2022-08-31 14:21:15
#የመጨረሻው_ስብከት
The Christian News - የክርስቲያን ዜና
እንኳን በአሜሪካ ምድር በሌሎች አለሞችም እጅግ ታዋቂው ሰባኪ እና ጸሃፊ ፓስተር ሪክ ዋረን ታዲያ ይህ ታዋቂ ሰባኪ ከሰሞኑ የመጨረሻ የሆነውን ስብከቱን ማቅረቡን ክርስቲያን ፖስትን ጨምሮ በርካታ የክርስቲያን ሚዲያዎች ብፊት ገጻቸው ይዘውት ወጥተዋል።
ፓስተር ሪክ ዋረን ‘አላማ መር ህይወት’ በተሰኘው እና በበርካታ ቋንቋዎች በተተረጎመው መጽሀፉ ነው ብዙዎች የሚያውቁት በፈረንጆቹ 1980 ለመጀመሪያ ጊዜ የጀመራት አነስተኛ ቤተክርስቲያን ዛሬ 40ሺህ አባላት ያላት እና በአሜሪካ ምድር ግዙፍ የምትባል ቤተክርስቲያን ሆናለች።
የቤተክርስቲያኒቱ ስም "ሳድል ባክ ቤተክርቲያን ስትባል ላለፉት 43 ዓመታት በዋና መጋቢነት አገልግሎባታል ታዲያ ከሰሞኑ የአገልግሎቱ የመጨረሻ የሆነውን ስብከት ሰብኳል።
ከሁሉም በላይ አነጋጋሪ የሆነው ደግሞ ከ ዛሬ 40 ዓመታት በፊት "ሕይወታችሁን ዘላለማዊ ዋጋ ባለው ነገር ላይ አውሉት" በሚል ርዕስ የሰበከውን ስብከት በድጋሜ ለመጨረሻ ጊዜ መስበኩ ነው።
በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት የምትገኘው "ሳድል ባክ ቤተክርስቲያን" 40,000 አባላት ያሏት ሲሆን ከ 40 አመታት በፊት በፈረንጆቹ 1980 ዓ.ም በሪክ ዋረን እና ባለቤቱ ኬይ ዋረን በላግና ሂልስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተጀመረች ቤተክርስቲያን ነች።
መጋቢ ሪክ ዋረን የአገልግሎቱ መጨረሻ የሆነውን ስብከቱን ያቀረበው በአንድ የቤተክርስቲያኒቱ አባል በተሰራውና በመጀመሪያዎቹ 15 ዓመታት ይጠቀምበት በነበረው የእንጨት ፑል ፒት ላይ ሲሆን "ለ43 ዓመታት እናንተን መውደድ፣ ለእናንተ መጸለይ፣ ማገልገል ፣ መቃብር አጠገብ ቆሜ ማጽናናት ፣ አልጋ አጠገብ ቆሜ ማበረታታት፣ ሰርጋችሁ ላይ መሰበክ ፣ በአስቸጋሪ ጊዜያት መምከር እና ማስተማር እግዚአብሄር ለእኔ የሰጠኝ ትልቅ ዕድል ነበር በማለት ምዕመናኑን አመስግኗል።
ቤተክርቲያኒቱ በፈረንጆቹ ሴብቴምበር 3 እና 4 የፓስተር ሪክ ዋረንን የአገልግሎት 43ኛ ዓመት የምታከብር ሲሆን በሴብቴምበር 10 እና 11 ደግሞ ሪክ እና ባለቤቱ በአዲስ የአገልግሎት ዘርፍ የሚመደቡበት ቀን ይሆናል።
በሴብቴምበር 12 ደግሞ የግዙፏ ሳድል ባክ ቤተክርስቲያን አዲስ ሲኒየር ፓስተርን እንደምትሾም ክርስቲያን ፖስት አክሎ አስነብቧል።
253 viewsedited 11:21