Get Mystery Box with random crypto!

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ harunmedia — Harun Media - ሀሩን ሚዲያ H
የቴሌግራም ቻናል አርማ harunmedia — Harun Media - ሀሩን ሚዲያ
የሰርጥ አድራሻ: @harunmedia
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.42K

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-01-28 19:45:36
3.0K views16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-28 19:45:17 የኮልፌ መካነ መቃብር የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እንቅስቃሴ ላይ መሆኑ ተገለጸ ።
...
ሀሩን ሚዲያ፥ ጥር 20/2015
...
የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የመካነ መቃብር ይዞታዎችን በተገቢው ለማስተዳደር ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል። በከተማው የሚገኙት የዘላቂ ማረፊያዎች ለሙስሊሙ ማህበረሰብ የሚሰጡትን አገልግሎት ለማሻሻል ጠቅላይ ምክር ቤቱ ባለፉት ሶስት ወራት ይህንን ጉዳይ ብቻ የሚከውኑ አምስት አባላት ያቀፈ ኮሚቴ በማዋቀር ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል።
...
በዛሬውም እለት የአ/አ/ከ/እ/ጉ/ጠ/ም/ቤት የምክር ቤት አባልና የፕሬዝዳንት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ካሊድ መሀመድ ፣ የም/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ሪያድ ጀማልን ጨምሮ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ እ/ጉ/ከ/ም/ቤት ዋና ስራ አስፈፃሚ ኡስታዝ ባህሩ ተማም እና ዋና ፀሀፊ ኡስታዝ አንዋር ሱልጣን ተገኝተው ኮሚቴው በአጭር ጊዜ ያከናወናቸውን ተግባራት ተመልክተዋል።
...
ለተቋቋመው ኮሚቴ ምክር ቤቱ ስራ አስኪያጅ በመመደብ የተጠናከረ ስራ እንዲከናወን አድርጎል። ኮሚቴው ከተዋቀረ ጀምሮ በከተማው የሚገኙ የመካነ መቃብር ስፍራዎችን በመመልከት ያሉበትን ተጨባጭ በመገምገም ያሉባቸውን ችግሮች በመለየት የመፍትሔ ሀሳቦች የማፈላለግ ተግባራትን አከናውኗል። ኮሚቴው በእቅስቃሴውም ከፍተኛ አገልግሎት ለአዲስ አበባ ህዝበ ሙስሊም እየሰጠ የሚገኝውን ኮልፌ መካነ መቃብር ለማሻሻል የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል።
...
የኮልፌ መካነ መቃብር ከዚህ ቀደም ያለወን ቦታ ጥበትን ፣ የአጠቃቀም ችግር ፣የቀብር ጉድጎድ ቁፋሮ ወጥነት አለመኖር፣በበቂ መልኩ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል በእኩል ያለ ማስተናገድ ተግባራት ሲከናወኑ እንደነበር እና በአሁኑ ጊዜ መሰል ችግሮች እየተቀረፉ እንደሆነ በመስክ ጉብኝቱ ወቅት የኮሚቴው አመራሮች ይፋ አድርገዋል።
...
ከዚህ በተጨማሪ በኮልፌ መካነ መቃብር የህዝብ መገልገያ የሆኑ መፀዳጃ ቤቶች፣ መታጠቢያ ቤቶች፣ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎችና ሌሎች መሰረታዊ የሚባሉ ግንባታዎች መሰራታቸውንም ኮሚቴው አብራርቷል።
...
የኮልፌ መካነ መቃብር አስተዳደርና የፋይናስ ክፍል ሃላፊው አቶ ዳውድ መሀመድ በመካነ መቃብሩ ዙሪያ ለቀብር አፈፃፀም ሥራው የመሬት ይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጥን በሚመለከት ችግር መኖሩን አንስተዋል።
...
የመቃብር ይዞታ የሆኑ ቦታዎችም እየተሸራረፉ መሆናቸውን ሌላኛው የዘላቂ ማረፊያ አስተዳደር የሆኑት አቶ አብዱረህማን ጁሃር ገልፀዋል። ይህንን የተገነዘበው የከተማው እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መሠል ችግሮችን ለመቅረፍና የተሻለ የመካነ መቃብር አስተዳደር እንዲኖር በዋናነት ኮልፌን መነሻ አድርጎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
...
ኮልፌ ለዚህ ስራ ሲመረጥ ስፍራው ከታሪካዊነቱ ባለፈ ሌሎች ተመሳሳይ መካነ መቃብሮች በዚህ መልኩ ማደራጀት እንዲቻል ታስቦ መሆኑን የመካነ መቃብሩ አስተዳደር አቶ መሀመድ ዘይን ተናግረዋል። በውይይትና ጉብኝቱ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሪያድ ጀማል ቦታው ላይ ተገኝተን ያለውን ዕውነታ መመልከታችን ችግሮችን በጥልቀት እንድንረዳ አድርጎናል ብለዋል።
...
ምክር ቤቱ በመካነ መቃብር አስተዳደሩ የተነሱትንና በጉብኝቱ ወቅት የተገነዘቡትን ችግሮች ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራም ገልፀዋል። በተጨማሪም ከመንግስትና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በተለያየ መልኩ ግንኙነት በማድረግ ያለውን ችግር ለመፍታት ይሰራል ያሉት አቶ ሪያድ እስካሁን የተሰሩ ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው ጥበቃ የሚደረግበት ሁኔታ ይመቻቻል ብለዋል።
...
መረጃው የአ/እስ/ጉ/ከ/ም/ቤት ነው።

ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራ፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
3.1K views16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-28 19:45:14
2.7K views16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 20:56:28 በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሱሉልታ ወረዳ ቃሶ ወሰርቢ ልዩ ስሙ እንጦጦ ፓርክ አካባቢ የሚገኝ የሙስሊም መቃብር ቦታ ያለ አግባብ ለግለሰብ በመሰጠቱ ውዝግብ ማስነሳቱ ተገለጸ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ ጥር 19/2015
...
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሱሉልታ ወረዳ ቃሶ ወሰርቢ ልዩ ስሙ እንጦጦ ፓርክ አካባቢ የሚገኝ የሙስሊም መቃብር ቦታ ያለ አግባብ ለግለሰብ በመሰጠቱ ውዝግብ ማስነሳቱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ። ቦታውን ሙስሊሞች የተረከቡት 1890 ዓ/ል ሲሆን ቦታው ከጥንት ጀምረው የወርጂ ኦሮሞ አባቶችና መሻኢሆች (ኡለሞች) የተቀበሩበት መሆኑን ገልጸዋል።

የእነዚህ አባቶች መካነ መቃብር አሁን ደረስ ሳይፈርስ በመካነ መቃብሩ በርካታ መቃብሮች እንደሚገኙ የገለጹት የአካባቢው ነዋሪዎች በቅርቡ ግን በ2012 ዓ/ል አንድ በመካነ መቃብሩ አቅራቢያ የሚገኝ ግለሰብ መካነ መቃብሩን በመድፈር በምሽት ጭለማን ተገን በማድረግ በለሊት 4800 የችግኝ ጉድጓድ በመቆፈር የባህር ዛፍ ችግኝ መትከሉን ገልጸዋል።
...
በቆፈረው ጉድጓድ ላይ ችግኝ እንዳይተክል ይታገድልን በሚል የአካባቢው ሙስሊም ማኅበረሰብ ለሱሉልታ ፍርድ ቤት አመልክተው ታግዶ የነበረ ቢሆንም የፍርድ ቤቱን እግድ በመጣስ ግን ችግኝ እንደተከለበት ነዋሪዎች ይገልጻሉ።
...
ከ125 አመት በላይ ያስቆጠረና ሳይት ፕላን እና ካርታ ያለውን መካነ መቃብር የህግ አካላት ምንም የይዞታ ማረጋገጫ ለሌለው አንድ ግለሰብ በመስጠት ትልቅ በደል እንደፈጸሙባቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። ይህ የልብ ልብ የሰጠው ግለሰቡ የሞተም ሰው እዛ አይቀበርም በማለት መከልከሉንና ጀናዛ እየመለሰ እንደሚገኝ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።
...
ከዚህም በተጨማሪ የሱሉልታ ወረዳ እስልምና ጉዳዮች የወከሏቸው ኮሚቴዎችን በራሱ ግብረ አበሮች አማካኝነት ከፍተኛ የሆነ ድብደባ መፈጸሙን በተለይ አንድ ወንድም በድብደባው ምክንያት የአካል ጉዳት እንደገጠመው ለማወቅ ችለናል። ይህንን ጉዳይ የሚመለከተው አካል ተገቢውን ትኩረት እንዲሰጠውና ተጨማሪ ቀውሶች ሳይፈጠሩ ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ የአካባቢው ሰዎች ተማጽነዋል።
..
ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራ፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
3.6K views17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 20:56:27
3.4K views17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 22:40:18
የሀድያው ጥቃት በማን ተፈጸመ? የአካባቢው ነዋሪዎች የሰጡንን መረጃ እንደሚከተለው ወደናንተ አቅርበናል፦
..


3.8K views19:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-24 23:18:22 የሀድያ ሙስሊሞችን ጉዳይ ለመከታተል በፌዴራል መጅሊስ የተወከለው የልዑካን ቡድን የሰራቸውን ስራዎችና የአካባቢው ተጎጂዎች ያቀረቡትን ስሞታ በተመለከተ በዝርዝር ሀሩን ሚዲያ በቦታው ተገኝቶ አሰናድቶታል። የመሰናዶውን ሙሉ ይዘት በሚከተለው ሊንክ እንዲከታተሉ ጋበዝን፦



5.0K views20:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-24 11:20:04
በጅማ ከተማ ሙኒር መስጊድ ለ42 ዓመታት በሙአዚንነት ያገለገሉት ሼህ ካሚል አህመድ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ወደ ማይቀረው ቀጣይ ዓለም ተሻግረዋል።

እኛ የአላህ ነን፤ ወደርሱም ተመላሾች ነን
..
ሀሩን ሚዲያ፥ ጥር 16/2015
..
በጅማ ከተማ ሙኒር መስጊድ ለ42 ዓመታት በሙአዚንነት ያገለገሉት ሼህ ካሚል አህመድ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ወደ ማይቀረው ቀጣይ ዓለም ተሻግረዋል። ሀሩን ሚዲያ በ"ጀዛከሏህ" ፕሮግራሙ ካመሰገናቸው ባለውለታዎቻችን መካከል ሸይኽ ካሚል አንዱ ነበሩ።
..
ሸይኽ ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር የሆኑት የወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል አባት ናቸው። ለሸይኻችን አሏህ (ሱ.ወ) ይዘንላቸው፤ ለሙፈሪሀት ካሚልና መላው ቤተሰቦቻቸውም አላህ መጽናናቱን ይስጣቸው።
..
በአንድ ወቅት ሀሩን ሚዲያ በ"ጀዛከሏህ" ፕሮግራሙ ከሸይኽ ካሚል ጋር ያደረገውን ቆይታ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ መመልከት ይችላሉ፦




ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራ፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
5.3K viewsedited  08:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-18 10:46:59
የሀረሪ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት 2ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የአንድ መቶ ሚሊዮን ብር በጀት በማፅደቅ ተጠናቀቀ።
...
ሀሩን ሚዲያ፥ ጥር 10/2015
...
በሀርላ ሆቴል ሲካሄድ የነበረው የሀረሪ ክልላዊ መንግስት እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት 2ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ አንድ መቶ ሚሊዮን ብር አመታዊ በጀት በማፅደቅ ተጠናቋል። በጉባዔው ረቂቅ የክልሉ መጅሊስ ሕግ ቀርቦ በጉባዔው አባላት ሰፊ ውይይት ተደርጎበት የፀደቀ ሲሆን በቀጣይም የክልሉ መጅሊስ ሕግ ሆኖ ያገለግላል ።
..
ጉባዔው የሶስት የኦዲትና ቁጥጥር አባትን ሹመት ያፀደቀ ሲሆን በተጨማሪ የሀረሪ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤትን እንዲያገለግሉ ለሀጂ መሀመድ ሀሺም ፣ ለአባገዳ አህመድ ዩሱፍ ፣ ለሀጂ ነስረዲን አሊ ፣ ለሼይኽ መሀመድ ቃዲ እና ለሀጂ አህመድ ኢብሮሽ የግልግል ሸንጎ አባትን ሹመት አፅድቋል።
...
የሀረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የእስልምና ምክር ቤቱን ስራ ዘመኑን የዋጀ እንዲሆን እና የክልሉን ሙስሊም ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ 11 አባላት ያሉት የአማካሪዎች ቦርድ አባላትን ማለትም፦

1ኛ.አቶ ተወለዳ አብዶሽ
2ኛ.አቶ ያሲን አብዱላሂ
3ኛ.ዶ/ር አብዱላሂ ወዚር
4ኛ. ኡስታዝ ረመዳን ተማም
5ኛ.አቶ ሀምዛ ሽመልስ
6ኛ.አቶ መሀመድ አብዱረህማን
7ኛ. ሼህ አብዱረህማን መሀመድ
8ኛ. አቶ ሙስጠፋ መሀመድ
9ኛ.አቶ ፊላ አህመድ
10ኛ.ሼህ አልዪ መሀመድ
11ኛ.ሼህ ጀማል መሀመድን በመምረጥ ጉባዔውን አጠናቋል።

መረጃው የኢ/እስ/ጉ/ጠ/ም/ቤት ነው።

ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.2K views07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 19:26:20 ከሰሞኑ ሙስሊሞች ላይ ጥቃት በደረሰበት የሀድያ ዞን ጭንጎ ወረዳ ታላቅ ኮንፈረንስ በዛሬው እለት መካሔዱ ተገለጸ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ ጥር 9/2015
...
❐ በኮንፈረሱ ከ4,000 እስከ 5,000 የሚሆን ሰው ተገኝተዋል ተብሎ ይገመታል።

❐ ከክልል እስከ ወረዳ ድረስ ያሉ የመንግስት መስሪያ ቤትችን የሚወክሉ ልዑካንም ጉዳቱን ለመታዘብ በቦታው ተገኝተው ነበር።

❐ ሀሩን ሚዲያ ክስተቱን ከመነሻው ጀምሮ የተከታተለ ሲሆን ሙሉውን ፕሮግራም ወደናንተ የሚያደርስ ይሆናል።

ከሰሞኑ ሙስሊሞች ላይ ጥቃት በደረሰበት የሀድያ ዞን ጭንጎ ወረዳ ታላቅ ኮንፈረንስ በዛሬው እለት መካሔዱ ተገለጸ። ጉዳዩን በተመለከተ የፌዴራል መጅሊስ ልዑካን ቡድን አባላት በቦታው በመገኘት ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን በዛሬው እለት በቦታው ታላቅ ኮንፈረንስ በማካሔድ ከህዝቡ ጋር ውይይት አድርገዋል። በውይይቱም ህዝቡ የደረሰበትን በደልና ግፍ ለልዑካን ቡድኑ እና ለመንግስት አካላት የገለጸ ሲሆን አጥፊዎቹ ላይ ተመጣጣኝ እርምጃ እንዲወሰድም ጠይቋል።
...
በኮንፈረንሱ ከመንግስት በኩል የተገኙ የዞኑ ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ ሳምኤል ሽጉጤ፣
የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ፣ የክልሉ ፀጥታ ቢሮ የግጭት አፈታት ባለሙያ እንዲሁም የወረዳው ፀጥታ ሀላፊ የተገኙ ሲሆን በመጅሊስ በኩል ከፌዴራል መጅሊስ ልዑካን በተጨማሪ የክልሉ እስልምና ጉዳይ ከፍተኛ ም/ቤት፣ የዞኑ መጅሊስ ሰብሳቢና ስራ አስፈፃሚወች እንዲሁም የሀገር ሸማግሌዎች ተገኝተዋል።
...
በውይይቱ ላይ የተገኙት የመንግስት ኃላፊዎች አስፈላጊውን ማጣራት ከተደረገ በኋላ በአጥፊዎቹ ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ የገለጹ ሲሆን የክልሉ እና የዞኑ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች የሀይማኖት ጉባኤ ተወካዮች የፌደራል እና የክልል መጅሊስ ተወካዮች የሚያደረጉት ውይይት እስከ ነገ እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል። በውይይታቸው መጨረሻ በጋራ መግለጫ እንደሚሰጡ ለሀሩን ሚዲያ ገልጸዋል።
...
ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራ፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.5K views16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ