም

ብቻ ካንቺ ይሁን....

በዚህ ባህር ዓለም መዋኘት እንደቻልሽ
አድኝኝ ጎትተሸ፡፡
መስጠሜም እንደሆን ይዘጋጅ ከፈኑ
"ሳይኖር ሞተ" ብለው
ቀላያት ነፋሳት ካንቺ ጋር ይዝፈኑ፡፡

ብቻ ካንቺ ይሁን....

(ታገኝው እንደሆን ንገርልኝ ለእግዜር)
1-
"እሱ ብቸኛ ነው
እሱ ባይተዋር ነው መኖር አያውቅበት
እኔን ስጠውና ሁሉን ውሰድበት"

2-
"መከራ ፈተና ቢመጡበት እኩል
መሻገሩ አይቀርም
ብቻ ላከው እንጂ በሚወድው በኩል "

~ ~ ~ ~ ~ ~
2.2K views17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 09:54:16
2.0K views06:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 22:01:34
2.3K views19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ