2023-03-20 21:37:31
ከ19 ነጥብ 2ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጣ የዕርዳታ ቁሳቁስ ከአዲስ አበባ መጅሊስ ወደ ቦረና ተጓጓዘ።
...
ሀሩን ሚዲያ፥ መጋቢት 11/2015
..
የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከነዋሪዎች ያሰባሰበውን እና ለቦረናና አጎራባች አካባቢዎቹ የድርቅ ተጎጂዎች ያዘጋጀውን ምግብ እና መጠጦች የሽኝት ሥነ ሥርዓት አከናውኗል። በሽኝት ስነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮች፤ የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሱልጣን አማን፣ ምክትል ፕሬዝዳንት ሼህ ፈትሁዲን ሐጂ ዘይኑ፣ ዋና ፀሐፊው ሼህ ሁሴን በሽር እና ሌሎችም አመራሮች ተገኝተዋል።
...
በዚህ ወቅት ፕሬዝደንቱ ሼህ ሱልጣን አማን እንዳሉት ይህ ድጋፍ በዚህ የተወደደው ወርሃ ረመዷን ዋዜማ ላይ ያጋጠመውና በርካቶች ምላሽ የሰጡበት የቦረናው ችግርም በወሩ ውስጥ ለምንተገብረው በጎ ሥራ እንደ ምሳሌ ሊመራን የሚችል ተግባር ነው። ይህ ችግር በወገኖቻችን ላይ መድረሱ በታወቀ ግዜ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በአንድነት መንፈስ ተንቀሳቅሰው ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ ካሉ በኋላ የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤትም ለዚህ ችግር ምላሽ ከሰጡ ተቋማት መካከል አንዱ መሆኑን አስታውሰዋል።
..
የከተማዋ ሙስሊሞች ደግሞ ቀዳሚውን ሚና በመወጣታቸው አመስግነው ሙስሊምች ይህንን ለማድረግ ሐይማኖታዊ ትዕዛዙ የሚያስገድዳቸው ሲሆን በተባረከው የረመዷን ወር ምክንያት የተጎናፀፉት የመረዳዳት እሴት የሰጣቸው የደግነት ልብ ትልቁን ሚና ይወጣል ሲሉ በቀጣይም ተባባሪነታቸው እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
...
በሽኝት መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው መረዳዳት ከእስልምና መርሆዎች አንዱ በመሆኑ እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ የዛሬውም ተግባር የሚያስመሰግንና በቀጣይም የሚጠበቅ ሥራ መሆኑን አንስተዋል።
የከተማው መጅሊስ ለድጋፍ ካዘጋጀው የዓይነት ድጋፍ ውስጥ ዱቄት፣ መኮሮኒ፣ ሩዝ፣ ዘይት፣ ውሃ፣ የተለያዩ ጭማቂዎች፣ ተምር፣ የእንስሳት መኖና ሌሎችም መካተታቸው ታውቋል። በሽኝቱ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፤ የኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት፣ የሰበታ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት፣ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የአደጋ ስጋት መከላከል የአዲስ አበባ ከተማ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራሮችና ሌሎችም ተገኝተዋል።
...
ለድጋፍ መርሃ ግብሩ አሰባሰብ አስተዋፅኦ ላደረጉ የበጎ አድራጎት ተቋማት፤ የክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትና ሌሎች ተባባሪዎች የዕውቅና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
...
መረጃው የአ/እስ/ጉ/ከ/ም/ቤት ነው።
...
ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.2K views18:37