Get Mystery Box with random crypto!

ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የሰርጥ አድራሻ: @memehirhenok
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 12.40K

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2023-03-27 18:51:32

1.8K views15:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 09:31:24
1.4K views06:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 09:31:18 #_የንስሐ_እና_የቄደር_ጥምቀት_ጥሪ!

#_በካሊፎርኒያ_ሳክራሚንቶ_አሜሪካ!

#_March_31_ወይም_መጋቢት_22_አርብ_ጠዋት_3_ሰዓት

"ጥሩ ውኃንም እረጭባችኃለሁ እናንተም ትጠራላችሁ" ሕዝቅ 36፥25

"የትኛውንም ኃጢአት ብንሠራ ሁሉም ኃጢአቶች ከንስሐ በታች ናቸው። ከንስሐ በላይ የሆነ ኃጢአት የለም። የእኛ ኃጢአት ከእግዚአብሔር ቸርነት በላይ አይደለም"

#_ቄደር_ለመጠመቅ_የሚያበቁን_ኃጢአቶች_የትኞቹ_ናቸው?

#_ቄደር_ለምን_እንጠመቃለን?

#_ቄደር_በመጠመቃችን_ምን_ጥቅም_እናገኛለን?

የነፍስ ጉዳይ ነውና ሳትቸኩሉ በደንብ አንብቡት!

"የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት ለጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና።" 1ኛ ጴጥ 4፥3

ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

#_ሼር_በማድረግ_የነፍስ_ግዴታዎትን_ይወጡ!

ተወዳጆች ሆይ Mar 31 አርብ ጠዋት 3 ሰዓት በደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ወቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስትያን ካሊፎርኒያ ሳክራሚንት የቄደር ጥምቀት እና ንስሐ የመስጠት አገልግሎት ስላለ መጥታችሁ ንስሐ ግቡ ቄደር ተጠመቁ። እባካችሁ ሰዓቱን ጠብቃችሁ ኑ። በተቻለ መጠን ደጇ ሁለት ሰዓት ድረሱ!

ወዳጆቼ ጌታችን ጾማችንን፣ ጸሎታችንን፣ ልመናችንን እንዲቀበልልን እኛ ደግሞ ንስሐ መግባት ግድ ይለናል። በተለይ ታላቁን ዓብይ ጾም በንስሐ ብንቀበል እግዚአብሔር በንሰሐ የሆነውን ጸሎታችንን፣ ጾማችንን ይቀበላል። ግድ የለም ጊዜው ፈተናው ያለሰባኪ አስታማሪ ነውና ንስሐ ገብተን ከእግዚአብሔር የሚሆነውንና የሚሆንልንን እንጠባበቅ።

የጸሎት መርሃ ግብሩ ካለቀ በኋላ ብትጠመቁ ዋጋ የለውም። ምክንያቱም ለምሳሌ የጸሎቱ መርሃ ግብር ላይ አቡነ ዘበሰማያት 41 ጊዜ ካርያላይሶን 41 ጊዜ እግዚኦ መሃረነ ክርስቶስ ወዘተ እንድትጸልዩ ስለሚሰጣችሁ እነዚህን ጸሎቶች ሳትካፈሉ ሰዓት አርፍዳችሁ ብትመጡ መጠመቅ አይቻልም። ስለዚህ የነፍስ ጉዳይ ነውና ሰዓት ይከበር።

#_ቄደር_ለመጠመቅ_የሚያበቁን_ኃጢአቶች_የትኞቹ_ናቸው?

ቀደር ለመጠመቅ የሚያበቁን ኃጢአቶች ለምሳሌ ረቡዕ ብና አርብ የፍስክ ከበላን፣ ውርጃ ከፈጸምን፣ ከሃይማኖታችን ውጪ ካሉ ሰዎች ጋር ሩካቤ ሥጋ ከፈጸምን፣ በልጅነት እና ካደግን በኃላ ግብረ ሰዶም ከፈጸምን፣ ከእንስሳት ጋር ግንኙነት ካደረግን፣ በልጅነት መሬትን ካወሰብን፣

ከሥጋ ዘመድ ጋር ግንኙነት ከፈጸምን፣ ቅዱስ ቁርባን ተቀብለን በዝሙት ከወደቅን፣ በቅዱስ ቁርባን አግብተን ባል በሚስት ላይ ሚስት በባል ላይ ከዘሞተች፣ ኢ- ሩካቤ ከፈጸምን ማለት ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ ግንኙነቶችን ከፈጸምን፣ የአሕዛብን ምግብ ከበላን፣ ኦርቶዶክስ ሆነን ወደ ሌላ እምነት ገብተን ከተመለስን፣

ለዛር ለጨሌ ለአቴቴ ከገበርን፣ የተገበረውን መስዋዕት ከበላን፣ ጠንቋይ ቤት ከሄድን፣ ዛር አንጋሽ ጋር ከሄድን፣ ግለ ወሲብን ከፈጸምን፣ ሴት የወር አበባዋን ሳትጨርስ ግንኙነት ካደረገች፣ ወንድም የወር አበባ ካልጨረሰች ሴት ጋር ግንኙነት ካደረገ፣ ጫት ሲጋራ ከተጠቀምን ወዘተ ቄደር የግድ መጠመቅ አለብን።

ወዳጆቼ ልብስ በሳሙና ይታጠባል በመጨረሻ በኦሞ ተዘፍዝፎ ይለቀለቃል። በዚህም ጸዐዳ ይመስላል። ንስሐ ኃጢአታችንን የምናጥብበት ሳሙና ነው። ቄደር ደግሞ ኦሞ ነው ያነጻናል።

በተለይ ንስሐ ገብታችሁ ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል ያሰባችሁ ቄደር ተጠምቃችሁ ብትቀበሉ መልካም ነው። በንስሐ ያላካተትነው ኃጢአት በቄደር ይነጻልና። እንዲሁም በቄደር ነጽተን ቅዱስ ቁርባን ብንቀበል ይሰምርልናል።

የወለላይቱ እመቤት ልጆች የትኛውንም ኃጢአት ብንሠራ ሁሉም ኃጢአተቶች ከንስሐ በታች ናቸው። ከንስሐ በላይ የሆነ ኃጢአት የለም። የእኛ ኃጢአት ከእግዚአብሔር ቸርነት በላይ አይደለም።

የእኛ ኃጢአት የደም ጠብታ ነው። የእግዚአብሔር ቸርነት ደግሞ ውቅያኖስ ነው። ስለዚህ የደም ጠብታ የውቅያኖስን ውሃ እንደማያደፈርስ ሁሉ የትኛውም የእኛ ኃጢአት የእግዚአብሔርን ቸርነት አይበልጥም። ንስሐ ግቡ ቄደር ተጠመቁ።

Mar 25-2023
ካሊፎርኒያ ከሜሪካ
1.4K views06:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 07:12:54

359 views04:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 18:53:42

1.1K views15:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 01:03:24

1.1K views22:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 18:43:49

1.6K views15:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 06:55:54
418 views03:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 06:55:50 ስለዚህ ይህ የጌታችን የምጻት ቀን ለኃጥአን እለተ ፍዳ ናት፡፡ ለጻድቃን ደግሞ የደስታቸው ቀን ናት፡፡ ጌታችንን ተዘጋጅተን ከጠበቅነው በእውነት ይህቺ ቀን በትንሽ የጽድቅ ሥራችን ብዙ ዋጋ የምንቀበልበት፣ በብዙ የጽድቅ ሥራችን ደግሞ እጥፍ ደርብ የሚንቀበልበት ቀን ናት፡፡
ይችህ ቀን ዳግም ምጻት የትንሳኤ ሙታን መቅድም ነው፡፡ ወይም ቅድመ ሁኔታ ነው፡፡ ምክንያቱም ጌታ ሲመጣ ነው የሞቱት የሚነሱት፡፡

እኛ የሰው ልጅች ከሞትን በኃላ ፈርሰን በስብሰብ የምንቀር አይደለንም፡፡ ይልቁንም አፈር ትብያ ከሆን በኃላ በመጨረሻ እለት ህይወትን አግኝተን እንነሳለን፡፡ ትንሳኤያችንም በሁለት የተከፈለ ነው፡፡ የክብር ትንሳኤ እና የሐሳር ትንሳኤ ነው፡፡ የክብር ትንሳኤ የምንለው በሠራነው ስራ ከብረን የምንነሳበት፤ ዋጋ የምንቀበልበት ነው፡፡ የሐሳር ትንሳኤ የምንለው ፍዳና መከራ ለመቀበል የምንነሳው ነው፡፡

ግን ዋጋችንን ተቀብለን ወደ መንግስተ ሰማያት ለመግባት በመጨረሻ እንደ ይለፍ የሚጠይቀን ነገር አለ፡፡ እሱም በማቴዎስ ወንጌል በምዕራፍ 25÷34 ጀምሮ ‹‹እናንተ የአባቴ ብሩካን ኑ ዓለም ከተረጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችኑን መንግስቴን ውረሱ›› ለመባል ምግባርን፣ ሰብአዊነትን፣ ርህራሄን፣ የተመለከቱ ጥያቄ እንጠየቀቃለን፡፡
እነሱም ተርቤ አብልታችሁኛልን፤ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልን እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልን፤ታርዤ አልብሳችሁኛልን፤ታምሜ ጠይቃችሁኛልን፣ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኃልን›› በማለት ይጠይቀናል፡፡

እኛም ጌታን መቼና የት አግኝንተንህ በማለት ለማምለጥ ብንሞክር በማቴዎስ 25÷45 ባለው ቃል ‹‹ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ለአንዱ ስላላደረጋችሁት ለእኔ ደግሞ አላደረጋችሁም›› በማለት ያሳፍረናል፡፡
ብዙዎች እንደሚመስላቸው የምንጠየቀው በእሱ ማመናችንን ብቻ ሳይሆን በእሱ ስም ምንም ባለማድረጋችን እንጠየቃለን፡፡ ጥያቄውም በእምነት የሆነ ምግባር ነው፡፡

ለዚህም ነው ቅዱስ ያዕቆብ በ 2÷26 ላይ ‹‹ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደሆነ፤እንዲሁ ደግሞ ከሥራ/ከምግባር/ የተለየ እምነት የሞተ ነው›› ያለው፡፡ ስለዚህ ጌታችን መቼ እንደሚመጣ፤ ዛሬ ይሁን ነገ፤ ቀን ይሁን ሌሊት አናውቅምና በንስሐ ተዘጋጅተን በስጋ ወደሙ ታትመን ልንጠብቀው ይገባል፡፡ ምክንያቱም ጌታችን በማቴዎስ ወንጌል በ 24÷42 ላይ ‹‹ጌታችሁ በምን ሰዓት እደሚመጣ አታውቁምና እንግዲህ ንቁ›› ብሎናል፡፡

ስለዚህ ከተኛንበት ኃጢአት በንስሐ ልንነቃ ይገባል፡፡ ከክፋት መንገድ ርቀን በጽድቅ ጎዳና ለመጓዝ መዘጋጀት አለብን፡፡ ምክንያቱም ብዙዎቻችን የክርስቶስ መምጫው ገና ነው በማለት በንስሐ መዘጋጀት አልቻልንም፡፡ ግን ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት ሞት ለብዙዎች ክፉ ምጻት በመሆን ህይወትን እየቀጠፈ ነው፡፡ ላወቀበት ሞት ምጻት ነው፡፡ በድንገት ባልታሰበ ሰዓት ሞት የስንቱን ቤት እያንኳኳ ነው፡፡

ሰው ንስሐ ገብቶ ተዘጋጅቶ ለመኖር የግድ የክርሰቶስን እለተ ምጻት በማሰብ ብቻ ሳይሆን ድንገተኛው፣ ቀጠሮ አልባው፣ የንስሐ እድል የማይሰጠውን፣ ሞት እንደ እለተ ምጻት፣ በማሰብ መዘጋጀት አለብን፡፡
ምክንያቱም ስለዛች አስጨናቂ ሰዓት ማለትም ኃጥአን ጨለማን የሚጎናጸፉባት፤ጻድቃን ብርሃን ስለሚለብሱባት ቀን ከእግዚአብሔር በቀር በሰማይ ያሉ መላእክቶች፤ በምድር ያሉ የሰው ልጆች አያውቁም፡፡

ስለ ቀኒቱም ቅዱስ ጴጥሮስ በ2ኛ ምልእክቱ በምዕ 3÷10 ላይ ‹‹የጌታው ቀን ግን እንደ ሌባ ሆኖ ይመጣል፡፡ በዚያም ቀን ሰማያት በታላቅ ድምጽ ያልፋሉ፣ የሰማይ ፍጥረት በትልቅ ትኩሳት ይቀልጣል፣ምድርም በእርሷዋም ላይ የተደረገው ሁሉ ይቃጠላል›› በማለት ተናግሯል፡፡

ወገኖቼ የጌታ ቀኑ መድረሱን የተፈጸሙት ምልክቶች ይናገራሉ፡፡ ዛሬ ዓለም ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ሁኔታዋ እየተለዋወጠ ለመጥፋት እጠሮጠች ነው፡፡ እኛም የሰው ልጆች መንገዳችን ከእግዚአብሔር ስለራቀ ፈተናችን መከራችን በዝቷል፡፡
በርዕሳችን እንዳነሳነው ጌታችን ተዘጋጅታችሁ ኑሩ ብሎናል ስለዚህ እንዴት ነው የምዘጋጀው?

በመንፈሳዊ ህይወት ዝግጅት የምንለው፤ ለነፍስ ማሰብ ነው፡፡ ዝግጅታችንም ስለ እውነት ቀላል ነው፡፡ ለብዙ ዓመታት የሰራነውን ኃጢአት በአንዲት እለት በንሰሐ ማራገፍ ነው፡፡ የትኛውንም በደል እና ኃጢአት ብንሰራ ኃጢአታችን እግዚአብሔር ከሰጠን ከንስሐ በላይ አይሆንም፡፡ እግዚአብሔርም በንስሐ ይቅር የማይለን አንዳችም ኃጢአት የለም፡፡ እስኪ እኛ ለንስሐ እንዘጋጅ፤ እግዚአብሔር የሚያደርግልንን የቸርነቱን፣ የፍቅሩን ሥራ እናያለን፡፡

መዘጋጀት ማለት፦ ንስሐ መግባት የበደሉትን መካስ፣ የቀሙትን መመለስ፣ የተጣሉትን መታረቅ፤ቂም የቋጠሩበትን ልብ በይቅርታ መፍታት፤ በጾም በጸሎት ተግተን በመጨረሻም ቅዱስ ስጋውንና ክቡር ደሙን መቀበል ነው፡፡ ይህን ካደረግን የክርስቶስን ሰማያዊ መንግስት ለመውረስ ዝግጁ ነን ማለት ነው፡፡

የአባቶቻችን አምላክ ልዑለ ባህሪይ ቅዱስ እግዚአብሔር ስለሁሉም ነገር እርሱ ይርዳን፡፡ ፍጻሜያችንን ያሳምርልን፡፡ ጌታችን ሊፈርድብን ሳይሆን ሊፈርድልን፤ ሊኮንናን ሳይሆን ሊያጸድቀን፤ ሰማያዊ የክብር ዋጋችንን ሊሰጠን ከፈለግን፤ በንስሐ ተዘጋጅተን እንጠብቀው፡፡

‹‹እንግዲህ እንዴት እንደተቀበልህና እንደ ሰማህ አስብ ጠብቀውም ንስሐ ግባ፡፡ እንግዲያስ ባትነቃ እንደ ሌባ እመጣብሃለሁ በማናቸው ሰዓት እንደምመጣ አታውቅም›› በማለት አመጣጡ ስውርና ድንገት መሆኑን በራዕ 16 ÷15 ላይ ነግሮናል፡፡

‹‹ተዘጋጅታችሁ ኑሩ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰአት ይመጣልና››

‹‹አዎ በቶሎ እመጣለሁ ይላል፡፡ አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ና፡፡
ራዕ 22÷20

መጋቢት 10-7-15 ዓ.ም

ካሊፎርኒያ አሜሪካ
429 views03:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 06:55:50 እንግዲህ ምጽአት የምንለው ጌታችን ዳግም ወደዚህ ዓለም ለፍርድ የሚመጣበት ጊዜ ነው፡፡ ምጽአት በሁለት ያከፈላል፡፡ አንደኛ የጌታ ምጽአት እና ሁለተኛ የጌታ ምጽአት ይባላል፡፡

የመጀመርያው የጌታ ምጽአት የምንለው ፦ ነብያት በተነበዩት፤አባቶች በሱባኤ ተስፋ ባደረጉት መሰርት ጌታችን ከድንግል ማርያም ተወልዶ ወደዚህ ምድር መምጣቱን ነው፡፡ ይህ ምጽአት ጌታ ለመአት ሳይሆን ለምህረት፣ ለአሳር ሳይሆን ለፍቅር፤ ለጸብ ሳይሆን ለእርቅ የመጣበት ነው፡፡ ይህ ምጻት የጌታን ምህረትና ለሰው ያለውን ፍቅርና ቸርነት ያየንበት ነው፡፡

ይህ ምጽአት የጌታን ፍርድ ሳይሆን የፍቅር መንገድ አሳይቶናል፡፡ ይህ ምጽአት እኛ የሰው ልጆች የዳንበት ነው፡፡ ይህ ምጽአት በሰይጣን ያጣነውን የልጅነት ክብር ያስመለሰልን ነው፡፡ ይህ ምጽአት ስለ እኛ ፍቅር ከግርፋት እስከ ሞት ዋጋ የከፈለበት ነው፡፡ ይህ ምጽአት ስጋውን የቆረሰበት ደሙን ያፈሰሰበት ነው፡፡

በዚህ ምጽአት ከክርስቶስ ጋር በእናቱ በእመቤታችን በድንግል ማርያም በኩል በስጋ የተዛመድንበት ነው፡፡ በዚህ ምጽአት በረከተ ስጋ በረከተ ነፍስ አግኝተንበታል፡፡ በዚህኛው ምጽአት ብዙዎች የንስሐ እድል አግኝተዋል ከቅድስናው በረከትም ተካፍለዋል፤ የሰማይ ቤታቸውንም አሳምረዋል፡፡

በመጀመሪያው ምጽአት ጌታ ከፈሪሳውያን ከሰዱቃውያን ጀምሮ ያሉትን ተከታዮቹንም አስተምሯል፤ መክሯል፤ የታመሙትንም ፈውሳል፤ ድንቅ ድንቅ ተአምራት አድርጓል፡፡ ይህ ምጽአት ደስ የሚያሰኝ ነበር፡፡

በሁለተኛውና በሚጠበቀው ምጽአት ፦ ጌታችን እንደ ቀድሞው በትህትና በፍቅር ሳይሆን ሊነገር በማይችል በታላቅ ክብር ነው የሚመጣው፡፡ በዚህ ምጽአት አይታገስም፤ ፊቱንም ለማየት አይቻልም፡፡ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስፈራ ግርማ መለኮት፤ በታላቅ መፈራት ይመጣል፡፡ ይህንንም ቅዱስ ማቴዎስ 24÷ 30 ላይ ‹‹የሰው ልጅ በኃይልና በታላቅ ክብር በደመና ላይ ሆኖ ይመጣል›› ብሏል፡፡

ይህንንም ጌታ በሐዋርያት ፊት በደመና በሚያርግበት ጊዜ ሁለት ሰዎች ተብለው የተገለጡት የጌታ መላእክት ‹‹ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት እንዲሁ ይመጣል›› ብለው ጌታ ለፍርድ እንደሚመጣ ተናግረዋል፡፡ /የሐዋ 1÷11/

ታድያ ጌታችን በመጨረሻ የሚመጣው ለምህረት ለይቅርታ ለቸርነት ሳይሆን ለእያንዳንዱ ሰው በዚህ ዓለም እንደ መልካምና ክፉ ሥራው ዋጋውን ለመስጠት ነው፡፡ ይህንንም ጌታችን በዮሐንስ ራዕይ በምዕራፍ 22÷12 ላይ ‹‹እነሆ በቶሎ እመጣለሁ፣ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ›› ብሎናል፡፡

ሲመጣ እንደ ቀድሞ ሰው ሆኖ በትህትና፤ በታላቅ ሰብእና ሆኖ ሳይሆን በፈራጅነቱ በዳኝነቱ በአምላክነቱ በግርማ መለኮቱ ነው፡፡ ዳኝነት ስንል በሰጠን ህግ ያለ ርህራሄ እንዳኛለን፡፡ እውነተኛ ዳኛ ዘመድ ባዳ ሳይል በህጉ ይዳኛል፡፡ ጌታም ኃጥእ ጻድቅ ሳይል በሥራችን ይዳኘናል፡፡

በዚህኛው ምጽአት የንስሐ እድል የለም፤ የንስሃን ዋጋ በቀበል እንጂ፡፡ ጽድቅ የመሥራት እድል የለም፤ የጽድቅን ዋጋ መቀበል እንጂ፡፡ በዚህኛው ምጻት ሥጋ በበደለበት ነፍስ የሚቀጣበት ነው፡፡ ሥጋ በጎ ነገር በሠራበት ነፍስ ዋጋ ተቀብላ፤ ጸጋን ታድላ፤ ለዘላለም ከጌታዋ ጋር የምትኖርበት ነው፡፡ ይችህ ቀን ምንኛ ታስፋራ ይሆን!

ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ በቅዳሴው ከሚያስፈሩት ነገሮች ውስጥ አንደኛው በአምላክ ፊት ለፍርድ መቆም መሆኑን ተናግሯል፡፡ ወገኖቼ እግዚአብሔር ፊት እንኳን ለፍርድ ለሽልማት መቆም እጅጉን ያሥፈራል፡፡ በፍርድ ቀን ባለጸጋው ስለ ባለ ጻግነቱ አይፈራም፤ ድሃም ስለ ድህነቱ አይታዘንለትም፡፡ ሁለም የሥራውን ያገኛል፣ በክርስቶስ ፊት የዘራውን ያጭዳል፡፡

የእግዚአብሔር ልጆች ጌታ ሲመጣ ምን ይዘን እንጠብቀው ይሆን? ከጌታ ምጽአት በፊት ሞት ሲቀድመን፤ በነፍሳችን ምን ይዘን እንሄድ ይሆን?

ይቺ ቀን ጌታችን ህጉን ትእዛዙን አክብረው በተሰጣቸው እድሜ በጎ ነገር ሰርተው ላለፉት፤ ለተገኙት የማታልፍ መንግስተ ሰማያትን የሚያወርስበት ቀን ነው፡፡ ለኃጥአን ማለትም ንስሐ ሳይገቡ፤ ነፍሳቸውን ኃጢአት ሲቀልቡ፤ ለኖሩት ፍዳና ገሃነመ እሳትን የሥራቸው ዋጋ አድርጎ ይከፍላቸዋል፡፡ ግን ጌታችን ለጻድቃን ይፈርድላቸዋል በኃጥአና ላይ ይፈርድባቸዋል ስንል ጌታችን ና አንተ ጻድቅ ነህ የሚገባህ ይህ ነው፡፡ ና አንተ ኃጥእ ነህ ዋጋህ ይህ ነው ብሎ በተናጠል አይፈርድም፡፡ ለእኛ የሚፈርድልንና በእኛ ላይ የሚፈርድብን ሥራችን ነው፡፡ እርሱ ዋጋችንን ነው የሚሰጠን፡፡

የሠራነው ጽድቅና መልካም ሥራ ከሆነ በጻድቃን ጎን ያቆመናል፡፡ ሥራችን ኃጢአት እና ክፉት ከሆነ በኃጥአን ጎራ ያሰልፈናል፡፡ ጌታችን በማቴ 25÷31-33 ‹‹የሰው ልጅ በክብሩ በሚመጣበት ጊዜ ከእርሱ ጋር ቅዱሳን መላእክቱ ሁሉ በዚያን ጊዜ በክብሩ ዙፋን ይቀመጣል፤ አሕዛብም ሁሉ በፊቱ ይሰበሰባሉ፤ እረኛም በጎቹን ከፍየሎች እንደሚለየው እርስ በእርሳቸው ይለያቸዋል፤ በጎችን በቀኙ ፍየሎችንም በግራው ያቆማቸዋል›› ቢልም የሚለየን ወገኖቼ ሥራችን ነው፡፡

ያኔ በሥራችን እርስ በእርስ እንለያያለን፡፡ ጌታ ለምንድነው ጻድቃንን በበጎች ኃጥአንን በፍየሎች የመሰለው? ብንል፡፡
በግ ፦ ትሁት ነው ወደ ምድር እያየ ይሄዳል፡፡ ጻድቃንም እለተ ሞታቸውን እያሰቡ በትህትና ይኖራሉና፡፡

በግ አፍረቷን በላቷ ትሰውራለች፡፡ ጻድቃንም የራሳቸውን ኃጢአት በንስሐ፤ የወንድማቸውን ኃጢአት በትእግስት ይሰውራሉና፡፡ እኛ ግን ለራሳችን እንደ ሸክም የከበደንን ኃጢአት ሰውረን፤ የሰውን ገልጠን እንኖራለን፡፡ የራሳችን ኃጢአት እንደ ምሰሶ በውስጣችን ተተክሎ፣ የሰውን ጉድፍ ነቅሎ ለመኖር እንጥራለን፡፡

በግ ከበረረ የሰው ልጅ ካመረረ እንደሚባለው በግ ከመካከላቸው አንዱን አውሬ ከነጠለው ይሸሻል አይመለስም፡፡ ጻድቃንም ከመካከላቸው አንዱ ከሞተ ሞታቸውን በማሰብ ወደ እግዚአብሔር ይጠጋሉ፡፡ የቆረጡትም ይመንናሉ ከመነኑም አይመለሱም፡፡ እኛ ግን ባየነው የወዳጅ የዘመድ ሞት፤ ለንስሐ ሕይወት መብቃት አቃተን፡፡
በግ ኑሮው በደጋ ነው፡፡ ጻድቃንም በደጋ በተመሰለው በመንግስተ ሰማያት ነው ኑሮአቸው፡፡ ስለዚህ በበግ ተመለሱ፡፡

ፍየል ፦ ትእቢተኛ ናት፡፡ ሽቅብ ሽቅብ ትመለከታለች፡፡ ፍየል ኃፍረቷን በላትዋ አትሰውርም፡፡ ኃጥአንም የራሳቸውን ኃጢአት በንስሐ፤ የወንድማቸውን ኃጢአት በትእግስት አይሰውሩም፡፡ እኛም ኃጢአታችንን በንስሐ አንሰውርም፡፡

ፍየል በዋለበት ቦታ፤ እህል፣ ከተክል እየገባ እየበላ ሰው ሲያሳዝን ይውላል፡፡ ኃጥአንም ሰውንም ፈጣሪንም ሲያሳዝኑ ይውላሉና፡፡
ፍየል ከመሃላቸው አንዱን አውሬ የበላው እንደሆነ ለጊዜው ይሸሻል፤ ኃላ ግን ይመለሳል፡፡ ኃጥአንም ከወገናቸው አንዱ የሞተ እንደሆነ ለጊዜው ይደነግጣሉ፤ ኃላ ወደ ቀደመ ግብራቸው ይመለሳሉ፡፡ ብዙዎቻችን የሰው ሞት ስናይ ለጊዜው እንደነግጣለን፤ ስለነፍሳችንም እንጨነቃለን ግን ብዙም ሳንቆይ እንረሳዋለን፡፡

ፍየል ኑሮው በቆላ ነው፡፡ ኃጥአንም የነፍስ ኑሮአቸው በቆላ በተመሰለው በገሃነም ነው፡፡ ለዚህ ነው ጌታ ጻድቃንን በበግ ኃጥአንን በፍየል የመሰለው፡፡ የአባቶቻችን አምላክ በቆላ ከተመሰለው ከሲኦል ይሰውረን፡፡
332 views03:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ