Get Mystery Box with random crypto!

#ስንት_ይሁዳ_እያለላችሁ_እኔን_ለምን_በየዓመቱ_ትወግራላችሁ? /በምናብ የሳልኩት፣ የይሁዳ የሲኦል | ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

#ስንት_ይሁዳ_እያለላችሁ_እኔን_ለምን_በየዓመቱ_ትወግራላችሁ?

/በምናብ የሳልኩት፣ የይሁዳ የሲኦል ብሶት/

የዛሬ አምስት ዓመት የተጻፈ!

የአራዳ ቋንቋ የተጠቀምኩት አራዳ ልሁን ያለውን ይሁዳን እያሰብኩት ነው። ስለ ቋንቋው ይቅርታ! እንድትማሩበት ነው።

ከመፍረዳችሁ በፊት በደንብ አንብቡት እራሳችሁን እዩበት!

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ይሁዳ ነኝ! እነሆ ጌታችሁ ከተሰቀለ ይቅርታ አሳልፌ ሰጥቼው፣ በማይረባ በሠላሳ ብር ሽጬው ተሰቅሎ ከሞተ ሁለት ሺ ምናምን ዓመት አለፈው፡፡ ከሲኦል እሳታማው ሰላምታዬ እኔ ካለሁበት ለመምጣት ተፍ ተፍ ለምትሉት ያልከበረ ሰላመ ቢስ ሰላምታዬ በየጭፈራ ቤቱ በዝሙት ለሚንገላቱ፤ በየጫትና ሐሺሽ ቤቱ ለሚጀዝቡ፤ በትዳርና በእጮኛቸው ላይ ለሚቀስጡ፣ እየዘሞቱ ለሚያላግጡ፤ ዛሬም እንደ እኔ ጌታቸውን በክህደት፣ በገንዘብ ወዘተ ለሚለውጡ ይድረሳችሁ ብያለሁ፡፡

አዳሜ ብልጣ ብልጥ እንደ እኔ በአቋራጭ ገነት ገባለሁ ብለሽ ያሰብሽ ሁላ ሳታስቢው እኔ ያለሁበት ሲኦል ከች ትያለሽ፡፡ ይቅርታ በሲኦል አፌ ስማቸውን መጥራት ስለከበደኝ ነው። እነዛ ጓደኞቼ ሐዋርያት ጌታቸውንና ጽድቁን ሲፈል፤ እኔ ሆዬ ጨላዋ ላይ ሳፈጥ ይኸው በሳጥናኤል ስደፈጠጥ እኖራለሁ፡፡ የሚገርማችሁ ሐዋርያት የጌታቸውን ወንጌል ለመሸከም ሲጥሩ እኔ ደግሞ ሙዳየ ምጽዋትዋን ብቻ ስሸከም ይኸው እነሱ በገነት እኔ በሲኦል ገፈት እኖራለሁ፡፡

እየውላችሁ ስንት ሺ ዓመታት በሲኦል ሆኜ እያንዳንድሽን ስታዘብ ከርሜ ነበር፡፡ ዛሬ ግን ትዝብቴን ልተንፍሰው ብዬ ነው፡፡ ‹‹የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም›› አይደል የምትሉት፡፡ መቼም ካለሁበት ስቃይ ያ ገሃነመ እሳት እስኪከፈት የበለጠ አይመጣ፡፡

ዛሬ በሲኦል ሆኜ ፍርፍር ብዬ ስስቅ ነው የዋልኩት፡፡ ነገርዬው ምን መሰላችሁ! እናንተው ‹‹የእምዬን ወዳብዬ አይደል የምትሉት፡፡ የጌታችሁን መከራ ለማሰብ ያንን የመሰለ ሥርዓት ስታከናውኑ ውላችሁ ማምሻውን ‹‹ይሁዳ ወልዱ እምውሉደ ውሉዱ ይደምሰስ›› እያለችሁ ስንት ይሁዳን ስራችሁ አስቀምጣችሁ በስሜ ስትደበድቡኝ ስትረግሙኝ ነው ያሳቀኝ፡፡

ጋይስ እኔ አንዴ ጌታዬን ሽጬ፣ በሲኦል ተቀምጬ፣ የዛ የሲኦል አበጋዝ መጫወቻ ሆኛለሁ፡፡ ግን ስንቶች አሉ በቤተ ክርስትያን አገልጋይ ነን እያሉ ጌታቸውን በስውር ሽጠው የሚኖሩ፡፡ ስንት አሉ እኔን በመቋሚያ እየደበደቡ በጀርባ እየጠነቆሉ፣ ሙዳየ ምጽዋቱን እየገለበጡ፣ የድሆች ኪስ እየመጠመጡ እሚኖሩ፡፡ ስንት ሴቶች ወንዶች አሉ ክብራቸውን በገንዘብ እየሸጡ ጌታቸውን የሚያስቆጡ፡፡

ስንት አሉ ቅድስናቸውን እያረከሱ፣ በኃጢአት ባህር የሚንከላወሱ፡፡ ኸረ የናንተን ጉድ ዘርዝሬ አልጨርሰውም፡፡ ምንኩስናሽን ያፈረሽ፣ ክህነትሽ የጣልሽ ንስሐ ካልገባሽ በሲኦል የስቃይ ስፖንሰር የምሆናችሁ እኔ ነኝ፡፡ አዳሜ እኔ ወዳለሁበት ስትመጪ የኃጢአት ሒሳብሽን እንደ እኔ በስቃይ በመከራ ታወራርጃለሽ፡፡

ምን እንደምመኝ ታውቃላችሁ! ጌታችሁ እድሉን ቢሰጠኝ እኔን ‹‹ይሁዳና ዘር ዘሮቹ ይጥፉ›› የሚሉትን ነጭ ለባሽ ሁላ በያዙት መቋምያ እግር ከወርች እያልኩ ነርታቸው ነበር፡፡ ደግሞም ንስሐ ሳይገቡ በዓመት አንዴ ለስግደት የሚመጡትን፤ በሥራ እንደ እኔ እንደ ይሁዳ፤ በአለባበስ ግን ጸአዳ የመሰሉትን በመቋምያ እየሸከሸኩ ልክ አገባቸው ነበር፡፡ ምን ዋጋ አለው ሰውን የሚቀይረው ዱላ ሳይሆን ወንጌል በመሆኑ ነው፡፡

እንደው ግን ‹‹ይሁዳና ዘር ዘሮቹ ይጥፉ›› እያላችሁ ቤተ ክርትያን ውስጥ ያላችሁ በመቋሚያ፤ ውጭ ያላችሁ ደግሞ በድንጋይ ስትወግሩኝ ስትረግሙኝ ትንሽ ሼም አይዛችሁም፡፡ ፈጣሪያችሁ ፊት የማያቆም ሥራ ይዛችሁ፣ እንደ ድንጋይ የከበደ ኃጢአት ተሸክማችሁ፣ በየዓመቱ ስትወግሩኝ ስትደበድቡኝ ግርም ይለኛል፡፡ መቼም ጌታ ለእኔ የሰጠኝን ያልተጠቀምኩበትን የንስሐ እድል ለናንተም ስለማይነሳችሁ ነው እንደ ፈለጋችሁ የምትሆኑት፡፡

እስኪ አንዳንድ አዛኝ አንጓቾች፣ ሌሎቹም አጉል ፈራጆች ሁሌ ‹‹ይሁዳ እንዴት በሰላሳ ብር ጌታውን ይሸጣል? እንዴት የንስሐ እድሉን ያበላሻል? እንዴት እራሱን ያጠፋል? እንዴት የሐዋርያነት እድሉን ያበላሻል?›› ለምትሉ ገብስ ገብሱን እነግራቹኃለሁ፡፡

በመጀመርያ ‹‹ይሁዳ እንዴት ጌታውን በሰላሳ ብር ይሸጣል?›› ለምትሉ ስለ እውነት ከሆነ እኔ ጌታዬን መሸጥ አልፈልግም ነበር፡፡ ግን ምን ላድርግ ትንቢቱ ቀድሞ ለእኔ ተነገረ በእኔም ላይ ወደቀ፡፡ ቲንክ እያረጋችሁ ነው ወይስ እያሽሟጠጣችሁ? ኦኬ እኔ ጌታዬን ወድጄ ሳይሆን በትንቢት ተገድጄ እንደሸጥኩ ለእያንዳንድሽ መረጃ አቀርባለሁ፡፡ መቼም ዘመናችሁ የመረጃጃ ሳይሆን የመረጃ እንደሆነ ሲኦል ሆኜ መረጃ ይደርሰኛል፡፡

እስኪ ጌታዬን እንዴት እንደሸጥኩት ከመንገሬ በፊት ከማዙካ የሰማሁትን ልንገራችሁ፡፡ እኔ አስቀድሞ ‹‹አባቱን ይሰልባል፣ እናቱን ያገባል፣ ጌታውን ይሸጣል›› የሚል ትንቢት ነበረኝ፡፡ ታድያ ምን ሆነላችሁ! ያ መናጢ አባቴ ስሙን ሰይጣን ይጥራውና አንድ ዕንባቆም የተባለ ነብይና መምህር ነበር፡፡ አንድ ቀን ዕንባቆም የተባለው ሰው ሊያስተምር ሲሄድ በሚያልፍበት መንገድ ላይ ፋዙካ ድንጋይ ላይ ዱቅ ብሎላቹኃል፡፡

በአገራችን መምህር ክቡር ስለሆነ የፋዙካ ጀለሶች ነብዩ ዕንባቆምን ሲያዩት አክበረውት ተነሱለት፡፡ ፋዙካ በንቀት ይሁን በኩራት እግሩን አንፈራግጦ ተቀምጦ ነበር፡፡ ነብዩ የፋዙካ ጀለሶችን መርቆ፣ ፋዙካን ንቆ ላሽ አለ፡፡ ነብዩ አስተምሮ ማታ ላይ ሲመለስ አሁንም ፋዙካ ያችው ድንጋይ ላይ ዱቅ ብሏል፡፡

ነብዩንም ሲያየው ባላየ ብሎ መንጬ ሊል ብሎ በገገመኛ እዛው ዱቅ አለ፡፡ ነብዩም ‹‹ከዚህ ሰው የሚወለደው አባቱን ይሰልባል፤ እናቱን ያገባል፤ ጌታውን ይሸጣል›› ብሎ ትንቢት ተናገረበት፡፡ ፋዙካም በነብዩ ትንቢት ድንግጥ ሳይል ነብዩንም ይቅርታ ሳይጠይቅ እዛው ድንጋይ ላይ ዱቅ እንዳለ ቀረ፡፡

ፋዙካም ሲመሽ ወደ ማዙካ ጋር ሄደ፡፡ ማዙካም የፋዙካ ፊት አሮ፣ ያ ነጭ ፊቱ እንደ ከሰል ጠቁሮ/ይቅርታ ለካ ከሰል የለም ሲኦል/ ብቻ ምን ልበላቹ ግራ ተጋብቶ ስታየው ‹‹ምንሆንክ? ዛሬ ምን አገኘህ?›› አለችው፡፡

እሱም ‹‹ምን… ባክሽ አንድ ነብይ የሚሉት ሰው በመንገድ ሲሄድ እኔ ድንጋይ ላይ ተቀምጬ ለምን አልተነሳህልኝም፤ ለምን አላከበርከኝም ብሎ ተናገረኝ›› አለ፡፡ ማዙካም ተደናግጣ ዓይኗን አፍጥጣ ‹‹ምን አለህ›› አለችው›› ፋዚካ ነብዩ የተናገረውን ነገራት፡፡

እሷም ‹‹እንዴት እንደዚህ ታደርጋለህ? በእኔስ ላይ ይህንን እርግማን ታመጣለህ›› ብላ አለቀሰች፡፡ ፋዙካ ዓይኑን በጨው የታጠበ ደንታ ቢስ ነበርና እሷ ስታለቅስ ምንም አልመሰለውም፡፡ ምን ቢላት ጥሩ ነው ‹‹በቃ አይዞሽ የነብዩ ትንቢት እንዳይፈጸም እኛም ያችን ነገር አንፈጽምም›› አላት፡፡ እሷም ለጊዜው ተረጋጋች፡፡ ዝም ብላችሁ እዩልኝ በእነዚህ ነገሮች ውስጥ ሁሉ እኔ የለሁበትም፡፡

አንድ ቀን ፋዙካ ከጀለሶቹ ጋር ሆኖ የግብጦ አረቄ/ይቅርታ በሐበሽኛ ለማስረዳት ስል ነው የግብጦ አረቄ ያልኩት/ ወይን ጠጁን ልፎ ልፎ ሰክሮ ተንጀፍጅፎ ጀለሶቹ ተሸክመውት ቤት ገባ፡፡