Get Mystery Box with random crypto!

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ harunmedia — Harun Media - ሀሩን ሚዲያ H
የቴሌግራም ቻናል አርማ harunmedia — Harun Media - ሀሩን ሚዲያ
የሰርጥ አድራሻ: @harunmedia
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.42K

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 25

2022-07-16 12:44:28
የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግና የፌዴራል ፖሊስ የጎንደሩን ጥቃት አስመልክቶ በጥምረት በሰጡት መግለጫ ላይ ቦንብ መወርወሩን በደፈናው ገልጸዋል። የቤተ ክርስቲያኑ ጥበቃ ጥይት መተኮሱን እንዲሁም የአብነት ተማሪዎች ድንጋይ መወርወራቸውን ከጠቀሱ በኃላ ለሰዎች መሞት ምክንያት የሆነውን የቦንብ ውርወራ ግን አደባብሰውት አልፈዋል። ተግባሩንም ግልጽ ባልሆነና ባለቤቱን በማይገልጽ ቃል "ተወርውሯል" በሚል አሻሚ አገላለጽ አልፈውታል።
..
ቦንብ በመወርወርና ሙስሊሞችን በመግደል ጥቃቱን የጀመረውና ለዚያ ሁሉ ውድመት መነሻ የሆነውን አካል በግልጽ መነገር ያልተፈለገበት ምክንያት ምንድን ነው? ከዚህ ቦንብ ወርዋሪ ጀርባ ማነው ያለው? የጥቃቱ መሪ ተዋናይ ይህ አካል ሁኖ ሳለ በሪፖርቱና በመግለጫው ሆን ተብሎ የተዘለለበት ምክንያትስ ምንድን ነው? እንደ ሚዲያ አሁንም ግልጽ ይሆን ዘንድ እንጠይቃለን!
..
ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
4.2K views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 22:51:34 ታሪካዊው የበድር ጉባዔ በኢትዮጵያ የመክፈቻ ፕሮግራም ||ሃሩን ሚዲያ


4.2K views19:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 22:15:06
በፍትህ ሚንስቴር የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግና የፌዴራል ፖሊስ በጋራ በሰጡት መግለጫ የተነሱትን ነጥቦች አስመልክቶ ከጹሁፍ ካፕሽን ጋር ዳሰናቸዋል። ይከታተሉት
..
ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
4.2K views19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 18:48:53

4.2K views15:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 18:21:29 የፍትህ ሚኒስቴር ከፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጋር በመተባበር ጎንደር፣ ወራቤና ጂንካ አካባቢ የተፈጸሙ ወንጀልችን ምርመራ አድርጌያለሁ ሲል ይፋ አድርጓል።
..
ሀሩን ሚዲያ፥ ሐምሌ 8/2014
..
የፍትህ ሚኒስቴር ከፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጋር በመተባበር ጎንደር፣ ወራቤና ጂንካ አካባቢ የተፈጸሙ ወንጀልችን ምርመራ አድርጌያለሁ ሲል ይፋ አድርጓል። በፍትህ ሚንስቴር የጠቅላይ አቃቤ ህግ ሕግ ዘርፍ ሚንስቴር ዴኤታ አቶ ፍቃዱ ጸጋ እና በፌዴራል ፖሊስ በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ኦፕሬሽን መምሪያ ሀላፊ የሆኑት አቶ ሙልኢሳ አብዱሳ በጋራ በመሆን ነው መግለጫውን የሰጡት
..
በመግለጫቸው በጎንደር ሙስሊሞች፣ የሙስሊም ንብረቶችና መስጅዶች ላይ የተፈጸመውን ጥቃት "ግጭት" በሚል ቃል የገለጹት ሲሆን መነሻውም ተራ የድንጋይ ጠብ ነው ሲሉ ደምድውታል። ከግጭቱ በፊት የነበሩ የጥላቻ ቅስቀሳዎችና የጎዳና ላይ ኢፍጣር ሊደረግ በመታሰቡ ሳቢያ የነበረውን የጥቃት ሒደት በሙሉ እንዳልነበረ በሚመስል መልኩ ሪፖርቱ ላይ ያልተካተተ ሲሆን የግጭቱ ምክንያት ድንጋይ ብቻ መሆኑ ተገልጿል።
..
በተቃራኒው በወራቤ የነበረውን ክስተት ግን "ግጭት" በሚል ከመጥራት ይልቅ በተቀናበረ መልኩ የተካሔደ ጉዳት ማድረስ አድርገው አቅርበውታል። ጉዳት አድራሾችንም ከጎንደሩ ጥቃት አድራሻች በተለየ መልኩ "ጽንፈኛ ሀይሎች" ሲሉ ገልጸዋቸዋል። ከዚህም በተጨማሪ በሀይማኖት መምህራን ሳይቀር ቅስቀሳ ተደርጓል በሚልም ተነግሯል። ሪፖርት አቅራቢው ሚንስቴር ዴኤታም ስለቤተ ክርስቲያን መቃጠሉ ሲገልጹ ስሜታዊ ሁነው ታይተዋል።
..
በጎንደር በተፈጸመው ጥቃት ሳቢያ የጎንደር ሙስሊም ከተማው እየለቀቀ የሚገኝ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን አሁን ድረስ ደህንነታቸው አደጋ ላይ በመሆኑ ሳቢያ ከቀናት በፊት የተከበረው የኢድ አል አድሀ በአልም ቤታቸው እንዲያሳልፉ የዞኑ መጅሊስ መግለጹ ይታወሳል።
..
ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
4.5K views15:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 18:21:25
3.9K views15:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ