Get Mystery Box with random crypto!

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ harunmedia — Harun Media - ሀሩን ሚዲያ H
የቴሌግራም ቻናል አርማ harunmedia — Harun Media - ሀሩን ሚዲያ
የሰርጥ አድራሻ: @harunmedia
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.42K

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-03-02 21:31:46
"እኛስ ለአድዋ" በሚል መነሻ አል-ወህዳህ የበጎ አድራጎት ማኅበር በቢላሉል ሀበሽ አዳራሽ ያዘጋጀው መሰናዶ በስኬት መጠናቀቁ ተገለጸ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ የካቲት 23/2015
...
"እኛስ ለአድዋ" በሚል መነሻ አል-ወህዳህ የበጎ አድራጎት ማኅበር በቢላሉል ሀበሽ አዳራሽ ያዘጋጀው መሰናዶ በስኬት መጠናቀቁን አዘጋጆቹ ገልጸዋል። በዝግጅቱ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የታሪክ ምሁራን የተገኙ ሲሆን በርዕሱ ዘሪያ ከመድረክ ተጋባዥ እንግዶች ውይይት ተደርጎበታል።
...
የፕሮግራሙን ሙሉ ይዘት በሀሩን ሚዲያ የማኅበራዊ ሚዲያ መገኛዎች ወደናንተ የምናደርስ ይሆናል።

ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
902 views18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 14:52:44
ዝናብ በሚቀርበት ጊዜ የሚሰገድ ሰላት (ሰላተል ኢስትስቃ) እንዲሰገድ የፌዴራል እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት
...
ሀሩን ሚዲያ፥ የካቲት 22/2015
...
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በቦረና ዞን በዝናብ እጥረት ምክንያት የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ በመላ ሀገሪቱ ሰላተል ኢስ ትስቃ እንዲሰገድ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጥሪ አቅርቧል።
...
ጠቅላይ ምክር ቤቱ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖቻችን ዕርዳታ የሚውል ድጋፍ ማሰባሰቢያ የባንክ ቁጥሮችንም ይፋ አድርጓል። የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በሰጡት መግለጫ "በእኛ ወንጀል ምክንያት የአላህ ራህመት የሆነው ዝናብ በመጥፋቱ ዛሬ ወጎኖቻችን በድርቅ ምክንያት የእኛን አፋጣኝ ምላሽ የሚፈልጉበት ወቅት በመድረሱ ሁላችንም የበኩላችንን ፈጣን ምላሽ መስጠት ይጠበቅብናል" ብለዋል።
...
አሏህ ሱብሀነ ወተዓላ ጥፋታችንን ይምረን ዘንድ ሰኞ የካቲት 27/2015 አ.ል በመላው ሀገራችን ሰላተል ኢስትስቃ እንዲሰገድ ጥሪ አቅርበዋል።

ሙሉ መግለጫው ከታች ተያይዞ ቀርቧል

ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
675 views11:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 14:52:28
በአዊ ዞን ቻግኒ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት አስተባባሪነት የሰላምና የአንድነት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው።
...
ሀሩን ሚዲያ፥ የካቲት 22/2015
...
በዛሬው እለት የካቲት 22 /2015 ተጀምሮ እስከ ነገ የሚቆይ በቻግኒ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት አስተባባሪነት የሰላምና የአንድነት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው።

በፕሮግራሙ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው የእለቱ የክብር እንግዳ እና የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ጀውሀር ሙሀመድ የተገኙ ሲሆን በተጨማሪም ከመጅሊሱ የክልሉ የዳእዋና የትምህርት ዘርፍ፣ የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ተጠሪዎች የምስራቅ ጎጃምና ምእራብ ጎጃም ዞን መጅሊስ ተወካዮች ተገኝተዋል።
...
የአዊ ብሄረሰብ ዞን የሀይማኖት ጉዳዮች ግጭት አስወጋጅ አቶ ሞገስና የሰላምና ደህነት ምክትል አቶ ሙሉአለም ዘሪሁን እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ሌሎችም የመንግስት ሃላፊዎች በፕሮግራሙ ላይ የተገኙ ሲሆን ከዑለሞችም ሸይኽ ሙሀመድ ዘይን ዘኽረዲን ኸሊልና ሸይኽ ሙሀመድ አወል በፕሮግራሙ ላይ ታድመዋል።
...
ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
646 views11:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 13:20:14
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በቦረና ዞን በድርቅ የተጎዱ ወገኖቻችንን ድጋፍ ዙሪያ በነገው እለት መግለጫ ይሰጣል።
...
ሀሩን ሚዲያ፥ የካቲት 21/2015
...
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በቦረና ዞን በድርቅ የተጎዱ ወገኖቻችንን ድጋፍ ዙሪያ በነገው እለት መግለጫ ይሰጣል። ረቡዕ የካቲት 22/15 ከጧቱ 4:30 በጠቅላይ ምክር ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሀን ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ ገልጾ የሚዲያ አካላት ሽፋን ይሰጡ ዘንድ ጥሩ አቅርቧል።
...
ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.4K views10:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 15:52:10 በኢስላማዊ ተቋማት ምዝገባ፣አገልግሎት አሰጣጥ ናአስተዳደር መመሪያ ላይ ስልጠና ተሰጠ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ የካቲት 20/15
...
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በኢስላማዊ ተቋማት ምዝገባ፣ አገልግሎት አሠጣጥና አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 01/2015 ላይ ለጠቅላይ ምክር ቤቱ፣ ከአዲስ ከተማ አስተዳደር እና ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለተውጣጡ ባለሙያዎች የሁለት ቀን የስራ ላይ ስልጠና በጠቅላይ ምክር ቤቱ የመሠብሠቢያ አዳራሽ ተሰጠ።
...
ስልጠናውን በቁርዓን በሼይኽ ያዕቁብ አብዱል ለጢፍ የተከፈተ ሲሆን በኢስላማዊ ተቋማት ምዝገባ ፣አገልግሎት አሰጣጥና አስተዳደር በመመሪያ ቁጥር 01/2015 ላይ በጠቅላይ ምክር ቤቱ በተዋረድ ለሚገኙ ባለሙያዎች እና ለባለ ድርሻ አካላት መሠጠት የተጀመረው ይህ ስልጠና የሚቀጥል መሆኑን የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ከማል ሀሩን በስልጠናው መክፈቻ ላይ ገልፀዋል።
...
በዘርፉ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ በተለያዩ ጊዚያት የድጋፍ ደብዳቤ ወስደው በስራ ላይ የሚገኙ እንዲሁም ከጠቅላይ ምክር ቤቱ የኢስላማዊ ተቋማት ምዝገባ፣አገልግሎት አሰጣጥ ና አስተዳደር ዳይሮክቶሬት በቅርቡ ለአገር በቀልና ለውጪ ሀገር የበጎ አድራጎት ድርጅቶች፣ማኅበሮች ፣የወቅፍ እና ጊዚያዊ ኮሚቴዎች መመዝገብ በቅርቡ እንደሚጀመር እና የምዝገባ ጥሪውን በጠቅላይ ምክር ቤቱ በይነ መረብ አማካኝነት ጥሪ እንደሚደረግ ስራ አስኪያጁ ገልፀዋል።
...
የኢትዮጵያ አስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እንደ አዲስ በአዋጅ ቁጥር 1207/2012 ከተቋቋመ በኋላ የኢስላማዊ ተቋማት ምዝገባ ፣አገልግሎት አሰጣጥ ና አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 01/2015 በጠቅላይ ምክር ቤቱ ታሪካዊ ያደርገዋል።
...
መረጃው የኢ/እስ/ጉ/ጠ/ም/ቤት ነው።

ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
2.0K views12:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 15:52:09
1.8K views12:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-26 19:40:17
በአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ግቢ ውስጥ ሲካሄድ የነበረው ኮንፈረንስ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ተገለጸ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ የካቲት 19/2015
...
"ኢስላማዊ አንድነት ለሀገር ሰላምና ልማት" በሚል መሪ ቃል በዛሬው እለት የተካሄደው ህዝባዊ ውይይት ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች የታዩበት መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በዋናነት የባህርዳር ከተማ ህዝበ ሙስሊሙ አንድ እንደሆነ ያሳየበት ፣ ወደፊቱን ዛሬ ላይ መገንባት እንዳለበት በጋራ የተስማማበት እጅ ለእጅ ተያይዞ ቃል የገባበት መድረክ እንደሆነ ተገልጿል።
...
መጅሊሱ የሁሉም ቤት እንደመሆኑ መጠን በመግባባትና በመመካከር ብዙ ስራዎች መስራት እንደሚጠበቅብን ከምንጊዜውም በበለጠ ተምረንበታል ያለው መጅሊሱ
ነገን ለመገንባት የዛሬ አንድነታችን ወሳኝ መሆኑን በአንድ ድምፅ አስምረንበታል ሲል ገልጿል። ለፕሮግራሙ መሳካት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ከጎናቸው ለነበሩ ሁሉ ምክር ቤቱ ምስጋናውን ያቀረበ ሲሆን በተከታታይ ለሚኖሩ ኮንፈረንስና ሴሚናሮች ከጎናቸው እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል።
...
ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.2K views16:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-26 15:01:31
የሙፍቲ ሸይኽ አደም ቱላ (ረሒመሑላህ) ፍሬ የሆኑ 6 ሺህ ሴቶች እና 3 ሺህ ወንድ ተማሪዎች ተመረቁ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ የካቲት 19/2015
...
የሙፍቲ ሸይኽ አደም ቱላ (ረሒመሑላህ) ፍሬ የሆኑ 6 ሺህ ሴቶች እና 3 ሺህ ወንድ ተማሪዎች በዛሬው እለት ተመረቁ።
..
የሸይኽ አደም ቱላ ማዳ ሀራሺ የተማሪዎች ምርቃት ፕሮግራም በሀረሪ ከተማ በደማቁ ተካሒዷል። በምረቃ ስነ ስርዓቱም 6ሺህ ሴቶች እና 3ሺህ ወንድ ተማሪዎች ተመርቀዋል።
...
ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
2.0K views12:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-26 11:14:24
በዘይድ ኢብን ሳቢት የቁርዓን ማኅበርና በሞሮኮው ንጉስ መሃመድ ስድስተኛ ፋውንዴሽን ድጋፍ የተዘጋጀው ዓመታዊ የቁርዓን ውድድር ትላንት በአዲስ አበባ ተጀምሯል።
...
ሀሩን ሚዲያ፥ የካቲት 19/2015

በዘይድ ኢብን ሳቢት የቁርዓን ማኅበርና በሞሮኮው ንጉስ መሃመድ ስድስተኛ ፋውንዴሽን ድጋፍ የተዘጋጀው ዓመታዊ የቁርዓን ውድድር ዛሬ በአዲስ አበባ ተጀምሯል። በውድድሩ ከተለያዩ የአገሪቱ አከባቢዎች የተውጣጡ 50 ተወዳዳሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ውድድሩ ትላንት እና ዛሬ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገልጿል።
...
በዘይድ ኢብን ሳቢት የቁርዓን ማኅበር ፕሬዝዳንትና የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የቁርዓንና የአዛን ውድድር ዋና ኃላፊ ኡስታዝ ኑረዲን ቃሲም በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ በአፍሪካ 32 አገራት የሚሳተፉበት የቁርዓን ውድድር ላይ የሚሳተፉ ኢትዮጵያዊያን እየተለዩ ነው።
...
የቁርዓን ውድድሩ የኃይማኖትን ዕውቀት ከማሳደጉም በተጨማሪም ኢትዮጵያዊ እሴቶችን ጠብቆ ለትውልድ ለማስተላለፍና ኢትዮጵያዊያን ወጣቶችን ከሌላውን ዓለም ሕዝቦች ጋር የባህል ልውውጥ እንዲያደርጉ እድል የሚፈጠር መሆኑን ተናግረዋል።
...
በውድድሩ ላይ በኢትዮጵያ የሞሮኮ አምባሳደር ኑዝሓ አላዊ፣ የሠላም ሚኒስቴር ተወካይ አቶ ትዕዛዙ ደሳለኝና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተገኝቷል። በውድድር መርኃ ግብሩ ላይ አስር አባላት ያለው የሞሮኮ ልዑክም ታድመዋል። የተለያዩ አካላትን ያቀፈው ይኸው ልዑክ የአል ነጃሽን መስጂድ እንደሚጎበኙ የተገለጸ ሲሆን ከተለያዩ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት እንደሚያደርጉም ተጠቁሟል።
...
ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.8K views08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 20:01:37
በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ከፍተኛ ድብደባ መፈጸሙ ተገለጸ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ የካቲት 16/2015
...
በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ከፍተኛ ድብደባ መፈጸሙ ተገለጸ። በዱራሜ ከተማ በሚገኘው የዋቻሞ ዩኒቨርስቲ ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ በአካባቢው የሚገኙ ጽንፈኛ የፕሮቴስታንት አማኞች ጥቃት አድርሰው በርካታ ቁጥር ያለው ተማሪ ለጉዳት ተዳርጓል።
...
ማክሰኞ እለት የተፈጸመው ጥቃት ከካምፓሱ የጸጥታ ኃይሎች አቅም በላይ ሆኖ የነበረ ሲሆን ዩኒቨርስቲውም ለተማሪዎቹ የደህንነት ከለላ ማድረግ ሳይችል ቀርቷል። ጥቃቱ በሚቀጥለው ቀንም ቀጥሎ የነበረ ሲሆን ሙስሊም ተማሪዎችን በመምረጥ በሴቶችም በወንዶችም ላይ ዘግናኝ ጥቃቶች ሰንዝረዋል። በጥቃቱ ቁጥራቸው ለጊዜው የማይታወቅ በርካታ ተማሪዎች የተጎዱ ሲሆን በጥቃቱ 5 ተማሪዎች ግን ከባድ ጉዳት ማስተናገዳቸው ተገልጿል።

ሀሩን ሚዲያ ክስተቱን በተመለከተ በቅርበት እየተከታተለ ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎችን ወደ እናንተ የሚያደርስ ይሆናል።
..
ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
984 views17:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ