Get Mystery Box with random crypto!

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ harunmedia — Harun Media - ሀሩን ሚዲያ H
የቴሌግራም ቻናል አርማ harunmedia — Harun Media - ሀሩን ሚዲያ
የሰርጥ አድራሻ: @harunmedia
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.42K

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-02-05 10:28:57 የታላቁን አሊም ሙፍቲ ሸይኽ አደም ቱላ መታሰቢያ ፋውንዴሽን የተመለከተ ታላቅ ህዝባዊ ዝግጅት በሐረር ኢማም አህመድ ስታዲየም መካሄድ ተጀምሯል።
...
ሀሩን  ሚዲያ ፥ ጥር 28/2015
..
በየታላቁን አሊም ሙፍቲ ሸይኽ አደም ቱላ መታሰቢያ ፋውንዴሽን የተመለከተ ታላቅ ህዝባዊ ዝግጅት በሐረር ኢማም አህመድ ስታዲየም መካሄድ ተጀምሯል። ዝግጅቱ ላይም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ኘሬዝዳንት ሼይኽ ሃጂ ኢብራሂምን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታላላቅ ሼሆች ኡስታዞች የሀረርና የአቅራቢያ ከተሞች ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
....
የሀሩን ሚዲያ ባልደረቦችም በዝግጅቱ ላይ የተገኙ ሲሆን ሙሉ ዝግጅቱን በአላህ ፍቃድ ወደናንተ የምናደርስ ይሆናል።

ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
2.2K views07:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 12:59:08
ሼይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ ለ3:00 ሰዓታት የፈጀ ቀዶ ጥገና ተዶርጎላቸው በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። አላህ ሙሉ አፊያቸውን ይመልስላቸው ዘንድ በዱዓ እንበርታ

ሀሩን ሚዲያ
1.1K viewsedited  09:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 16:30:25 የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ለእስላማዊ ተቋማት በሚሰጠው የምዝገባ አገልግሎት ዙሪያ የትውውቅ መድረክ አካሄደ።
...
ሀሩን ሚዲያ፥ ጥር 25/2015
...
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር
ለእስላማዊ ተቋማት በሚሰጠው የምዝገባ አገልግሎት ዙሪያ የትውውቅ መድረክ በዛሬው ዕለት በዋና መስሪያ ቤቱ አዳራሽ አካሂዷል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በአዋጅ ቁጥር 1207/2012 በተሰጠው ስልጣን መሠረት በስሩ የኢስላማዊ ተቋማት የምዝገባ አገልግሎት እንደሚሰጥ ይደነግጋል።
...
በዚህ መሠረት በኢስላማዊ ተግባር ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች እና ማህበራት በሙሉ ተሳታፊ የሆኑበት በጠቅላይ ምክር ቤቱ በፀደቀው የኢስላማዊ ተቋማት የምዝገባና አገልግሎት መመሪያ ደንብ ዙሪያ የትውውቅ መድረክ ጠቅላይ ምክር ቤቱ የተዘጋጀ ሲሆን ጥር 25/ 2015 ዓ.ል ከቀኑ በ8:00 ሰዓት በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መሠብሠቢያ አዳራሽ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት አመራሮች የአዲስአበባ መጅሊስ አመራሮች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም ከየድርጅቶቹ እና ከማህበራት የተወከሉ ሰዎች የውይይቱ በተገኙበት ውይይት እና ትውውቅ ተከናውኗል።
...
በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሸይኸ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ መጅሊስ ኢስላማዊ ተቋማት ከሆኑት ግብረሠናይ ድርጅቶች ጋር በሰፊው እንደሚሰራ ተናግረዋል። በሌላ በኩልም ፈቃድ የሌላቸው ኢስላማዊ ተቋማት ፈቃድ አውጥተው ጀምረውት የነበረው በጎ ስራ ማስቀጠል እንደሚችሉም ተናግረዋል። በተጨማሪም ማንኛውም ኢስላማዊ ተቋማት ያገኙት ፈቃድ ከየትም ይሁን ከየትም ከመጅሊስ ጋር ተቀራርበው መስራት እንዳለባቸው ፕሬዝዳንቱ በአፅንኦት ተናግረዋል።
...
ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.6K views13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 16:30:25
1.5K views13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 13:14:30
ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በኢትዮጵያ የሳዑዲ አረቢያ አምባሳደር ጋር ተወያዩ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ ጥር 25/2015
...
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በኢትዮጵያ የሳዉዲ አምባሳደር የሆኑትን ዶክተር ፈኻድ ቢን ዑበይዱሏህ አል ሁመይዲንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል::
...
የሳዉዲ አምባሳደሩ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በተገኙበት ወቅት ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት በተጨማሪ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ፀሃፊ ሼይኽ ሐሚድ ሙሳ ፣ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ከማል ሀሩን እና የፕሬዝዳንቱ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ሐጂ መሐመድ ነጋ ተገኝተዋል። አምባሳደሩም በቆይታቸው ከጠቅላይ ምክር ቤቱ አመራሮች ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል::
...
መረጃው የኢ/እስ/ጉ/ጠ/ም/ቤት ነው።

ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.9K views10:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-01 22:16:19
ታላቁ ዓሊም ሼይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ ለተሻለ ህክምና ከሰአታት በኃላ ወደ ቱርክ ኢስታንቡል ያቀናሉ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ ጥር 24/2015
...
ታላቁ ዓሊም ሼይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ ለህክምና ከሰአታት በኃላ ወደ ቱርክ ኢስታንቡል ያቀናሉ። ከሰሞኑ የጤና እክል ገጥሟቸው ሆስፒታል ገብተው የነበሩት ሼይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ በዛሬው እለት ለተሻለ ህክምና ወደ ቱርክ እንደሚሔዱ ለማወቅ ተችሏል። አሏህ (ሱ.ወ) በአፍያ ይመልሳቸው ዘንድ ሁላችንም በዱዓ እናስታወሳቸው ዘንድ ጥሪያችን ነው።
..
ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራ፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
2.7K views19:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-01 19:58:18
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር
ለእስላማዊ ተቋማት በሚሰጠው የምዝገባ አገልግሎት ዙሪያ የትውውቅ መድረክ ማዘጋጀቱ ተገለጸ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ ጥር 24/2015
...
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር
ለእስላማዊ ተቋማት በሚሰጠው የምዝገባ አገልግሎት ዙሪያ የትውውቅ መድረክ ማዘጋጀቱ ተገለጸ። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በአዋጅ ቁጥር 1207/2012 በተሰጠው ስልጣን መሠረት በስሩ የኢስላማዊ ተቋማት የምዝገባ አገልግሎት እንደሚሰጥ ይደነግጋል።
...
በዚህ መሠረት በኢስላማዊ ተግባር ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች እና ማህበራት በሙሉ ተሳታፊ የሚሆንበትና በጠቅላይ ምክር ቤቱ በፀደቀው የኢስላማዊ ተቋማት የምዝገባና አገልግሎት መመሪያ ደንብ ዙሪያ የትውውቅ መድረክ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ማሰናዳቱን ገልጾ ጥር 25/ 2015 ዓ.ል ከቀኑ በ8:00 ሰዓት በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መሠብሠቢያ አዳራሽ ከየድርጅቶቹ እና ከማህበራት የሚወከሉ 3 ሰዎችን በመላክ የውይይቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል።
...
ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራ፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
965 views16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-30 21:10:55 ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም እና በአሜሪካ የሚኖሩ የስልጤ ኮሚዩኒቲ የተሰራ ወፍጮ ምረቃ በሀመር || Harun special



2.1K views18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-30 12:06:45
በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የሚገኘው ዋህደቱ ኒሳዕ የሴቶች የቁርዓን ሂፍዝ ማዕከል ለህዝበ ሙስሊሙ ያቀረበው ጥሪ
...


2.8K views09:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-28 19:45:41 በኮልፌ ቀራንዮ የእሳት ቃጠሎ አደጋ የደረሰበትን መስጂድ የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮች ጉበኙ።
...
ሀሩን ሚዲያ፥ ጥር 20/2015
...
በኮልፌ ቀራንዮ ክፈለ ከተማ ወረዳ 10 በተለምዶ አባ ጃሌ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ባልታወቀ ምክኒያት መስጂድ ተቃጥሏል። ይህንኑ ተከትሎ የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ፃሃፊ ሼህ ሁሴን በሽር ቃጠሎው ወደ ተከሰተበት ስፍራ አቅንተው ጉብኝት አድርገዋል።
...
በጉብኝታቸው ወቅት የከተማው ጠቅላይ ምክር ቤት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን አፋጣኝ የመልሶ ግንባት ስራ እንደሚሰራም ገልፀዋል። የቃጠሎ ምክኒያት ለጊዜው ምን እንደሆነ ባይታወቅም ከሚመለከተው አካል ጋር በጋራ በመሆን የማጣራቱ ስራ እንደሚሰራም ተናግረዋል።
...
ቃጠሎው ዛሬ ከረፋዱ 5 ሰአት ገደማ መድረሱን የገለፁት የወረዳው እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢ አቶ አህመድ መሀመድ እኛ እንደ አካባቢ ማህበረሰብ የሚጠበቅብንን ሁሉ አድርገን መስጂዱን ወደ ነበረበት ለመመለስ እንጥራለን፣ በተጨማሪም በተሻለ መልኩ ለመገንባት ሁሉም ሙስሊም ማህበረሰብ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግልን ሲል ጥሪ አቅርበዋል።
..
ፖሊስ አካባቢው ላይ ተገኝቶ ጥብቃ እያደረገ ሲሆን እሳቱ በተነሳበት ወቅት የኮልፌ ቀራንዮ ክፈለ ከተማ እሳትና አደጋ ሰራ አመራር ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን ቃጠሎው ወደ አጎራባች አካባቢዎች እንዳይስፋፋ በማድረግ በቁጥጥር ስር እንዲውል አድርጓል። የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ፀሃፊ አደጋውን ለመቆጣጠር ርብርብ ያደረጉ አካላትን በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
...
መረጃው የአ/እስ/ጉ/ከ/ም/ቤት ነው።

ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራ፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
3.5K views16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ