Get Mystery Box with random crypto!

⛤Ιѕℓαмιc нιѕтory⛤

የቴሌግራም ቻናል አርማ islamic_historyyy — ⛤Ιѕℓαмιc нιѕтory⛤ Ι
የቴሌግራም ቻናል አርማ islamic_historyyy — ⛤Ιѕℓαмιc нιѕтory⛤
የሰርጥ አድራሻ: @islamic_historyyy
ምድቦች: ስዕሎች እና ፎቶዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.48K
የሰርጥ መግለጫ

"በጊዜያቱ እምላለሁ ሰው ሁሉ በእርግጥ በኪሳራ ውስጥ ነው እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት በእውነትም አደራ የተባባሉት በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ"
ሱ,ዐስር፦(1፥3)
ለማንኛውም ጥያቄ እና ለማስታወቂያ ስራ ➱ @Mahiro_fkr
You tube channel➘➘➘
https://youtube.com/channel/UCUYbaX1b-BcwERNZybzSNYw

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 31

2022-09-30 21:47:21 ሰደቃ በምታበዛበት ወቅት
እርዝቅህ ይበዛል፡፡ ሶላት ውስጥ
መረጋጋት ስታበዛ ደስተኝነትህ ይበዛል፡፡
ለቤተሰቦችህ መልካም ስትሆን ሂወትህ
ይስተካከላል፡፡
:¨·.·¨: ❀  
 `·. @Nun_tube
3.7K viewsالحب الأسود, 18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-30 20:22:11 #ሱናን ተከተል ከቢድዓ ተጠንቀቅ

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿إنَّهُ ليس شيءٌ يُقَرِّبُكُمْ إلى الجنةِ إلّا قد أَمَرْتُكُمْ بهِ، وليس شيءٌ يُقَرِّبُكُمْ إلى النارِ إِلّا قد نَهَيْتُكُمْ عنهُ،﴾

“ወደ ጀነት የሚያቀርባችሁ ሆኖ ከሱ ያላዘዝኳችሁ አንድም ነገር የለም። ወደ እሳት የሚያቀርባችሁ ሆኖ ከሱ ያልከለከልኳችሁ አንድም ነገር የለም።”

ሲልሲለቱ አሶሂሃ: 2866

አብደላህ ኢብኑ መስዑድ (رضي ﷲ عنه) እንዲህ ይላል፦

“ተከተሉ! ቢዳዓንም አትፍጠሩ! ሱና በቂያችሁ ነውና። ሁሉም የቢድዓ ተግባር ጥመት ነው።”

አልመርወዚ ፊይ ሱና: 1/28

┄┉┉✽‌»‌ ✿ »‌✽‌┉┉┄
t.me/+jPQLXna9F-E3ZDQ0
https://bit.ly/3PJRnHE
4.0K viewsالحب الأسود, 17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-30 20:22:00 የአገር መሪ ናቸው። ፍትህን ያነገሱ የሐቅ ሰው። በእውነት ብርሀን ስር የዳኙ መሪ። አንድ ምሽት ላይ በመኖሪያ ቤታቸው በሻማ ብርሃን እየታገዙ የአስተዳደራቸውን የግምጃ ቤት የገቢና ወጪ ሂሳብ በመስራት ላይ ናቸው። በር ተንኳኳ። እሳቸውን ለማነጋገር የሚፈልጉ ሁለት ሰዎች ነበሩ። በአስተዳደሩ ስልጣን ውስጥ ሁነኛ ቦታ የማግኘት ምኞት ነበራቸው። የመጡትም ይህንን ህልማቸውን ያሳካልናል ያሉትን አንድ ሃሳብ ይዘው ነው። ይህንን ሃሳባቸውን በመቀበል በመንግስታቸው ውስጥ ከፍተኛ ስልጣን የሚስጧቸው ከሆነ እነርሱ በፊናቸው ሙሉ ድጋፍ ለመስጠት ቃል እንደሚገቡ በመግለፅ ለመደራደር ነበር። 

   ሰዎቹ እንደተቀመጡ የበራው ሻማ ጠፋና ሌላ ሻማ ተለኮሰ። በዚህ ጊዜ ሁለቱ ሰዎች በመገረም ሰሜት እርስ በእርሳቸው ተያዩ።  ምክንያቱን ለማወቅ የበለጠ ጉጉት ያደረበት አንደኛው ሰው የመጣበትን ጉዳይ ከማንሳቱ ቀደም ብሎ የሚበራውን ሻማ አጥፍተው ሌላ ሻማ የለኮሱበት ምክንያት ምን እንደሆነ ጠየቀ። እሳቸውም "እናንተ ወደቤት ስትገቡ ይበራ የነበረውን ሻማ ከመንግስት ግምጃ ቤት ገንዘብ ወጪ ተደርጎ የተገዛ የህዝብ ሀብት ነው። ይህ የምትመለከቱትን የግምጃ ቤት የወጪና ገቢ ሂሳብ ለመስራት ስል ነበር ያበራሁት አሁን እናንተ የመጣችሁበት ጉዳይ የግል ጉዳያችሁ በመሆኑ የበፊቱን ሻማ በማጥፋት ይህንን ከራሴ ገንዘብ ወጪ አድርጌ የገዛሁትን ሻማ ለኮስኩት" በማለት ለቀረበው ጥያቄ ማብራሪያ ሰጡ። በዚህ ጊዜ ሁለቱ ሰዎች ቀደም ሲል እንዳደረጉት እርስ በእርሳቸው ተያዩ የመጡበትን ዓላማ ማንሳት ቀርቶ አንዲት ሌላ ቃል እንኳ መተንፈስ ተሰኗቸው ወጥተው ሄዱ። ሰውየው አሊይ ኢብኑ አቢ ጣሊብ ነበሩ። አላህ መልካም ስራቸውን ይቀበላቸው።

   ኢስላም አለምን ሲመራ እንዲህ ነበር ፍትህ የነገሰው

╔════ ════╗
             ɪsʟamic history
             ɪsʟᴀᴍɪᴄ history
╚════ ════╝

•┈•❈••✦✾ቴሌግራማችንን ✾✦••❈•┈•
      Join & share
https://t.me/+jPQLXna9F-E3ZDQ0
✿✶┈┈┈┈•✶✶✾✶✶•┈┈┈┈✶✿
3.6K viewsالحب الأسود, 17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-30 20:20:24 ኢስቲቃማ ሁሌም አስፈላጊ ነው አላህን እንለምነው...
መጀመሪያ መስተካከሉ አይደለም ቁም ነገሩ
መጨረሻው ማማሩ ነው...

{رَبَّنَا لَا تُزِغْ قُلُوبَنَا بَعْدَ إِذْ هَدَيْتَنَا وَهَبْ لَنَا مِن لَّدُنكَ رَحْمَةً ۚ إِنَّكَ أَنتَ الْوَهَّابُ}
"(እነሱም ይላሉ)፡- «ጌታችን ሆይ! ቅኑን መንገድ ከመራኸን በኋላ ልቦቻችንን አታዘምብልብን፡፡ ከአንተ ዘንድ የኾነን ችሮታም ለኛ ስጠን፡፡ አንተ በጣም ለጋስ ነህና፡፡»"
                   [ሱረቱ አሉ ዒምራን:6]

┄┉┉✽‌»‌ ✿ »‌✽‌┉┉┄
t.me/+jPQLXna9F-E3ZDQ0
https://bit.ly/3PJRnHE
3.3K viewsالحب الأسود, 17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-30 20:19:59 ከሰለፎች ምርጥ አጋጣሚዎች…

አንዱ ተጠየቀ …" ለሰዎች መልካምን ነገር አውለህ ስታበቃ ውለታህን ሲረሱብህ አታዝንምን ??? "
እሱም ፦ " ሲጀመርም ምስጋናቸውን ስላልጠበቅኩ  አላዝንም ።  አላህ በጎ ሰሪዎችን መውደዱ ብቻ ይበቃኛል " አላቸው

•┈┈• ❀ ❀ •┈┈•

የየሱፍ ወንድሞች « እኛ ለሱ ጠባቂዎች ነን»  ሲሉ አባታቸው ደግም « አላህ ከጠባቂዎች ሁሉ በላጭ ነው» አላቸው
እነሱ ዩሱፍን ሲጥሉ አላህ ግን ጠባቂው ሆነ
 
የምንወዱትን ነገር ለአላህ አደራ ስጡ

•┈┈• ❀ ❀ •┈┈•

{ ٱقْرَأْ كِتَٰبَكَ كَفَىٰ بِنَفْسِكَ ٱلْيَوْمَ عَلَيْكَ حَسِيبًۭا }

«መጽሐፍህን አንብብ፡፡ ዛሬ ባንተ ላይ ተቆጣጣሪነት በነፍስህ በቃ» (ይባላል)፡፡

ዛሬ አንተ ስራህን ታፅፋለህ  ነገ ደግሞ ያፃፍከውን ታነባልህ ። ስለዚህ ነገ በምታነበው እንድትደሰት ዛሬ የምታፅፈውን አሳመር !  

•┈┈• ❀ ❀ •┈┈•


ሰዎች ጠየቁት… "ሰላትህ ላይ እንዴት ቀጥ ልትል ቻልክ ???"

እሱም ፦ « አንድ ሸይኽ " አንተ ሰላትህን የተውከው ሰው ሆይ ! ያንተ መከራ እኮ ከ ኢብሊስ የበለጠ ከባድ ነው። ምክንያቱም ኢብሊስ ለአደም ሱጁድ ውረድ በተባለ ጊዜ እምቢ ሲል አንተ ደግሞ ለአደም ጌታ ሱጁድ ለማድረግ እምቢ አልክ ። እንደው በአንተና በጌታህ መካከል  ምን ቢኖር ነው እርሱን መገናኘትን የጠላኸው ! ?" ብለው ሲናገሩ  ሰምቼ ነው »  አላቸው

•┈┈• ❀ ❀ •┈┈•


አንዲት እናት 10 ልጆች ቢኖሯት አስሩንም ተንከባክባ ትይዛለች ። የሚገርመው ነገር ግን ምን አልባት 10 ልጆች አንድ እናታቸውን መንከባከብ ያቅታቸዋል ።

አላህ ወላጆቻችን ለመንከባከብ ይወፍቀን…

ከእናቱ እግር ስር ሁኖ እሷን የተንከባበከ … ከሰዎች ሁሉ  በላይ ሁኖ ይኖራል።

•┈┈• ❀ ❀ •┈┈•

{ وَأَدْخَلْنَٰهُ فِى رَحْمَتِنَآ ۖ إِنَّهُۥ مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ }

«በችሮታችንም ውስጥ አገባነው፡፡ እርሱ ከመልካሞቹ ነውና፡፡»

ከአላህ እዝነት ድርሻህ የሚሆነው በመልካምነትህ ልክ ነው…


•┈┈• ❀ ❀ •┈┈•

{ إِذْ نَادَىٰ رَبَّهُۥ نِدَآءً خَفِيًّۭا }

«ጌታውን የምስጢርን ጥሪ በተጣራ ጊዜ (አስታውስ)፡፡»

ዱዓህን አሳንሰህ አትመልከት ። ይህ ዝቅ ያለው ድምፅ የሰማያት በሮች ተከፍተውለታል።

•┈┈• ❀ ❀ •┈┈•


{ إِذْ يَقُولُ لِصَٰحِبِهِۦ لَا تَحْزَنْ إِنَّ ٱللَّهَ مَعَنَا ۖ }

« ለጓደኛው አትዘን አላህ ከእኛ ጋር ነውና ባለ ጊዜ አስታውስ »

ምርጥ ጓደኝነት ማለት የዱንያን ውጣውረድ የሚያቀልልህና ወደ አላህ የሚያቀርብህ ነው።

•┈┈• ❀ ❀ •┈┈•


{وَمَنْ أَعْرَضَ عَن ذِكْرِى فَإِنَّ لَهُۥ مَعِيشَةًۭ ضَنكًۭا وَنَحْشُرُهُۥ يَوْمَ ٱلْقِيَٰمَةِ أَعْمَىٰ}

«ከግሣጼዬም የዞረ ሰው ለእርሱ ጠባብ ኑሮ አለው፡፡ በትንሣኤም ቀን ዕውር ኾኖ እንቀሰቅሰዋለን፡፡»

ጭንቀትና ሀዘን ባጋጠመህ ጊዜ ፈጥነህ  ከቁርዓን ጋር ያለህን ሁኔታ አስተካከል።


┄┉┉✽‌»‌ ✿ »‌✽‌┉┉┄
t.me/+jPQLXna9F-E3ZDQ0
https://bit.ly/3PJRnHE
3.7K viewsالحب الأسود, 17:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-30 13:56:44 Irraa if-eegaa ይጠንቀቁ! ያስጠንቅቁ!

Namni muslima tahe Ayyaana Irreechaa akka hin dhayne.
ሙስሊም የሆነ ሰው ኢሬቻ የሚከበርበት ቦታ እንዳይሄድ!

Ayyaanni Irreechaa Ayyaana Waaqeefataan waggatti Kabajan.
የኢሬቻ በዓል ዋቄፈታዎች በዓመት የሚያከብሩት በዓላቸው ነው።

Kan Bakka bishaanii fi bakka odaan jirutti buna dhadhaa wajji godhanii ibidda odaa jalatti aarsanii odaaf sujuudani.

ውሃ ያለበት ቦታ እና ኦዳ ዛፍ ያለበት ቦታ በመሄድ ቡናን በቅቤ ጋር አድርጎ ኦዳ ስር እሳት አያይዞ ለኦዳ ይሰግዳሉ።

kan bishaan citaan tuqanii waliti facaasani akka (Xabalaa).
ሳር ቆርጦ ውሃን በማስነካት እንደ ጠበል ይረጫጩበታል።

Kuni ammoo Shirkii dha. ይህ ደግሞ ሽርክ ነው።

Rabbiin nama Isatti yagutoomsuu hin araaramu.
አላህ በእሱ ለሚያጋራ አይምርላቸውም፣

Nama Rabbitti yagutoomsu Jannata hin seenu kana Rabbumatu Qur'aana keessatti dubbate.
የሚያጋሩበት ሰዎች ጀነት አይገቡም፣ ይህን አላህ በቁርዓን ተናግሮታል።

Garuu namootni waan kana hin beeyne ayyaana oromoo itti fakkata.
ይህን የማያውቁ ሰዎች መላው የኦሮሞ በዓል ይመስላቸዋል፣

Oboleeyyan Islaamaa waliif dhaamaa nama Islaamaa hunda Jaahilummaarraa deebisaa.
ውድ ሙስሊም ወንድሞች ይህን የጃሂሊያን ድርጊት ሙስሊሞች እንዳይተገብሩት ህዝቡን እንምከር።

Dirqamummaa keessan bayaa.
ግዴታችንን እንወጣ፣

irreechaan sabboonummaa miti Islaamummaa ganuudha malee.
ኢሬቻ ሰቦኑማ አይደለም ኢስልምናን መክዳት እንጂ፣

Islaamummaan Rabbi biraa nuuf dhufte.
Kharaa Rabbii Haa Qabannu.
እስልምና የመጣልን ከአላህ ነው። የአላህን መንገድ እንያዝ፣

La Ilaha IllAllah Muhammadur Rasulullah!

Nun Tube
t.me/+erRKiinjTgc3MDE0
t.me/+erRKiinjTgc3MDE0
4.5K viewsالحب الأسود, edited  10:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 21:22:42
4.2K viewsFurqan Online Quran, 18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 21:22:42 ተባበሯቸው!

«بسم الله الرحمن الرحيم
እነሆ ተጀመረ!

ለኢብኑል ጀዘሪይ የቁርአንና የዲን ትምህርት ማዕከል ግንባታ የሚሆን የቦታ ግዢ እንቅስቃሴ ከዛሬው ቀን ጀምሮ በይፋ መጀመሩን እያበሰርን አቅማችን በፈቀደው ልክ የዚህ ዘመን ተሻጋሪ ፕሮጀክት አካል እንድንሆን ጥሪያችንን እናቀርባለን።

ማዕከሉ አሁን ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን በቁርአን ሒፍዝና በተለያዩ የዲን ትምህርቶች በኢስላማዊ ተርቢያ እያስተማረ ይገኛል።


ቁርአንን መሰጠት ከአላህ የሆነ ስጦታ እንደመሆኑ መጠን በዚህ ላይ መሳተፍ በራሱ ትልቅ የሆነ እድል ነው።

አላህ እንዲህ ይላል፦

ثُمَّ أَوْرَثْنَا الْكِتَابَ الَّذِينَ اصْطَفَيْنَا مِنْ عِبَادِنَا ۖ فَمِنْهُمْ ظَالِمٌ لِّنَفْسِهِ وَمِنْهُم مُّقْتَصِدٌ وَمِنْهُمْ سَابِقٌ بِالْخَيْرَاتِ بِإِذْنِ اللَّهِ ۚ ذَٰلِكَ هُوَ الْفَضْلُ الْكَبِيرُ

ከዚያም እነዚያን ከባሮቻችን የመረጥናቸውን መጽሐፉን አወረስናቸው፡፡ ከእነርሱም ነፍሱን በዳይ አልለ፡፡ ከእነርሱም መካከለኛ አልለ፡፡ ከእነሱም በአላህ ፈቃድ በበጎ ሥራዎች ቀዳሚ አልለ፡፡ ያ (ማውረስ)፤ እርሱ ታላቅ ችሮታ ነው፡፡

የአላህ መልዕክተኛም(ﷺ) እንዲህ ይላሉ፦

خيركم من تعلم القرآن وعلمه
ከእናንተ በላጫችሁ ቁርአንን ተምሮ ያስተማረ ነው።

መስጂዳችን የራሱ የሆነ መድረሳ የሌለው እንደመሆኑ ከተማሪው ብዛት የተነሳ በወንዶችም በሴቶችም በኩል በአግባቡ ሰላት ለመስገድ እስከመቸገር ድረስ አድርሶናል።መስጂዱ ሲጀመርም ጠባብና ምንም አይነት የግቢ ቦታ የሌለው እንደመሆኑ ከፍተኛ የሆነ መጨናነቅ አለ።በዛ ላይ አካባቢው ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነ ሙስሊም ማኅበረሰብ የሚገኝበት ሲሆን በተለይ ረመዳን ሲመጣ ከመስጂዱ አቅም በላይ የሚሆንበት ሁኔታ ዘወትር የሚስተዋል ተጨባጭ ነው።

ይህ ከፍተኛ የቦታ ጥበት ባለበት ሁኔታ ከመስጂዱ ጎን ያለ 200ካሜ የግለሰብ ቦታ አስገዳጅ በሆነ ምክንያት ለሽያጭ ቀርቧል።ያም ብቻ ሳይሆን ሽያጩ በአስቸኳይ መፈፀም የግድ የሆነበት ሁኔታ ተፈጥሯል።በመሆኑም በጥቂት ቀናት ውስጥ ይህን ግዢ ማሳካት ካልቻልን ቦታውን ዳግም ልናገኘው የማንችልበት ሁኔታ ከፍ ያለ ነው።አሁን ላይ ያሉብን መጠነ ሰፊ ችግሮችም ተባብሰው የሚቀጥሉ ይሆናሉ።እንዳጋጣሚ ሆኖ ከዚህ ቦታ ሌላ መስጂዱ ዙሪያ ምንም አይነት አማራጭ ቦታ አለመኖሩ ደግሞ የዚህን ቦታ አስፈላጊነት ይበልጥ የግድ ያደርገዋል።

ስለሆነም የመጀመሪያው አላማችን የቦታውን ግዢ ማሳካት ነውና የሚቻለንን ሁሉ ማድረግ የግድ ይለናል።እናም እንደየ አቅማችን አላህ ያግራልንን ያህል አስተዋፅኦ በማድረግ ላይ እንበርታ።

ከራሳችን ባለፈ ሌሎችን በማሳተፍም ከሰጪዎቹ እኩል ምንዳን እናግኝ።ይህ እጅግ ብልህ የሆኑ ሰዎች ንግድ ሲሆን ትርፋማነቱም የተረጋገጠ ነው።

ኢብኑል ጀዘሪይ የቁርአን ትምህርት ማዕከል ከኢብኑ መስኡድ ኢስላሚክ ሴንተር ቅርንጫፎች አንዱ ሲሆን ማኅበረሰቡን በተስተካከለ ዐቂዳና በመልካም ስነ ምግባር ለመቅረፅ ሌት ተቀን እየሰራ ያለ ማዕከል ነው።አድራሻውም ጀሞ ከመስታወት ፋብሪካ ጀርባ ቻይና ካምፕ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ  "ከራህማ መስጂድ" ጎን ነው።
=============


ኢብኑል ጀዘሪይ የቁርአን ትምህርት ማዕከል
1000492485687 (የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)

[የቦታው የሽያጭ ዋጋ፦4,200,000ብር]

፨፠ ገቢ ያደረጋችሁበትን ደረሰኝ ወይም Screen shot በሚከተሉት አማራጮች ያድርሱን፦

https://t.me/+suWUfRlR1xJjNTg0
@mirajnesru
@Nesraahmed
@abdellah638

0937213444»
4.1K viewsFurqan Online Quran, 18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 20:24:25 ውዷ እህቴ ለትዳርሽ ብቁ ነሽን?
             
ባለቤትሽ ወደ ቤት በገባ ግዜ በእጅሽ ያለውን ነገር ትተሽ እሱን ለመቀበል ካልሄድሽ፣ ፊቱ ላይ የተመለከትሽውን የድካም ስሜት ካላስረሳሽ
{ አንቺ ለትዳርሽ ብቁ አይደለሽም}

ባለቤትሽ አንቺ በእጅሽ ሰርተሽ የማታበይው ከሆነ ከምግብ ቤቶች ከተመገበ ፣ ልብሶቹን የማታዘጋጂለት ከሆነና ወደ ማጠቢያ ቤት ከወሰደ
{አንቺ ለትዳርሽ ብቁ አይደለሽም}

ባለቤትሽ በተቆጣ ግዜ በአስር ቃላት የምትመልሺለት ከሆነ፣ድምፅሽን ከፍ አድርገሽ ካወራሽው{አንቺ ለትዳርሽ ብቁ አይደለሽም}

ከባለቤትሽ አጠገበ በተቀመጥሽ ግጔዜ ጠረንሽ ጥሩ ካልሆነ፣የልብስሽን ንፅህና ካልጠበቅሽ፣እሱን የሚማርኩ ካልሆኑ {አንቺ ለትዳርሽ ብቁ አይደለሽም}

ከሱ ጋ በተጣላሽ ወቅት ወደ እናትሽ ቤት፣ወደ እህትሽ፣ ወደ ጓደኛሽ ቤት የምትሄጂ ከሆነ
{አንቺ ለትዳርሽ ብቁ አይደለሽም}

ከባለቤትሽ ቤተሰቦች ጋር ስትሆኚ የሱን ቤተሰቦች መልካምን በማድረግ የማትንከባከቢ ከሆነ {አንቺ ለትዳርሽ ብቁ አይደለሽም}

አላህን በመታዘዝ ላይ የማታበረታቺው ከሆነ፣ ክልክል ነገራቶችን እንዲተው የማታደርጊ እና ወደ ተውበት የማትገፋፊው ከሆንሽ
{አንቺ ለትዳርሽ ብቁ አይደለሽም}

ባልሽ የሚወዳቸውን እና የሚጠላቸውን ነገሮች ለይተሽ ካላወቅሽ {አንቺ ለትዳርሽ ብቁ አይደለሽም}

ሲራ TUBE
t.me/+ab1ZviUdLYExZWJk
t.me/+ab1ZviUdLYExZWJk
3.7K viewsإنت حايت, 17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 20:23:11 #ተስፋ አትቁረጥ!

ከአነስ ቢን ማሊክ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿يقولُ: قال اللهُ: يا ابنَ آدَمَ، إنَّك ما دَعَوْتَني ورجَوْتَني غفَرْتُ لك على ما كان فيك ولا أُبالي، يا ابنَ آدَمَ، لو بَلَغَتْ ذُنوبُك عَنانَ السَّماءِ ثمَّ استَغفَرْتَني غَفَرْتُ لك ولا أُبالي، يا ابنَ آدَمَ، إنَّك لو أَتَيْتَني بقُرابِ الأرضِ خَطايا ثمَّ لَقيتَني لا تُشرِكُ بي شَيئًا، لَأَتَيْتُك بقُرابِها مَغفرةً.﴾

“የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ የኣደም ልጅ ሆይ! ከለመንከኝና ከከጀልከኝ ባንተ ላይ ላለው (ወንጀል) ደንታ አይኖረኝም እምርልሃለሁ፡፡ የኣደም ልጅ ሆይ! ወንጀሎችህ የሰማይ ደመናን ቢደርሱ ከዚያም ምህረትን ከጠየቅከኝ እምርልሃለሁ፡፡ የኣደም ልጅ ሆይ! አንተ ምድርን ሊሞላ የቀረበ ወንጀል ጋር ብትመጣኝ፣ ከዚያ በኔ ላይ ምንም ሳታጋራ ካኘኸኝ እሷኑ ሊሞላ የቀረበ ምህረትን ይዤ እመጣሀለሁ፡፡”

ቲርሚዚ ሀሰን ብለውታል: 3540

┄┉┉✽‌»‌ ✿ »‌✽‌┉┉┄
t.me/+jPQLXna9F-E3ZDQ0
https://bit.ly/3PJRnHE
3.7K viewsإنت حايت, 17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ