Get Mystery Box with random crypto!

#_ታላቅ_የንግስ_በዓል_ጥሪ_በወይን_አምባ_ማርያም! #_ሚያዝያ_30_ሰኞ_ዕለት የመጥምቀ መለ | ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

#_ታላቅ_የንግስ_በዓል_ጥሪ_በወይን_አምባ_ማርያም!

#_ሚያዝያ_30_ሰኞ_ዕለት

የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ በዓለ እረፍት እና የወይን አምባ ማርያም ቅዳሴ ቤት!

ሼር በማድረግ ላልሰሙት አሰሙ አዳርሱ!

የወለላይቱ እመቤት ልጆች ተአምረኛው፣ ፈዋሹ፣ ጌታን ያጠመቀው መጥምቀ መለኮት የተባለው የቅዱስ ዮሐንስ ታቦቱ በወይን አምባ ማርያም አለ። ብዙዎች በተአምረኛ ጸበሉና እምነቱ እየዳኑ ነው።

ሚያዝያ 15 ቀን መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የከበረችው አንገቱ 15 ዓመት ዓለምን ዞራ ወንጌልን አስተምራ በክብር ያረፈችበት ዕለት ነው። እንዲሁም የተአምረኛዋ የወይን አምባ ማርያም ቅዳሴ ቤቷ ነው። የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ የከበረችው አንገቱ ያረፈችበትን ዕለት ለበዓሉ እንዲመች ሚያዝያ 30 ሰኞ በዕለተ ቀኑ ይከበራል።

ሚያዝያ 30 ሰኞ የመጥምቀ መለኮት እና የእመቤታችን ታቦቶች ወጥተው ሕዝቡን ይባርካሉ። ስለዚህ መጥታችሁ ከበዓሉ ረድኤት፣ ከጥምቀቱ ድህነት፣ ከዝክሩ በረከት ተካፈሉ!

#_የትራንስፖርት_መምጫው ፦

ከየትኛውም አቅጣጫ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርዳችሁ፣ ሠፈራ ብላችሁ በባጃጃ ተሳፍራችሁ፣ ድልድዩን እንደተሻገራችሁ አስፓልቱ ጫፍ ላይ ቤተ ክርስትያኗ ትገኛለች።

ከመገናኛ በቀጥታ ጎሮ ብለው ተሳፍረው፣ ጎሮ አደባባይ ወርደው፣ ከዚያ ባጃጅ ተሳፍረው፣ ሠፈራ ድልድይ ጫፍ ላይ ስትወርዱ ትገኛለች፡፡

ከመገናኛ ቀጥታ ወይን አምባ ማርያም ብላችሁ መሳፈር ትችላላችሁ።

ከሲ አምሲ፣ ከአያት፣ ከሰሚት የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርደው፣ ባጃጅ ተሳፍረው ሠፈራ ድልድይ ጫፍ ወርደው ትገኛለች፡፡

ከቃሊቲ፣ ከቱሉ፣ ዲምቱ፣ ከኮዬ ፈጩ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርደው ከዚያ በባጃጅ ተሳፍረው ሠፈራ ድልድይ ወርደው ጫፍ ላይ ትገኛለች፡፡

ማያዝያ 25-8-15 ዓ.ም

ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

አዲስ አበባ