Get Mystery Box with random crypto!

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ harunmedia — Harun Media - ሀሩን ሚዲያ H
የቴሌግራም ቻናል አርማ harunmedia — Harun Media - ሀሩን ሚዲያ
የሰርጥ አድራሻ: @harunmedia
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.42K

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 24

2022-07-21 18:39:31
አዲሱ የመጅሊስ አመራር በአስቸኳይ ቢሰራቸው በሚል በጋዜጠኛ ኢስሀቅ እሸቱ የቀረቡ 11 ምክረ ሀሳቦችን ሀሩን ሚዲያ ለአድማጮች በሚመች መልኩ ወደ ድምጽ ቀይሯቸዋል። ከዚህ በታች ባለው ሊንክ መመልከት ይችላሉ፦
..


2.5K views15:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 11:31:23 መቀመጫውን በጀርመን ፍራንክፈርት ያደረገው አል-ኑር የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ማኅበር የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥና አንድነት ሁለተኛው ዙር አገር አቀፍ ጉባኤን በማስመልከት የደስታና የምስጋና መግለጫ አውጥቷል።
.
ሀሩን ሚዲያ፥ ሐምሌ 14/2014
.
መቀመጫውን በጀርመን ፍራንክፈርት ያደረገው አል-ኑር የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ማኅበር የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥና አንድነት ሁለተኛው ዙር አገር አቀፍ ጉባኤን በማስመልከት የደስታና የምስጋና መግለጫ አውጥቷል። ከሁሉም በላይ በአላህ ሱ.ወ. ፈቃድና እርዳታ በመቀጠልም በህዝበ ሙስሊሙ ትእግስትና ጥረት፣ በሰላም ወዳድ ኢትዮጵያውያን እና ጉዳዮ በሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ድጋፍ የዘመናት ጥያቄ የሆነው የጠንካራ ተቋም ባለቤትነት ጥያቄ እልባት እንዲያገኝ የተጀመረው ሂደት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሐምሌ 11 ቀን 2014 የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥና አንድነት ሁለተኛውን ዙር አገር አቀፍ ጉባኤ በማካሄድ የምክር ቤቱን የጠቅላላ ጉባኤ እና የሥራ አስፈፃሚ አባላትን በመምረጥ የጠቅላይ ምክር ቤቱን አመራሮች በመሰየም የምርጫ ሂደቱ በሰላም ተጠናቋል። ከትውልድ ትውልድ ሲሸጋገር የቆየው ይህ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የመጂሊስ ባለቤትነት ጥያቄ ለዚህ ታላቅ ስኬት በመድረሱ አል-ኑር በጀርመን ፍራንክፈርትና አካባቢው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ማኅበር የተሰማውን ደስታ ገልጿል።
..
አል -ኑር ለቀጣይ ሶስት አመታት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት በመሆን ለተመረጡት ሸኽ ሐጅ ኢብራሂም እና ለምክትል ኘሬዝዳንት ሸኽ አብዱል ከሪም በድረዲን እንዲሁም ባልደረቦቻቸው ሁሉ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክቱን የገለጸ ሲሆን መጪዉ የስራ ዘመናቸው መልካም የአገልግሎት ዘመንና የተሳካ እንዲሆንላቸው፣ ሙስሊሙን ማኅበረሰብ አንድ አድርገው ካሉብን ውስብስብ ችግሮች ወጥቶ በሀገሩ በሁሉም ዘርፍ ቀጥታ ተሳታፊ እንዲሆን የበኩላቸውን እንዲጥሩና፣ አላህም እንዲረዳቸው ተመኝቶ በሚቻለው አቅም ሁሉ ማኅበሩ ትብብሩ እንዳማይለያቸው ገልጿል።
..
ሙስሊሙ ማኅበረሰብም አንድነቱን በመጠበቅ በቀጣይ ከአዲሱ አመራር ጋር በመሆን መሪ ተቋሙን እንዲያጠናክርና ጠንካራ ኢስላማዊ ተቋም በመመስረት ሂደት ላይ እንዲያግዝና የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ መልዕክቱን አስተላልፏል።
..
ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.3K views08:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 11:31:19
1.2K views08:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 11:28:35 በሰሜን አሜሪካ ሲያትል የሚገኘው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ማኅበር (ኢማስ) የሙስሊሙ የመጅሊስ ጥያቄ ምላሽ ማግኘቱን በማስመልከት የእንኳን ደስ አላችሁ መግለጫ አውጥቷል።
.
ሀሩን ሚዲያ፥ ሐምሌ 13/2014
.
በሰሜን አሜሪካ ሲያትል የሚገኘው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ማኅበር (ኢማስ) የሙስሊሙ የመጅሊስ ጥያቄ ምላሽ ማግኘቱን በማስመልከት የእንኳን ደስ አላችሁ መግለጫ አውጥቷል። የኢትዮጲያን ሙስሊሞች የዘመናት ጥያቄዎች ከነበሩት አንዱ የሆነው መጅሊስ በህዝብ በተመረጡ አካላት ይመራ የሚለው መልስ በማግኘቱ የእንኳን ደስ አላችሁ ብሏል ኢማስ በመግለጫው።
.
የአትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሐምሌ 11 ቀን 2014 ኢትዮጵያን ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥና አንድነት ሁለተኛው ዙር አገር አቀፍ ጉባኤ በማካሄድ ለቀጣይ ሶስት አመታት የሚያገለግሉ የምክር ቤቱን የጠቅላላ ጉባኤ እና የሥራ አስፈፃሚ አባላትን በመምረጥ የጠቅላይ ምክር ቤቱን አመራሮች በመሠየም የምርጫ ሂደቱ በሰላም ማጠናቀቁን በመግለፁ ከፍተኛ ደስታ የተሰማቸው መሆኑንም በመግለጫዝ ጠቅሰዋል።
.
የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት በመሆን ለተመረጡት ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋና ምክትል ሆነው ለተመረጡት ሸኽ አብዱል ከሪም ሸይኽ በድረዲን እንዲሁም ለሁሉም ባልደረቦቻቸው በሙሉ በተሰጣቸው ለሶስት ዓመት የሚቆይ ኃላፊነት ብዙ ስራ የሚጠበቅባቸው መሆኑን ገልጸው ሙስሊሙን አንድ በማድረግ ማህበረሰቡን እና ሃገሪቱን የሚጠቅም ስራ እንዲሰሩ እንዲሁም ጠንካራ ተቋማዊ አሰራርን ገንብተው ለቀጣይ ትውልድ እንዲያስርክቡ ማህበሩ አሳስቦ መልካም ምኞቱን ገልጿል።
..
የጉባኤው አባላት የመረጣቸው የሥራ አስፈፃሚዎች ቢሮ ተረክበው ሥራ መጀመራቸው አድንቀው በመንግስትም በኩል እስካሁን ለጉባኤው መሳካት እንዳሳየው ትግስት የተሞላበት የፀጥታ ማስከበር ኃላፊነቱን በቀጣይም ከህጋዊ የመጅሊሱ አመራሮች ጎን በመቆም አጠናክሮ እንዲቀጥልና ማንኛውንም አስፈላጊ ትብብር እንዲያደርግላቸውም በትህትና ጠይቀዋል።
.
ሕዝበ ሙስሊሙም በቀጣይ ከአዲሱ አመራር ጋር በመሆን መሪ ተቋሙን እንዲያጠናክርና የህዝበ ሙስሊሙ የረጅም ጊዜ ህልምና ጥያቄ የሆነውን ጠንካራ ኢስላማዊ ተቋም በመመስረት ላይ እንዲያግዝ አሳስበው ኮሚኒቲያቸውም ጠቅላይ ምክር ቤቱ እንዲጠናከርና አንድነቱን ጠብቆ እንዲቀጥል ሁሌም በተፈለገበት ጉዳይ አብሮ የሚሠራ መሆኑን ገልጸው የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
..
ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.3K views08:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 11:28:31
1.3K views08:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 10:10:07
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የአትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ያካሔደውን ምርጫ አስመልክቶ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቱን ገለጸ።
.
ሀሩን ሚዲያ፥ ሐምሌ 12/2014
.
በትላንትናው ዕለት ሐምሌ 11 ቀን 2014 የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለወጥና አንድነት ሁለተኛው ዙር አገር አቀፍ ጉባኤ በማካሄድ የምክር ቤቱን የጠቅላላ ጉባኤ እና የሥራ አስፈፃሚ አባላትን በመምረጥ የጠቅላይ ምክር ቤቱን አመራሮች በመሠየም የምርጫ ሂደቱ በሰላም በመጠናቀቁ ጉባኤው የተሰማውን ልባዊ ደስታ ገልጿል።
..
የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት በመሆን ለተመረጡት ሸኽ ሐጅ ኢብራሂም እና ባልደረቦቻቸው በሙሉ መልካምና የተባረከ የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንላቸው የተመኘ ሲሆን በተመሳሳይ ላለፉት 3 ዓመታት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት በመሆን ያገለገሉትን ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር እድሪስ እና ባልደረቦቻቸው ለሰጡት አመራር ጉባኤያችን ምስጋናውን አቅርቧል።
..
ሕዝበ ሙስሊሙም በቀጣይ ከአዲሱ አመራር ጋር በመሆን መሪ ተቋሙን እንዲያጠናክር የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ያሳሰበ ሲሆን ጠቅላይ ምክር ቤቱ እንዲጠናከር አብሮ የሚሠራ መሆኑን ጉባኤው አሳውቋል።
..
ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
2.2K views07:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-18 17:17:10
3.7K views14:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-18 15:17:48
3.9K views12:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 15:56:29 የፌዴራል አቃቤ ህግና የፌዴራል ፖሊስ በጥምረት አጣርተነዋል ባሉት የጎንደሩ ጥቃት ዙሪያ የሚከተለውን ድምዳሜ አቅርበዋል፦
..
❝ግጭቱ ባህሪው ቀድሞ ታስቦበት ያልነበረ በቀብር ስነ-ስርዓቱ ላይ የተፈጠረ ነገር ግን የሰፋ፤ የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታዮች የእስልምና ዕምነት ተከታዮችን የማምለኪያ ቦታ እና የንግድ እንዲሁም የመኖሪያ ቤቶችን በመምረጥ ጉዳት በማድረስ፤ የእስልምና ዕምነት ተከታዮችም ደግሞ በአጸፋው የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታዮች የንግድ ቦታ ላይ ጉዳት አድርሰዋል❞
..
ይህንን በተመለከተ የሚከተሉትን ጥያቄዎች እንደ ሚዲያ ለታሪክ ይሆን ዘንድ እንጠይቃለን፦
..
1/ የጎንደር ከተማ እስልምና ጉዳዩች ም/ቤት በጎንደር የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ ባዘጋጀው ሪፖርት ገጽ 2 ጀምሮ ጥቃቱ በአንድ ጀንበር በድንገት የተፈጠረ ሳይሆን በተለይም ከ2010 ጀምሮ ዘመቻ ሲደረግበት የነበረ እንደሆነ በመዘርዘር ስጋቶችን ለሚመለከተው አካል ጭምር በተደጋጋሚ ሪፖርት ማድረጉን ገልጿል። በዚህ መልኩ የነበረውን ስጋት ሁሉ ችላ ባለ መልኩ ጥምር መርማሪ ቡድኑ "ቀድሞ የታሰበበት አልነበረም" ሲል የመረጃና የምርመራ ምንጩ ምንን መሠረት ያደረገ ነበር? የአካባቢውን ሙስሊምና የከተማውን ወይንም የዞኑን መጅሊስ ሀሳብና ማስረጃዎች እንዴት ሳያካትትና ምርመራ ሳያደርግ ሊደመድም ቻለ?
..
2/ ጥቃቱ ከመፈጸሙ ከአንድ አመት ጀምሮ በተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት በኩል የማኅበረ ቅዱሳን መዋቅሮች "የጎንደር ከተማ በሙስሊሞች ተወረረ" የሚል አደገኛ ስልጠናዎችን ለአብነት ተማሪዎችና ለዩንቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ሲሰጡ እንደነበር በዚህ ሚዲያ ሳይቀር የተገለጸ ሲሆን የስልጠና ማንዋል ፓወር ፖይንቱም ሳይቀር እጃችን ገብቶ በተከታታይ ፕሮግራም የሰራንበት ጉዳይ ነበር። ከሁለት አመት በፊት በሚዲያችን የተሰራውን ፕሮግራም በዚህ ሊንክ መከታተል ይቻላል፦




ይህ ስልጠና በባለቤቶቹ ሳይቀር የሚታወቅና ማስተባበያ እንኳን ያልተሰጠበት ሁኖ ሳለ ጥምር መርማሪ ቡድኑ ግን ምንም ጥቃቱን ሊፈጥር የሚችል ሞቲቭ ከዚያ በፊት እንዳልነበረ ሲገልጽ እነዚህን መረጃዎች ሳይደርሱት ቀርተው ነው ወይንስ ምክንያቱ ምንድን ነው?
..
3/ በማኅበራዊ ሚዲያ በማስተማር የሚታወቁና በጎንደር የሚኖሩ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ሳይቀር እጅግ አደገኛ መልዕክት ያለምንም ሀፍረት በማኅበራዊ ሚዲያ ሲያስተላልፉ መቆየታቸው ይታወሳል። ከእነዚህ ግለሰቦች መካከል የሆነው መምህር ዮርዳኖስ የተባለ በጎንደር የሚኖር ግለሰብ በግልጽ "ጉልበታችንን አንድ ቀን ታዩታላችሁ" የሚል መልዕክት ሳይቀር ሲያስተላልፍ እንደነበር ይታወሳል። የግለሰቡን ንግግር በዚህ ሊንክ ያገኙታል፦
https://t.me/harunmedia/655
መሠል ቅስቀሳዎች በከተማዋ በስፋት ሲሰራጩ እንደነበር በተደጋጋሚ የተገለጸ ሲሆን በጥምር መርማሪ ቡድኑ ሪፖርት ውስጥ ግን ምንም ነገር እንዳልነበር እንዴት ሊገለጽ ቻለ?
..
ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
5.0K views12:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 15:56:24
3.9K views12:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ