Get Mystery Box with random crypto!

ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የሰርጥ አድራሻ: @memehirhenok
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 12.40K

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-03-19 06:55:50 #_ተዘጋጅታችሁ_ኑሩ_የሰው_ልጅ_በማታስቡበት_ሰዓት_ይመጣልና!

/ማቴ 24፥44/

/የጌታችንን እለተ ምጽአት ታሳቢ ተደርጎ የተጻፈ/

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ!

ተወዳጆች ሆይ "ተዘጋጆታችሁ ኑሩ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና" ብሎ የተናገረው ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይሁንና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ በሐዲስ ኪዳን ብዙ ቦታ ጌታችን እራሱን አምላክ በማለት ሳይሆን ‹‹የሰው ልጅ›› በማለት ነው እራሱን ይገልጽ የነበረው፡፡ ጌታችን ስለ መወለዱ፤ ስለ ቤዛነት አመጣጡ፤ ስለ ሞቱ፤ ስለ ትንሳኤው፤ ስለ ዕርገቱ፤ ስለ ዳግም ምጽአቱ፤ ስለ ሰማያዊው የፍርድ ሂደቱ ሲናገርና ሲያስተምር ‹የሰው ልጅ› እያለ ይናገር ነበር፡፡ አምላክ ቢሆንም የሰውን ሥጋ ስለለበሰ እራሱን የሰው ልጅ አለ፡፡

ጌታችን እራሱን እንዲህ በማለት በመግለጹ ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያን አምላክነቱን ለመረዳት አልቻሉም፡፡ ወትሮም በትህትና ስለ ሰው ልጆች ፍቅር ነውና የመጣው፤ እራሱን አምላክ ፈጣሪ ከማለት ይልቅ የሰው ልጅ በማለት ገልጿል፡፡

እንግዲህ ለዚህ የጌታችን ትምህርት ምክንያት የሆነው የሐዋርያት ጥያቄ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታችንን ብዙ ጥያቄ እየጠየቁ ከጌታ ምላሽ ቢያገኙም፤ ሰው ናቸውና እንደ ሰው አስጨንቋቸው ከጠየቁት ጥያቄዎቸ ውስጥ አንዱ ስለ እራሱ ስለ ጌታችን መምጣትና ስለ ዓለም መጨረሻ ነው፡፡ ይህን ጥያቄ ሲጠይቁ ለጥያቄያቸው ደረቅ ምላሽ ብቻ ሳይሆን የጥያቄውን መልስ ምልክትም ጭምር ነው የጠየቁት፡፡ ይህም ሐዋርያትን ስለ ጌታ መምጣት እና ስለ ዓለም መጨረሻ ያላቸውን ጭንቀት ያሳየ ነበር፡፡

ሐዋርያት ምንም እንኳን ከጌታቸው ጋር ውለው ቢያድሩም፤ አምላክነቱን ቢያምኑም፤ የእሱ መምጫው ስለማይታወቅ፤ መምጫውንና ምልክቱን ጠየቁት፡፡ በእርግጥ እነርሱ የነበሩበት ዘመን ጌታችን በሥጋ የተገለጠበት ቢሆንም፤ የዓለም ፍጻሜና የክርስቶስ ዳግም ምጻት አስጨናቂ ስለሆነ፤ ይልቁንም መንፈሳዊ ዝግጅትን የሚጠይቅ ስለሆነ ለሰማያዊው ሽልማት፤ በንስሐ መዘጋጀት ስለሚያስፈልግ ለእኛ ጠይቀውልናል፡፡ እነሱማ ጌታቸው እንኳን ለፍርድ ሊመጣ ገና ተሰቅሎ ዓለምን በሞቱ እንደሚያድን አላዩም፡፡ ስለዚህ በእኛ እግር ገብተው ነው የእሱን መምጣት ከነምልክቱ የጠየቁት፡፡

የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያንም አማኝ ልጆችዋ እንዲያውቁ እንዲጠነቀቁ አጥብቃ ከምታስተምራቸው ትምህርቶች ውስጥ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ እለተ ምጽአት ወይም ዳግም ምጽአት ነው፡፡ በተለይም በቤተ ክርስትያንዋ ከሚፈሩት ትምህርቶች አንዱ ነው፡፡

በዚህ ትምህርት ውስጥ የምንኖርባት ዓለም ኃላፊ ጠፊ መሆንዋ፤ ሰውም ሰንባች ሳይሆን ሟች መሆኑን አጥብቃ የምታሳስብበት ትምህርት ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ትምህርቱ በነፍስ የክርስቶስን መንግስት ለመውረስ ያዘጋጃልና፡፡ በእርግጥ የሰው ልጅ ፍጻሜው እለተ ሞቱ ነው፡፡ ይህ ትምህርት በቤተ ክርስትያኒቱ ይሰጥ እንጂ አስተማሪው ጌታችን ነው፡፡ ትምህርቱም ሊሰጥ የቻለው ከላይ እንዳልኩት በሐዋርያት ጠያቂነት ነው፡፡

ቅዱሳን ሐዋርያት የአለም ፍጻሜ እንዳለ፤ እግዚአብሔርም የፈጠረውን አለምና ፍጥረት ሊያሳልፍ እንደሚመጣ በትንቢት ያውቃሉ፡፡ ነብዩ ኢሳያስ ‹‹የእግዚአብሔር ቀን ይመጣል›› ብሎዋል፡፡ /ኢሳ.13÷9/ ነብዩ ኢዮኤልም ስለ ቀኑ ሲናገር ‹‹የእግዚአብሔር ቀን ቀርቦአልና ለቀኑ ወዮ›› በማለት ተናግሯል፡፡ /ኢዮ 1÷15/ ስለዚህ እለተ ምጽአት የእግዚአብሔር ቀን ናት፡፡

ቅዱስ ዳዊትም በመዝ. 49÷2-4 ላይ ‹‹እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል፡፡ አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም፤ እሳት በፊቱ ይቃጠላል፣ በዙርያውም ብዙ አውሎ አለ፡፡፡ በላይ ያለውን ሰማይን ምድርንም፤ በሕዝቡ ለመፍረድ ይጠራል›› ብሏል፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ግን ጌታ መቼ እንደሚመጣ፤ እንዴት እንደሚመጣ ስለማያውቁ በተለይም የመምጣቱ ነገር ስላስጨነቃቸው ጌታቸውን በደብረ ዘይት ተራራ ጠይቀውታል፡፡

ደብረ ዘይት ከኢየሩሳሌም በስተ ምስራቅ በኩል የሚገኝ ኮረብታማ ስፍራ ነው፡፡ በተለይ በቦታይ የወይራ ዛፍ በብዛት ስለሚገኝ ደብረ ዘይት ተብላል፡፡ የአብይ ጾም አጋማሽም ደብረ ዘይት የተባለው በዚህ ቦታ ስያሜ ነው፡፡ ደብረ ዘይት ጌታችን ከሚያዘወትራቸው ቦታዎች አንዱ ነበር፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በምዕራፍ 22÷39 ላይ ‹‹ወጥቶም እንደ ልማዱ ወደ ደብረ ዘይት ሄደ›› ማለቱ ቦታውን ማዘውተሩን ያሳየናል፡፡

እንዲሁም በምዕራፍ 21÷37 ላይ ‹‹ሌሊት ግን ደብረ ዘይት ወደ ምትባል ተራራ ወጥቶ ያድር ነበር›› በማለት ደብረ ዘይት ጌታችን ያድርበት እንደ ነበር ይገልጻል፡፡ የሚገርመው ጌታችን በደብረ ዘይት የሚያድረው መጠለያ ኖሮት ሳይሆን ተራራውን እንደ ቤት ተጠልሎ ነው፡፡

ቅዱስ ማቴዎስ ስለ ጌታችን ለፍርድ መምጣት እና ስለ ዓለም ፍጻሜ በወንጌሉ በምዕራፍ 24÷3 ጀምሮ አንዲህ በማለት ጽፎልናል፡፡ አንድ ቀን የጌታ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው፦ ንገረን ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድን ነው? አሉት፡፡ ጌታችን መልሶ እንዲህ አላቸው ይለናል፡፡ ‹‹ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ፡፡ ብዙዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ›› አላቸው፡፡ ይህ ጌታችን የተናገረውን ሐዋርያት እንዲሰሙት እኛ ደግሞ እንድንጠነቀቅበት ነው የነገራቸው፡፡

ዛሬ ከወደ ምዕራባውያን ክርስቶስ ነን በማለት የተነሱትን በዘመናችን አይተናል፡፡ በመቀጠል ‹‹ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነው፡፡ ብሎ መደንገጥ እንደሌለባቸው ተናግራል፡፡ ይህም በዘመናችን ተፈጽሞ አይተናል እያየንም ነው፡፡ ‹‹ህዝብ በህዝብ ላይ መንግስትም በመንግስትም ላይ ይነሳል›› ብሎም ነገራቸው፡፡ ይህም በዘመናችን ተፈጽሟል፡፡

አንዱ ህዝብ በአንዱ ላይ በተለያየ ምክንያት እየተነሳ አገራዊ ቅርጽ እየያዛ አፋጅቷል እያፋጀም ነው፡፡ ‹‹ረሃብ፣ ቸነፈር፣ የምድር መናወጥ በተለያየ ስፍራ ይከሰታል›› ያለው በዘመናችን ብዙ አሳይቶን ምስክር አድርጎናል፡፡ ዛሬ እኛ ሰዎች ከእህል ረሃብ እስከ ፍቅር ረሃብ እየተሰቃየን እንገኛለን፡፡ የምድር መናወጡም ለብዙ አገራት ስጋት እና ለዜጎች ድንገተኛ ሞት እና ለንብረት መጥፋት ምክንያት እየሆነ ነው፡፡

በተለይ ‹‹ብዙ ሐሰተኛ ነብያትም ይነሳሉ ብዙዎችንም ያስታሉ›› ያለው ዛሬ አንዳንዶች ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ያለ መንፈስ ቅዱስ ሿሚነት፤ በራሳቸው ስጋዊ ፍላጎት፤ ‹ነብይ› ነን በማለት ለብዙዎቹ የመሰናከያ ዓለት በመሆን ላይ ይገኛሉ፡፡

ጌታም የህግ ሁሉ ፍጻሜ የሆነችው ፍቅር ከአመጻ ብዛት የተነሳ እንደምትቀዘቅዝ ነገራቸው፡፡ ዛሬ ፍቅር ማደርያዋ ከሆነው ከአባቶች፤ ከመንፈሳዊ ሰዎች ልብ ወጥታ ትንገላታለች፡፡ ከክፋታችን የተነሳ ፍቅር ማረፍያ አጣች፡፡ የሚገርመው ‹‹ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፣ በዚያን ጊዜ መጨረሻው ይመጣል›› አላቸው፡፡ ይኸው ወንጌል አልሰማንም ብለን እንዳንክድ ለፍርድ እንዲመች በየቤታችን በተለያየ ምክንያት ይሰበካል፡፡

ጌታችን ለቅዱሳን ሐዋርያት ከዛሬ ሁለት ሺ ዓመት በፊት በትንቢት መልክ የነገራቸው ዛሬ ሁሉም ተፈጽሟል፡፡ ‹‹በዚያን ጊዜ መጨረሻው ይመጣል›› እንዳለ ጌታችን ይመጣል፡፡ ግን ‹‹ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፣ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና›› በማለት መምጫውን በመንፈሳዊ ዝግጅት እንድንጠባበቅና ስለ ዳግም ምጽአቱ አስተምሮናል፡፡
401 views03:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 02:04:47

597 views23:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 20:48:03

1.1K views17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 06:45:29
1.8K views03:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 06:45:25 ጌታችን በዘር ዘሪው ምሳሌ በሚያስተምርበት ጊዜ "ጠላት መጣና በስንዴው መካከል እንክርዳድ ዘርቶ ሄዴ" ብሏል። /ማቴ 13፥25/
ወዳጄ ፍሬ ከሌለህ እንክርዳድ ትሆናለህ። እንክርዳድ ደግሞ ፍሬውን ያበላሻል። ዛሬ እኛ አገልጋዮች እንክርዳድ ሆነን ምዕመናኑ ባለ ብዙ ፍሬዎች ሆነዋል። የእኛም እንክርዳድነት የምዕመናኑም ፍሬያማነት እየታየ ነው። ጠላት በስንዴው መሃል እንክርዳድ እንደዘራበት፣ ስንቶች ጠላት ሆነው፣ ፍሬ የሌላቸው እንክርዳድ የሞላባቸው ስለሆኑ በምዕመናኑ መሃል እንክርዳድ ይዘራሉ። ፍሬውን መዝራት እየቻሉ እንክርዳዱን ይዘራሉ። በዚህም የሰይጣን ጠበቃ ይሆናሉ።

ምዕመናኑ ስለ ክፉ መናፍስት ሴራ አውቀው፣ በአምልኮት ሕይወት ታግለው ሲላቀቁ፣ የእኛዎቹ አንዳንድ አገልጋዮች ምንም ሳያውቁ ሳይነቁ ይኖራሉ። እስከ መቼ እናንተ እስኪገባችሁ ምዕመናኑን ግራ ታጋባላችሁ? እናንተ ሳታውቁ ምዕመናኑ ስለነቁ፣ ስላወቁ በፈውስ መንገዳቸው ላይ የመንገድ ላይ ሰይጣን አትሁኑባቸው።

ጌታችን ሰይጣንን "ተቃወሙ" ነበር ያለን። ምነው እናንተ ሰይጣንን መቃወም ትታችሁ በግልጽ ደገፋችሁ? የሰይጣን ማህበርተኞች ወይም የምስጢር ማህበራት አባል ይመስል ሰይጣን ተነካ ብላችሁ ለሰይጣን ጠበቃ መሆናችሁ ሰይጣንም ሰይታዘባችሁ አይቀርም። አንድ ካህን ሰባት አጋንንት እንዲያወጣ ስልጣን ተሰጥቶታል።

ሰባት አጋንንት የተባሉት መግደላዊት ማርያም ላይ ያሉት ሰባት ዓይነት አጋንንት ማለት ነው። እነሱም የትዕቢት መንፈስ፣ የስድብ መንፈስ/መንፈሰ ጽርፈት/፣ የቅንአት መንፈስ፣ የትዝውፍት መንፈስ/የምንዝር ጌጥ:- እላፊ የሚያጋጌጥ/፣ የዝሙት መንፈስ፣ የሐሜት መንፈስ፣ የሐሰት መንፈስ ናቸው። ታዲያ ከእነዚህ በአንዱ የማይፈተን የማይሰቃይ አለ? እነዚህና ሌሎች ከሰው ሕይወት እንዲለቁ እና እንዲርቁ ማድረግ እየቻላችሁ ለሰይጣን ጠበቃ መሆናችሁ ያሳፍራል።

ምዕመናኑ እየተቸገረ ያለው በአንዳንድ አገልጋዮች፤ በአንድ እጃቸው መስቀል በአንድ እጃቸው ቅጠል በያዙት ነው። ከቻላችሁ በምዕመናኑ ያደሩትን፣ ሳያውቁት አብረዋቸው የኖሩትን፣ በቤተሰብ በኩል የመጡትን፣ በዕድላቸው የገቡትን ክፉ መናፍስት አስወጡ። ካልቻላችሁ አርፋችሁ ተቀመጡ፣ በእውነት አትችሉም እንጂ ብትችሉ መተተኞችን ደብተራዎችን አጋልጡ። ደርሶ የሰይጣን ጠበቆች አትሁኑ። ሰይጣን ከሰው ለምን ወጣ ስትሉ፣ ሰይጣን እራሱ ገርሞት "አሽቃባጮች" ሳይላችሁ ይቀራል።

"እነዚህ ደግሞ አእምሮአቸው የጠፋባቸው ስለ እምነትም የተጣሉ ሰዎች ሆነው፣ እውነትን ይቃወማሉ" 2ኛ ጢሞ 3፥8

መጋቢት 8-7-15 ዓ.ም

ካሊፎርኒያ አሜሪካ
2.1K views03:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 06:45:25 #_የሰይጣን_ጠበቆች_አታርፉም_አታፍሩም!

#_የመንገድ_ዳር_ሰይጣኖች!

ሰይጣን ከሰው ለምን ወጣ ብላችሁ ሰይጣናዊ ሰልፍ እንውጣ ትላላችሁ?

እሳቸውን ለመቃወም ፊርማ እንዳሰባሰባችሁ መተተኛ ደብተራዎችንም ለመቃወም ፊርማ አሰባስቡ!

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ!

ተወዳጆች ሆይ ክቡር አባታችን መላከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ በአሜሪካ አትላንታ March 24-25 እና 26 ለሦሰት ቀን የሚቆይ ታላቅ ጉባኤ አላቸው። በጉባኤው ላይ እኔም እንድገኝና አብረን ምዕመናኑን እንድናገለግል ጋብዘውኝ ነበር። ነገር ግን እኔ በካሊፎርኒያው አገልግሎት ምክንያት አትላንታ ሄጄ ማገልገል አልቻልኩም። እጅግ በጣም የሚገርመው የእሳቸውን ጉባኤ ለማደናቀፍ፣ በመተት ወዘተ የተያዙት እንዳይድኑ የመንገድ ዳር ሰይጣኖች ብዙ መልፋታቸውን ሰምቼ አዘንኩ በእነሱም አፈርኩ።

ወዳጆቼ ሰይጣን ለምን ከሰው ወጣ ብለው ለሰይጣን ጠበቃ የሚቆምበት አሳፋሪ ዘመን ላይ ደርሰናል። ክፉ መንፈስ ከሰው ለምን ወጣ የሚሉ የመንገድ ላይ ሰይጣኖች ብዙ አሉ። ትዝ ይላቹኃል አባታችን አብረሃምን ሲፈትነው የነበረው የመንገድ ላይ ሰይጣን ነው።

ወደ አብርሃም ቤት ሰዎች ሄደው የአብርሃምን የእንግዳ ተቀባይነቱን በረከት እንዳይቀበሉ፣ በአብርሃም ቤት እንዳይበሉ፤ ሰይጣን መንገድ ላይ ተቀምጦ፣ እራሱን በምትሃት ለውጦ፣ ጭንቅላቱ የተፈረከሰ፣ ደሙ የፈሰሰ ሰው መስሎ "ወደ አብርሃም ቤት አትሂዱ ይኸው አብርሃም እንግዳ ከመጥላቱ የተነሳ መሃል እራሴን ፈንክቶኝ፣ ደሜን አፍስሶኝ" እያለ ሰዎች ወደ አብርሃም ቤት ለበረከት እንዳይሄዱ ይከላከል ነበር።

ዛሬም የመንገድ ዳር ሰይጣኖች አሉ። ዳር ይዘው በሰዎች የድኅነት መንገድ ላይ ቆመው አትሂዱ፣ አትጠመቁ፣ ቅብዓ ቅዱስ አትቀቡ የሚሉ ብዙ የመንገድ ዳር ሰይጣኖች አሉ። ሰይጣን ወደ አብረሃም አይቀርብም። መንገድ ዳር ቆሞ የመከላከል ሥራን ብቻ ይሠራል። አሁን ያሉትም የመንገድ ዳር ሰይጣኖች ወደ ምዕመናኑ ቀርበው "ችግራችሁ ምንድን ነው? ፈተናችሁ ምንድን ነው? ምንድነው የሚያስቸግራችሁ? ምንድን ነው የሚያሰቃያችሁ ወተዘ" ብለው አጠይቁም መንገድ ዳር ቆመው ይቃወማሉ በሰው ቁስል እንጨት ይሰዳሉ።

ሰዎች ወደ አብረሃም ቤት ሲሄዱ መንገድ ዳር ቆሞ አትሂዱ እያለ የሚከላከለው ሰይጣን አብርሃም የሚሠራውን ሥራ ስለማይሠራ ይቃወማል። "አብርሃም ክፉ ነው፣ ደግ አይደለም፣ አጥፊ ነው፣ ገዳይ ነው" እያለ ለሰዎች እንቅፋት ይሆናል። ዛሬም የታመመውን አያጠምቁ፣ ቅብዓ ቅዱስ አይቀቡ፣ በክፉ መናፍስት ተይዘው የሚሰቃዩትን አያገለግሉ፤ በሰዎች ሕመም፣ ስቃይ እና ችግር ፈተና ይሆናሉ፣ በቁስላቸውም እንጨት ይሰዳሉ። የመንገድ ላይ ሰይጣን እጅጉን ክፉ ነው። ምክንያቱም እውነትን ሐሰት አድርጎ ስለሚያቀርብና በሐሰት ስለሚከስ ነው።

ወዳጆቼ በሰይጣን ጥበብ፣ በመተት ትልቅ ቦታ የደረሰ፣ የሰይጣንን ውለታ የተቋደሰ ሰው ሰይጣን ሲነካ ደስ አይለውም። ሰይጣን ከሰዎች ሲወጣ ነፍሳችን ካልወጣ የሚሉት ወደው አይደለም። አፍንጫ ሲመታ ዓይን ያለቅሳል የሚባለው ትክልክል ነው። የሰው ሲለቅ የእናንተም ስለሚጨነቅ ስለሚሳቀቅ ነው።

ቆይ ሰው እንዴት የሰይጣን ጠበቃ ይሆናል? ሰይጣን ከሰው ለምን ወጣ የሚሉት እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ በአንድም በሌላም የሰይጣን ውለታ አለባቸው። ለዜማ፣ ለቅኔ፣ ለድምጽ፣ ለመጻሕፍት እውቀት፣ ለግርማ ሞገስ፣ አቃቤ ርዕስ/ለመጠበቂያ/ ወዘተ እያሉ ያስገቡት ቢቃወሙ አይደንቅም።

ግብረ ሰዶማዊነት፣ ሌዝቢያንነት በሕግ በተፈቀደበት ሀገር፣ የሰይጣን ቸርች ባለበት ሀገር፣ መላከ መንክራት መምህር ግርማ ወንድሙ በአትላንታ እንዴት ያገለግላሉ ብላችሁ ፊርማ ከምታሰባስቡ "ግብረ ሰዶም፣ ሌዝቢያንነት ይቁም" ብላችሁ ፊርማ አሰባስባችሁ ለምን አትቃወሙም? የሚደርስባችሁን ስለምታውቁ ዝም ጭጭ ትላላችሁ።

ከኢትዮጲያ ዘፋኝ መጥቶ ኮንሰርት ሲያዘጋጅ፣ ሰዉን ዳንኪራ ሲያስመታ "ዘፋኝነት ኃጢአት ነው፣ መጽሐፍ ቅዱስም ይከለክላል ስለዚህ የእከሌ ኮንተሰርት ላይ አትገኙ" ብላችሁ ለምን አትቃወሙም? ደብተራና ዘፋኝ እንደልብ በሚፏልልበት ሀገር አገልጋይ መጣ ብላችሁ መጮኃችሁ ያሳፍራል። ደብተራና ዘፋኝን ለመቃወም በነካ እጃችሁ ፊርማ ብታሰባስቡ መልካም ነበር።

አባታችን የሚያገለግሉበትን ቦታ ለማዘጋት ለማስከልከል የዘፋኞችንም አዳራሽ፣ የሰይጣንን ቸርች ለማዘጋት ለምን ተሰባስባችሁ ፊርማ አታሰባስቡም? ምነው በቤተ ክርስቲያን የተሰገሰጉትን፣ ትውልድ አማካኞችን፣ የሰው ዕድል ሰላቢዎችን፣ አውደ ነገሥት ገላጮችን፣ ሟርተኞችን፣ አጋንንት ጎታቾችን፣ መተት መታቾችን፣ በጥላ ወጊ ሰው ገዳዮችን ለመቃወም ፊርማ ብታሰባስቡ?

ክፉ መንፈስ ከሰው ሲወጣ የምትቃወሙት ደህና ነገር የወጣ መስሏችሁ ነው? የወጣውኮ ደህና ነገር አይደለም። በተለይ እኔ የታዘብኩት እዚህ አሜሪካ ያሉት የሰይጣን ጠበቆች ይገርማሉ። ሰይጣን በገሃድ በሚመለክበት፣ የሰይጣን ቸርች ባለበት፣ ለሰይጣን ባፎሜት ተብሎ ሐውልት በቆመበት ሀገር ሰይጣን የለም ይላሉ። የእኛዎቹ አገልጋይ ተብዬዎቹ ሰይጣን የለም ሲሉ ሰይጣን የሚስቅባቸው ነው የሚመስለኝ። እሱ አለሁ ይላል እነሱ የለም ይሉታል። እሱ ሰው ላይ እየጮኸ ይወጣል እነሱ ለምን ወጣ ብለው ከእሱ በባሰ ይጮሁለታል።

እኔ የሚገርመኝ ሰይጣን ከሰው ለምን ወጣ ብላችሁ እርር ምርር የምትሉት ሰይጣን እንኳን እንደናንተ ከሰው ሲወጣ አልተማረረም። ሰይጣን "ትላንት ከገነት አስወጥቻቸው ዛሬ ከሰው ሲያስወጡኝ፣ ከሰው ለምን ወጣህ የሚሉኝ እነዚህ ከእኔ ወገን ናቸው እንዴ?" እያለ ግራ የሚጋባ ነው የሚመስለኝ። ሰይጣን ከሰው ለምን ወጣ ብላችሁ ተባብራችሁ ስትጮሁ፤ ከሰው የሚወጣው ሰይጣን እንኳን እንደናንተ አይጮህም። ሰይጣን ከሰው ውጣ ሲባል በሰከንድ ጮሆ ይወጣል። እናንተ ደግሞ ሰይጣን ከሰው ለምን ወጣ ብላችሁ ሦስት ሰዓትና ከዛ በላይ በሚዲያ ትጮኃላችሁ። ጉድ እኮ ነው! እባካችሁ የምዕመናኑ የነፍስ ጠበቃ እንጂ የሰይጣን ጠበቃ አትሁኑ!

በጣም የሚገርመው አሜሪካ ከአንድም ሁለት ሥራ እየሠሩ ጠብ የማይልላቸው፣ አመድ አፋሽ የሆኑ በልፋት ብቻ የሚኖሩ እልፍ አሉ። ሠርተው ሳይሆን እጅጉን ለፍተው፣ ደም ተፍተው ገንዘብ ያገኛሉ። ገንዘባቸው ግን የት እንደሚገባ፣ የት እንደሚደርስ አያውቁም። ገንዘቡ እጃቸው ይገባል ሳያውቁት እጥፍ ሆኖ ይወጣል። እነዚህ ሰዎች እኮ በሰላቢ መተት የሚሰቃዩ ናቸው። ለፍተው ለሰው፣ ሠርተው ለሰው! እነሱ ከአንድም ሁለት ሥራ ይሠራሉ ሌሎቹ አንድም ሥራ ሳይሠሩ የእነሱን እየሰለቡ ይኖራሉ። ደግሞኮ የሚገርመው ደብተራው ያለው እዚሁ አሜሪካ መሆኑ ነው!

እውነት እናውራ ከተባለ በአሜሪካ በአውሮፖ የሰው ዕድል ለሰው የሚሰጡ፣ የሚለውጡ፣ የሚሸጡ ሀገር የፈቱ፣ ትዳር ያፋቱ፣ ሰውን በመተት ያንገላቱ፣ ቤተሰብን የበተኑ፣ የሰውን መልካም ዕድል ያመከኑ የሉም? መጽሐፍ ቅዱስ "የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ" ይላል እናንተ ደግሞ ከመቃወም ትደግፋላችሁ። ከመደገፍም አልፋችሁ ለዲያብሎስ ጠበቃ ትሆናላችሁ። /ኤፌ 6፥11/
2.0K views03:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 23:44:40

269 views20:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 07:06:52
307 views04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 07:05:58 በአባቶች በካህናት መሳዮች የመጣብህ ፈተና ደጋግና ለነፍሳቸውም ለአገራቸውም በጸሎት የሚኖሩትን ካህናት ሊያሳጣህ ይችላል። መነኮሳት ባህታውያን ነን በሚሉት የሚመጣብህ ፈተና እውነተኞቹን መናንያን ሊያሳጣህ ይችላል። መንፈሳዊ ነን፣ የቤተ ክርስትያን ሰዎች ነን በሚሉት ሰዎች የሚመጣብህ ፈተና ንጹህ አገልጋዮችን ሊያሳጣህ ይችልል።

በሰው የመጣ ፈተና መላቀቂያው ከባድ ነው፡፡ ዛሬ በየቤቱ በሰው የመጣ ፈተናና መከራ የስንቱን ቤተሰብ ሰላሚዊ ሕይወት አናውጧል በትኗል፡፡ የሰው መከራ የተጫናቸው፣ የሰይጣን ፈተና የበዛባቸው በሺህ የሚቆጠሩ ምእመናን በየገዳሙ ይንከራተታሉ፡፡ አንድ አባት አንድ ልጅን ‹‹ልጄ ጀርባህ ላይ ሰው ከሚጫንህና ግንድ ከሚጫንህ የትኛው ይሻልኃል?›› አሉት፡፡ ልጁም ብልህ ኖሮ ‹‹አይ አባቴ ጀርባዬ ላይ ግንድ ቢጫነኝ ሰው ያወርድልኛል፡፡ ሰው ከተጫነኝ ማን ያወርድልኛል?›› አላቸው ይባላል፡፡

ዛሬም በሕይወታቸው ጀርባ ሰው ተጭኗቸው የሚኖሩ፣ አውርድልኝ እያሉ ፈጣሪ ላይ የሚያማርሩ ብዙ አሉ፡፡ ‹‹አቤቱ እዘንልኝ፣ ጠላቶቼም የሚያመጡብኝን መከራ እይ›› እያልክ ጸልይ፡፡ መዝ 9፥13 ደግሞም ጽድቁን በመፈለግ ስትለፋ፣ የመከራ ድንበርህ እየሰፋ ይሄዳል፡፡ ከሚታየው ሰው እስከ ማይታየው ሰይጣን በነገሮች ሁሉ ያብሩብኃል። ግን እንዲህ ተብለኃል ‹‹የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፡፡ እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል›› መዝ 34፥19

ቀዳሜ ሰማዕት ወጣቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ ያንን ሁሉ የድንጋይ ናዳ፣ የመከራ ዱብ እዳ ሲቀበል፤ቀድሞ ለአይሁድ ሕግ ቀናተኛ ሆኖ አሳዳጅ የነበረ፣ ኋላ ሐዋርያ ሆኖ ስለ ክርስቶስ ተሰዳጅ የሆነው ቅዱስ ጳውሎስ፤ በእስጢፋኖስ ሞት የገዳዮችን ልብስ በመጠበቅ ተባብሯል፡፡ ይህንንም እራሱ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ በማለት በጸጸት ምስክርነቱን ሰጥቷል፡፡ "የሰማዕትነትህንም የእስጢፋኖስን ደም ባፈሰሱ ጊዜ፣ራሴ ደግሞ በአጠገባቸው ስቆም ተስማምቼ የገዳዮችን ልብስ እጠብቅ ነበር"ብሏል፡፡ የሐዋ 22፥20

ስለዚህ ቅዱስ ጳውሎስ ለቅዱስ እስጢፋኖስ መፈተኛ ብቻ ሳይሆን ክብር ማግኛ ነበር። አንተም ነፍስህን የሚሿት ስለሚበዙ ከክርስቶስ ጋር ለመኖር በራስ ሰው መከራ መቀበል እንዳለ አትዘንጋ፡፡ መዝ 38፥12

"በግፍ መከራን የሚቀበል ሰው እግዚአብሔርን እያሰበ ኃዘንን ቢታገስ ምስጋና ይገባዋል" 1ጴጥ 2÷19

‹‹ከክርስቶስ ጋር እንዴት እንኑር?›› ከሚለው መጽሐፌ የተወሰደ፡፡

መጋቢት 6-7-15 ዓ.ም

ካሊፎርኒያ አሜሪካ
311 views04:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 07:05:58 #_መከራን_በራስ_ሰው_መቀበል!

#_በመተት_ወዘተ_የምትሰቃዩ_በጥሞና_አንብቡት!

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ!

ተወዳጆች ሆይ በመንፈሳዊ ሕይወት እና በሥጋዊ/በዓለማዊ/ ሕይወት ስኬቶቻችን ከሰይጣን ባልተናነሰ ሁኔታ የራሳችን ሰዎች እንቅፋት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ብዙዎቻችን ፈተናና መከራን የምንቀበለው ክብርም የምናገኘው በሰይጣን ብቻ ተፈትነን ይመስለናል። ነገሩ ግን ወዲህ ነው፡፡ ወዳጄ ከሰይጣን ባልተናነሰ ምናልባትም በባሰ መልኩ በራሳችን ሰዎች/የሰው የራስ ባይኖረውም/ መከራን ልንቀበል እንችላለን፡፡

በራሳችን ሰው መከራን መቀበል ክብር የሚያሰጥ ስለማይመስለን ፈታኞቻችንን እንደ ሰይጣን ከመታገስ ይልቅ ባደረሱብን መከራ ልክ ከፈጣሪ ፍርድ እንጠብቅባቸዋለን፡፡ ለዚህም ነው የበዳዮቻችንን ጉዳይ ፈጣሪ ፊት ይዘን በጸሎት ቆመን ‹‹እንደህ ሲያደርገኝ እንዴት ዝም ትላለህ፣ ፍረድልኝ፣ ፍረድበት፣ የእሱን/የእሷን መጨረሻ ካላሳየኸኝ የለህም…›› እያልን የምናማርረው በራሳችን ሰዎች መከራ ተቀብለን ክብር ማግኘታችንን ስለማናውቅ ነው፡፡

ወዳጄ ጌታ እራሱ ለልዩ አገልግሎት በመረጠው የእኔ ባለው በይሁዳ አይደል እንደ ዕቃ የተሸጠው? ለመከራ ተላልፎ የተሰጠው? እስኪ አንዱ ለአንዱ ክብርና መከራ እንደሆነ ወደ ገድሉ ይዤህ ጎራ ልበል፡፡ ታላቁ ጻድቅ አቡነ ተክለ ሐዋርያት የሰማዕትነትን መከራ ይቀበሉ ዘንድ ጌታችንንና እመቤታችንን ለምነው ነበር፡፡

ታዲያ አንድ እሁድ ቀን እኚህ አባት ቆመው ጸሎት ሲያደርጉ እመቤታችን በብርሃን ሠረገላ ተጭና መላእክትን አስከትላ መጥታ ‹‹የጳውሎስ አበባ፣ የጴጥሮስ ፍሬ የልጄ ተክል ወዳጄ ተክለ ሐዋርያት ሰላምታ ላንተ ይገባኃል፡፡ እነሆ የተመኘኸውን ታገኘዋለህ ጊዜው ቀርቧልና በርታ ጽና›› ብላው ተሰወረችው።

አባታችን አቡነ ተክለ ሐዋርያትም ምኞታቸው ስለ ፈጣሪያቸው ብለው በሥጋ መከራ መቀበል ነበር፡፡ የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ባለቤት የገላውድዮስ እናት ከለላ የምትባል አባታችንን ‹‹ስለ ክርስቶስ አስተምረኝ ስለ ኃጢአቴም ምከረኝ›› ብላ መልዕክት ላከችባቸው፡፡ እሳቸውም መጥተው የሚገባትን ነገር ሁሉ አስተምረው ንስሐም ሰጥተው አረጋጓት፡፡ ልጇን ገላውድዮስንም የመጻሕፍትንም ምስጢር አስተማሩት፡፡

በመጨረሻም ወደ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ቤት ገቡ፡፡ ንጉሡም ሥራቸውን ሁሉ ጠይቆ ማረፊያ ሰጣቸው፡፡ በዚያም ሦስት ወር ተቀመጡ፡፡ የመስቀል ክብረ በዓል ቀን የንጉሡ ወታደሮች በፈረስ ግልቢያ ሲጫወቱ፣ በድንጋይና በእንጨት፣ በአጥንት እየተመታቱ፣ ብዙዎቹም ሲሞቱ አቡነ ተክለ ሐዋርያት ተመለከቱ፡፡ ሁኔታውንም የአረመኔ ሥራ ነው ብለው ተቃወሙ፡፡

አቡነ ተክለ ሐዋርያትም አንድ ብርቱ ጉይ አለኝ ብለው ወደ ንጉሡ ገቡ፡፡ ንጉሡንም ሳይፈሩ ስለተደረገው ግፍ፣ በከንቱ ስለሚጠፋው ሕይወትም ተናገሯቸው፡፡ ንጉሡም እንዴት ደፍረው ተናገሩኝ፣አሻፈረኝ ብሎ ያለጥፋታቸው አቡነ ተክለ ሐዋርያትን ደማቸው በአፍና በአፍንጫቸው እስኪፈስ አስደበደባቸው፡፡ ይህ አልበቃ ብሎ በብርቱ ወታደሮች ዳግም አስደብድቦ አስገረፋቸው፤በእስር ቤትም አኖሯቸው፡፡ በእስር ቤትም ስምንት ወር በመከራ ተቀመጡ፡፡

አባታችን አቡነ ተክለ ሐዋርያትም በዚህ ጽኑ መከራ እስር ቤት ውስጥ እያሉ እመቤታችን ተገልጻላቸው ‹‹እነሆ የልጄን ትዕዛዝ ፈጸምህ የተመኘኸውን አገኘህ ሌላ የትዕግስት በር ይቀርኃል›› ብላ ተሰወረቻቸው፡፡ አባታችንም በመማረር "እመቤቴ ሰማዕትነትን ስጭኝ ያልኩሽ በክርስቲያናዊ እጅ ነውን" እንዳሉ ገድላቸው ይናገራል፡፡ /ገድለ አቡነ ተክለ ሐዋርያት ገጽ 74-76 ይመልከቱ/

ወዳጄ ፈተናና መከራን በራስህ ሰው፣ በቤተሰብህ፣ የቅርቤ በምትላቸው ሰዎች ሊመጣብህ ይችላል፡፡ ምናልባትም በእነዛ ሰዎች ግፍን መቀበልህ ደም አልባ ሰማዕት ሊያሰኝህ ይችላል፡፡ አየህ አቡነ ተክለ ሐዋርያት ስመ ጥር ጻድቅ ናቸው፡፡ አፄ ዘርዓ ያዕቆብም የእመቤታችን ልዩ ወዳጅ ናቸው፡፡ እነዚህን ሰዎች ስትመለከት አንዱ ለአንዱ መከራ አንዱ ለአንዱ ክብር ነበሩ፡፡

አቡነ ተክለ ሐዋርያት ሰማዕትነትን የሥጋ መከራን ከአረመኔዎች ከአሕዛቦች እቀበላለው ብለው ቢያስቡም ክርስቲያን ከሆነ፣ለዛውም የእግዚአብሔር ወዳጅ ከሆነ ሰው ከአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ተቀብለዋል፡፡

መከራና ፈተና ከማንምና በየትም ይምጣ ዋናው ታግሶ ማለፍና ክብሩን መቀበል ነው፡፡ ስለዚህ እንዴት በቤተሰቤ? በዙሪያዬ ባሉ የኔ ባልኳቸው ሰዎች ግፍ ይደርስብኛል? እንዴት መከራ እቀበላለሁ? እንዴት መተት ይመተትብኛል? እንዴት ይመትቱብኛል? አትበል፡፡

በተለይ መርሳት የሌለብህ ሰይጣንም አንተን ለመፈተን ከአንተ ሰው የበለጠ የሚቀለው የለም፡፡ ሰይጣን አንተ ላይ የመከራ ድንጋይ ለመጫን ተሸካሚ ከሌላ ቦታ የማታውቀውን ሰው አያመጣም፡፡ የሰይጣን ፈተና እሾህን በእሾህ ነው፡፡ ይልቁንም ሰይጣን አንተን በፈተና ለማንገላታት፣ በመከራ አፈር ከድሜ ለማብላት ያንተ ሰው ይቀለዋል፡፡

በአቡነ ተክለ ሐዋርያትም የሆነው ይኸው ነው፡፡ አንተም ቤተሰብህ ሊበድልህ፣ ጓደኛህ መከራ ሊያደርስብህ፣ ያመንከው ሊከዳህ ይችላል፡፡ በራስህ ሰው ገንዘብህን፣ ትዳርህን፣ሥራህን፣ ዕድልህን፣ መልካም አጋጣሚህን ልታጣ ትችላለህ፡፡ አንዳንዴም እነሱ አንተ ላይ አሲረው ካንተ በወሰዱት ነገር ሲለወጡ፣ አንተ ከድጡ ወደ ማጡ ልትሆን ትችላለህ፡፡

ባል ለሚስት ሚስት ለባል የሕይወት አጋር ብቻ ሳትሆኑ መፈተኛም ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ በቀናተኛ ባል እና ሚስት ፍቅር ይፈተናል፡፡ በተናጋሪ ሚስት ትዕግስትህ ይፈተናል፡፡ በቁጡ ባል ትህትናሽ ሊፈተን ይችላል፡፡ በአኩራፊ ሚስት ተለማማጭነትህ ሊፈተን ይችላል፡፡ በነጭናጫ ባል ከሚስትነትህ ባለፈ እንደ እናት ልትፈተኚ ትችያለሽ ወዘተ… በዚህ ሂደት ነገሮችን ሁሉ በማስተዋል በትዕግስት ማለፍ ትዳርን ከመታደግ፣ዕድሜውን ከማርዘምም ባሻገር መከራን በመቀበላችሁ በእግዚአብሔር ዘንድ ክብር ታገኛላችሁ፡፡

ወዳጄ በሕይወትህ የመከራ እንጀራ እንድትበላ፣ በሕይወትህ እንድትጉላላ ያደረጉህን ሰዎች እዘንላቸው፡፡ ሰይጣን አንተን ለመጉዳት እነሱን መሣሪያ አድርጎ መጠቀሙ፤ የራስህን ሰው ሥጋ ለብሶ፣ እነሱን መስሎ ፊት ለፊት ስለተዋጋህ ጸልይላቸው፡፡

አንዳንዴ መከራውን መሸከም እስኪከብድህ ድረስ ልትሰቃይ ትችላለህ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ስለ ሕይወታችን እንኳ ተስፋ እስክንቆርጥ ድረስ ከአቅማችን በላይ ያለ ልክ ከብዶብን ነበር›› በማለት በሰይጣንና በሰው የመጣው መከራ ሐዋርያውን እንዴት እንደከበደው ጽፎልናል፡፡ 2ኛ ቆሮ 1፥8

አንተ መከራ ባደረሱብህ ሰዎች መከራ ተጭኖህ በስቃይ ስትኖር፣ መከራ የሚያደርሱብህ ሰዎች በሥጋ ምቾት ሲኖሩ ስታይ፤ እግዚአብሔር ያለ ፍርድ በዝምታ የተባበረብህ አድርገህ እንዳታስብ፡፡ ለጊዜው አንተ እየተጎዳህ እነርሱ የተሻለውን ሲሆኑ ብታይ በጊዜው ጊዜ የዘሩትን ያጭዳሉ፡፡ ‹‹መከራን የሚዘሩ ይህንኑ ያጭዳሉ›› ተብሏልና፡፡ ኢዮ 4፥1

በአሁን ጊዜ ሰይጣን ለሰው ፈተና ከሆነው ባልተናነሰ መልኩ ሰው ለሰው ፈተና እየሆነ ነው፡፡ ክርስቲያን ነኝ የሚሉት ክርስትናህን እንዳትኖር ሊያደርጉህ ይችላሉ፡፡ ቆራቢ ነኝ የሚሉት በእነሱ የመጣ ፈተና እንዳትቆርብ ሊያደርጉህ ይችላሉ፡፡ ጻድቅ ነኝ የሚሉት ሰዎች በእነሱ የመጣ ፈተና ትንሿ ጽድቅህን ሊያሳጡህ ይችላሉ፡፡
313 views04:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ