2022-10-11 20:02:41
╔═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╗
". ዩንቨርስቲ እና የሴት ህይወት 2 ".
ፀሐፊ፦ ፎዝያ
╚═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╝
╭───── • ❊ • ─────╮
@Islamic_History
╰───── • ❊ • ─────╯
{ክፍል ²3}
<ሀዉሊ በአላህ አታስጨንቂኝ ዝም በይ የኔ ሀላል እያለ ይለምነኛል
<<እኔ ግን ይሄ ዉሸት ነዉ ብዬ በዝምታ አየዋለሁ
<ሀዉሊ በቃ ተነሺ አንዴ አግብተሽኛል ምንም ልታረጊ አትችይም ተነሺ
<<ሀሩን ግን እንዴት ላገባህ ቻልኩ እኔኮ የምወደዉ መሲ ነበር
<እሺ እኔስ ምን ልሁን እያለ ያለቅሳል የሱ እንባ የኔ ፊት ላይ ጠብ አለ ከዛም ብንን ብዬ ተቀመጥኩ ለካ ሀሱኑ ወረቀቱንም ይዛ አልወጣችም እሷ ነበረች ዉሀ ፊቴ ላይ ያርከፈከፈችብኝ ያአሏህ ደንገጥ ብዬ በቃ አገባሁት ብዬ በምሬት ተናገርኩ ሀስኑም ፈገግ ብላ <አላህኮ ሁለት ልቦችን ማገናኘት ከፈለገ የሰማይና የምድር ያህል ርቀት እራሱ አይገድበዉም ያገናኛቸዋል ብላኝ ከአጠገቤ ሄደች እኔ እዛዉ የነበርኩበት ክፍል አልጋ ስለነበረዉ ቁጭ ብዬ አንገቴን አቀረቀርኩ ከመቀስፈት ሀሩን ገባ ግን ሙሽራ ስለሆነ ይሁን ካለ ፍላጎቴ ስላገባሁት ይሁን ባላዉቅም አጠገቤ ከቆመ ደይቃዎች አልፈዉታል ግን ደሞ አልነካኝም አላወራኝም እኔ ዝምታዉ እያናደደኝ ለመናገርና ንዴቴን ለመወጣት ትሰማኛለህ እኔ መሳይ ብዬ ፊቱን ሳየዉ ሀሩን አይደለም ኦዉዉ አምላኬ ህልም ወይስ ቅዠት እያልኩ በጣም ተደሰትኩ
<ሀዉሊ የኔ ሚስት አሁን በደንብ ስሚኝ
<<ምን ልስማህ ግን እንዴት
<እሱን ለመናገር ሰአት የለኝም አሁን ይዤሽ ልወጣ ነዉ በጓሮ ስለሆነ የምንወጣዉ ባዳ የሆነ ወንድ አያይሽም መኪና ደሞ የራሴን ነዉ የያዝኩት ብሎ ምንም ኮተት ሳንይዝ ከነ ሀስኑ ቤት ለቀን ወደ መሳይ ቤት ሄድን መኪና ዉስጥ ምንም አላወራንም እኔ ሁሉም ነገር ቅዠት ነዉ የመሰለኝ አይ እወነት አይደለም እያልኩ ለራሴ ነግረዋለሁ በመሀል ስልክ ተደወለና መሳይ አንስቶ ወተናል በቃ ኢንሻአላህ ሲመቸን እንደዉላለን ብሎ መልሶ ስልኩን አስቀመጠ
<<ሚስ ግን
<ሚስ ግን ምናምን ብሎ ነገር አይሰራም አሁን ባል ስለሆንኩኝ እቆጣሻለሁ እቆጣጠርሻለሁ ብሎኝ ፈገግ አለ ብቻ በምን ፍጥነት እንደሆነ ባላዉቅም ቤት ደረስንና ወደ ሳሎን ገባን እኔም ድካሙ ይሁን ባላዉቅም ምግብ ለመፈለግ እንጎዳጎድ ጀመር መሲም እርቦኛል እባክሽ ቶሎ በይ ብሎ ይጮህ ጀመር እኔም ስፈልግ የተሰራ ነበርና አቀራርቤ ወደ መሲ ጋር ወሰድኩለት እሱም ፈገግ እያለ ለመብላት መዘጋጀት ሲጀምር
<<ዉስጤ አንድ ነገር ነገረኝ አዎ ባሌ ስለሆነና ታሞ ስለተነሳ በደንብ መንከባከብ ጀመርኩ በጣም አጎርሰዉ ጀመር መሲም በግማሽ ፈገግታ ታጅቦ እጆቼን እየሳመ ይበላልኝ ጀመር ብቻ በላልተን ከጨረስን ቡሀላ እስከሚመሽ ብለን ቁረአን መቅራት ጀመርኩ እሱ ደሞ ዲያሪ ይፅፍ ጀመር እስከመግሪብ በዛ መልኩ አሳለፍንና ወደ ኢሻ ሰአት ለመዘዋወርና እኛም እንደ ባልና ሚስት ለመተኛት በእርጋታ መጨበቅ ጀመርን የማይደርስ የለምና የኛም የፍልሚያ ሰአታችን ደረሰች አልሀምዱሊላህ ዱአ አድርገን በጥሩ ሁኔታ አብረን ነበርን መሲ ድንግል ስለነበርኩ ደስ እያለዉ ነበር እናም ጠዋት ሱቢ ሁለታችንም ስለደከመን አረፈድን እናም ተነስተን ገላችንን ተጣጥበን ሰግደን ቁርስ ለመስራት ተነሳዉ መሲም አብሮኝ ተነሳ
<<እንዴ
<ምነዉ
<<ተኛ እንጂ
<ለምን
<<ስለደከመህ ነዋ
<እዉነት እናዉራ ከተባለ የደከምሽዉስ አንቺ ነሽ
<<እንዴ ማለት
<እስከዛሬ ለባልሽ ያስቀመጥሽዉን ክብረንፅህና በታማኝነት ስለአስረከብሽ ነዋ
<<አሀሀሀሀሀ እረ እስኪ እዉነት በል
<ሚካኤልን
<<ምን ብዬ ሳፈጥበት
<ኦዉዉዉ ይቅርታ የኔ ሚስት ብሎኝ አቅፎኝ <<ታዉቂያለሽ እኔ ከአንቺ ጋር አንድ ቤት በሀላል እኖራለሁ ብዬ አስቤ አላዉቅም ነበር ነገር ግን የፈጣሪ ስራ ዱአዬን ሰምቶኝ ዛሬ ከአንቺ ጋር አደረገኝ የኔ ሚስት በኔ አስተሳሰብ አሁንም ቢሆን የዛሬ እንጂ የነገ የሚባል ነገር የለም>>
<<ምን ማለት ነዉ
<አይ ምንም እያለኝ በመሀል ዳኒ እየተክለፈለፈ መጣ
<<ምን ያሮጥሀል አቶ ዳኒ ብዬ ፈገግ አልኩ
<ይወልሽ የወንድሜ ሚስት ዩንቨርስቲ ነዉ ያደርኩትና አሁን ገና መዉጣቴ ነዉ ያዉ ለቁርስ ነበር ወደዚ የመጣሁት ሳስበዉ እናንተም አልበላቹሁም መሰለኝ
<<አዎ አልበላንም ቁርስ ልሰራ ተነስቼ ነበርናም ወንድምህ ወይ አይሰራ ወይን ደሞ አያሰራኝ ዝምብሎ ያስጮህኛል ብዬ እየቀለድኩ ወደ ሚስ ስዞር ተኮሳትሮ ወደ መኝታዉ ገባ እኔ የመኮሳተሩ ነገር ባይገባኝም ግን ወደ ዳኒ ዞሬ ይወልህ ዉዱ አማቼ ባልየዉ ገና ከአሁኑ መኮሳተሩን ጀምሯል
<ተይዉ እንቅልፉን አልጨረሰም ይሆናል
<<እረ ዛሬ ለሱቢሂ እራሱ አርፍደን ነዉ የተነሳነዉ
<እና በመጀመሪያ አዳራቹ ለሊት ለማኝ ሳያራ ልትነሱም ፈልጋቹ ነበርንዴ ብሎ አሳቀኝ
<<አንተም ብታገባ ጥሩ ነዉ
<ማን እኔ
<<አዎ አንተ
<የሴጣን ጆሮ ይደፈን
<<ማለት
<እስኪ አስቢዉ አገባሁ እንበል ከዛስ
<<ከዛማ ትኖራላቹህ
<ሀዉሊ የዋህኮ ነሽ እሺ ማንን ላግባ ምረጪልኝ
<<ሩታን ለምን አታገባትም
<በስመአም አንቺ በጣም ትቀልጂያለሽ
<<እረ የእዉነቴን ነዉ
<ሀዉሊ ምን በደልኩሽ ቆይ ሩታን አግብቼ በተአምር የቆመ ፖስታ መስዬ እንድታይኝና አንቺና ባልሽ ቱሪስቶችን እየጠራቹ ወንዱ ሉሲን ኑ ጎብኙልን እያላቹ እንድታፌዙብኝ ነዉዴ
<<እንዴ ለምን እንደሱ አልክ ሩታስ ምን ያንሳትና ነዉ
<ይወልሽ ሀዉሊ ሩታ ትምርት ላይ እንጂ ኩሽና ላይ ጎበዝ አይደለችም እኔ ደሞ በደንብ ሙያ ያላትን ሴት ነዉ የምፈልገዉ እንደዉ በፈጠረሽ ከእናንተ ሀገር ጎበዝ ሴት ካገኘሽልኝ ጠልፈሽም አስጠልፈሽም ቢሆን አምጪልኝ አስበሽዋል እኔ በሆዴ ቀልድ አላዉቅም ካልበላሁ ደም እከሳና የእናንተ መሳቂያ ነዉ የምሆነዉ ብሎ ቲኒሽ ፈታ አደረገኝ በዚ መሀል መሳይ የኔ ዉድ ስልክሽ እየተደወለበት ነዉ ብሎኝ ሰጠኝ ደዋዩን ሳይ ሀሱኑ ናት ላነሳዉ ስል ተቋረጠ ሚስኮል ነዉዴ ብዬ ስልኬን ስከፍተዉ ሀስኑ አስራ ሁለት ጊዜ ደዉላልኝ ነበር በጣም ደነገጥኩ ለካ ከሚስ ጋር ከክፍላችን ከወጣንበት ጊዜ ጀምሮ ነበር የደወለችዉ በጣም ደነገጥኩና መልሼ ልደዉል ስል እራሷ ቀድማኝ ደወለች ስልኩን አንስቼ ላወራ ስል እያለቀሰች ሀዉሊ ቶሎ ነይ ችግር ተፈጥሯል አለችኝ ከሀስኑ ጋር አብሮ ወደ ስልኬ የሚያስተጋባ ድምፅ አለ የብዙ ሰዎች የለቅሶ ድምፅ...
ክፍል ሃያ አራት ይቀጥላል
┄┉┉✽» ✿ »✽┉┉┄
t.me/+jPQLXna9F-E3ZDQ0
t.me/+jPQLXna9F-E3ZDQ0
1.1K viewsالحب الأسود, edited 17:02