Get Mystery Box with random crypto!

Harun Media - ሀሩን ሚዲያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ harunmedia — Harun Media - ሀሩን ሚዲያ H
የቴሌግራም ቻናል አርማ harunmedia — Harun Media - ሀሩን ሚዲያ
የሰርጥ አድራሻ: @harunmedia
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.42K

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-03-19 13:32:11 ዱዓቶች ተቀናጅተው ማህበረሰቡን እንዲያስተምሩ ተጠየቀ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ መጋቢት 9/15
..
በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዳዕዋ ስራን የተቀናጀ ለማድረግ ከዱዓቶች ጋር የትውውቅና የምክክር መድረክ በጠቅላይ ምክር ቤቱ የመሠብሰቢያ አዳራሽ ተካሄደ። በምክክር መድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ ዑለማዎች የነብያት ወራሾች በመሆናቸው ዑማውን ዕለት ከዕለት በተቀናጀ መልኩ የማስተማር ኃላፊነት እንዳለባቸው አስታውሰው እስካሁን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትሉ ምንዳውን ከአሏህ ብቻ በመፈለግ ሕብረተሰባችንን በማስተማራችሁ በዚህችኛዋ አለም ስኬት በዛችኛዋ አለም ደግሞ ጀነትን እንዲወፍቃቸው ምኞታቸውን ገልፀዋል።
...
ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው ማጠናቀቂያ ላይ አንደተናገሩት "ከቀናት በኋላ ትልቅ ዕንግዳን እንቀበላለን ለዚህ ለተከበረው ወር በመድረሳችንን ፈጣሪያችንን አሏህ ሰ.ወ እናመሠግናለን " ብለዋል። ሁላችንም ሰዎች በመሆናችንን መሳሳታችን የማይቀር በመሆኑ በስራ ሂደት የተቀየማችሁኝ "እኔን አውፍ እንድትሉኝ። ዑማውም አውፍ እንዲለኝ መልዕክት አስተላልፉልኝ" ብለዋል
...
የጠቅላይ ምክር ቤቱ ስራ አስፈፃሚ አባል ሼይኽ አሚን ኢብሮ የዳዕዋ ስራ የጠቅላይ ምክር ቤቱ የጀርባ አጥንት ስራ በመሆኑ ዱዓቶች በመቀናጀት ዑማውን ከመቼውም በተሻለ መልኩ ዲናዊ ትምህርት መስጠት ይገባል ብለዋል። በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በዛሬው በተደረገው የትውውቅና የምክክር መድረክ ላይ በዶክተር ጀይላን ኸድርና በዶክተር ሙሐመድ ሐሚዲን ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።
...
ይህ መሰሉ የምክክር መድረክ በጠቅላይ ምክር ቤቱ መደረጉን የውውይቱ ተሳታፊ የሆኑት ዱዓቶች አመስግነው በቀጣይ መሰል ውይይቶች በስፋት መቀጠል እንደሚኖርበት አሳስበዋል። በምክክር መድረኩ ላይ ከክልልና ከተማ አስተዳደር የመጡ ታዋቂ ዱዓቶች ተገኝተውበታል።
...
ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.7K views10:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 13:32:11
1.6K views10:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 13:23:58
አሱና የኢስላማዊ ዕውቀትና የዐረብኛ ቋንቋ ማዕከል(መዕሀደ ሱና) በአቅሷ ቅርንጫፍ በመሰናዶ ት/ት ዘርፍ ለሦሥት ዓመት ሲያስተምራቸው የቆዩ መሻይኾችን በታላቅ ድምቀት አስመረቀ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ መጋቢት 10/2015
...
አሱና የኢስላማዊ ዕውቀትና የዐረብኛ ቋንቋ ማዕከል(መዕሀደ ሱና) በአቅሷ ቅርንጫፍ በመሰናዶ ት/ት ዘርፍ ለሦሥት ዓመት ሲያስተምራቸው የቆዩ መሻይኾችን በታላቅ ድምቀት በዛሬው እለት አስመርቋል።
...
በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይም ተጋባዥ እንግዶችና፣ ኡለሞችና ዱዓቶች ተገኝተዋል።
...
ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.6K views10:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 12:55:27 የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በርካታ ዑለሞችና ዱዓቶች በደሴ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል
...
ሀሩን ሚዲያ፥ መጋቢት 7/2015
...
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በርካታ ዑለሞችና ዱዓቶች በደሴ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። እንግዶቹንም የደሴ ከተማ ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ፣ የደሴ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሞላ ሁሴን ፣ የክልል እና የደሴ ከተማ መጅሊስ አመራሮች በተገኙበት በደሴ ኮምቦልቻ አየር መንገድ ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል ።
...
ፕሮግራሙን በተመለከተ ሀሩን ሚዲያ በቅርበት እየተከታተለ ሲሆን ዝርዝር መረጃዎችን ወደናንተ የሚያደርስ ይሆናል።
...
ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.4K views09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-16 12:55:27
1.4K views09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 12:23:19
የጠቅላይ ምክር ቤቱ አገር አቀፍ የቁርዓን ውድድር ተጀመረ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ መጋቢት 6/2015
..
በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መሠብሰቢያ አደራሽ አገር አቀፍ የቁርዓን ውድድር እየተካሄደ ይገኛል። ፕሮግራሙን በቁርዓን ቃሪዕ ሙከሚል ከማል አብደላ ከፍቶታል።
...
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ሸይኽ ሐሚድ ሙሳ ዛሬ በሚደገው አገራዊ የቁርዓን ውድድር መክፈቻ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር የማድረግ እድል አላህ ሱ.ዉ ስለሰጣቸው ምስጋናቸውን ገልፀዋል።
...
ጠቅላይ ምክር ቤቱ ይህንን መሰል የቁርዓን ውድድር ስኬት የበኩሉን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። ለዛሬ የቁርዓን ተወዳዳሪዎች እዚህ መድረስ ድጋፍ ላደረጉ ወላጆች፣ መሻይዒኾችና መድረሳዎች ምስጋናቸው አቅርበዋል።
...
በዛሬዉ 2015/1444 የአገር አቀፍ የቁርዓን ውድድር ላይ ሰላሳ ተወዳዳሪዎች ብርቱ ውድድር የሚያደርጉ ሲሆን አሸናፊዉ በዱባይ በሚካሔደው አለም አቀፉ የቁርዓን ውድድር ላይ ኢትዮጵያ ወክሎ ይወዳደራል።
...
መረጃው የኢ/እስ/ጉ/ጠ/ም/ቤት ነው።

ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
2.1K views09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 21:09:27 ቢላሉል ሐበሺ ቀደም ሲል ለተረከበው ሰላም ዳለቲ ት/ቤት የምስጋና ፕሮግራም አደረገ፡፡
...
ሀሩን ሚዲያ፥ መጋቢት 5/2015
...
አቶ መሐመድ እንድሪስ ለሀገራቸው በርካታ ድንቅ ታሪካዊ አሻራ ጥለው ያለፉ ታላቅ ሰው ሲሆኑ የዳለቲ አካባቢን ህብረተሰብ ችግር በመረዳት በ2003 የዳለቲ ሰላም አንደኛ ደረጃ ት/ቤትን መስርተው ለ9 አመታት ከአካባቢው ማህበረሰብና ከመምህራን ጋር በመሆን አገልግለዋል፡፡ አቶ መሐመድ ት/ቤት ከመገንባት ባሻገር የተለያዩ መስጂዶችን በገጠር አካባቢ ገንብተዋል፣ የውሃ ጉድጓዶችን በማውጣት፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ የፖሊዮ ክትባት ስራ በመስራት ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጋር በመሆን አስተዋፅኦ አበርክተዋል፡፡
...
የኚህ ታላቅ ሰው ባለቤት ወ/ሮ ሃሊማ ሙሳና ቤተሰቦቻቸው የሰላም ዳለቲ ት/ቤትን ቀደም ሲል ለቢላሉል ሐበሺ ወቅፍ በማድረጋቸው የቢላሉል ሐበሺ የቦርድ አባላቶችና የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም የትምህርት ቤቱ መምህራን፣ የተማሪ ወላጆችና የአካባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት የምስጋና ፕሮግራም ተደርጓል፡፡ 
...
ቢላሊል ሐበሺም የአቶ መሐመድ እንድሪስን ረዕይ ለማሳካት የተረከበውን ት/ቤት በተቻለ መጠን አጠናክሮና ጥራቱን ጠብቆ ውጤታማ ለማድረግና ማህበረሰቡን ለመጥቀም ተግቶ ይሰራል፡፡ በዚሁ ፕሮግራም ላይ የቢላሉል ሐበሺ የቦርድ አባል የሆኑት አቶ ሙስጠፋ መሐመድ እንደተናገሩት “አንድ ሰው መልካም ስራ ሰርቶ ካለፈ በኋላ በዚህ መንገድ በጥሩነት ሲወሳ በሰዎች መወሳቱ ብቻ ሳይሆን ነገ ደግሞ በዕለተ ትንሳኤ ይሄ መልካም ስራ ሳይቋረጥበት መሄድ መቻሉ ይሄ ትልቅ መታደል ነው፣ ይህም ከአላህ መሰጠትን ይፈልጋል” ብለዋል። ዘገባው የቢላሉል ሀበሽ ነው።
...
ሀሩን ሚዲያ
___
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
2.4K views18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 21:09:25
2.2K views18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 13:40:52
የ2015/1444 አሂ የሃጅ መስተንግዶ በተሻለ መልኩ ለመስጠት ከክልልና ከተማ አስተዳደር የመጂሊስ የስራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ተደረገ
...
ሀሩን ሚዲያ፥ መጋቢት 4/2015
...
ጠቅላይ ምክር ቤቱ የ2015/1444 የተከበሩ የአሏህ እንግዶች(ሁጃጆች) መስተንግዶ ቀልጣፋ ለማድረግ የተለያዪ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ ከከተማ አስተዳደር ና ክልል የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የስራ ኃላፊዎች ጋር ዉይይት ተደረገ።
...
የዘንድሮ የሐጅ መስተንግዶ ዘመኑን በዋጀ በአይ ሲቲ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የሚከናወን ሲሆን የሁጃጆችን አንግልት ለመቀነስ መስተንግዶው በየክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤቶች አማካኝነት የሚከናወኑ ሲሆን የክልል መጅሊሶች ስራቸውን ለማሳለጥ ተጨማሪ ቅርንጫፎችን እንደሚከፍቱ ታውቋል።
...
ሰፊ ቁጥር የአሏህ እንግዶች( ሁጃጆች) ተመዝጋቢ የሌላቸው ክልሎች ወደ አጎራባች ክልል እስልምና ጉዳዮች በመሄድ መስተንግዶ እንዲያገኙ አሰራሮች መዘርጋታቸውን በውይይቱ ተገልጿል።
...
ለዘንድሮ የሐጅ ተጓዦች ጉዞ ከማድረገቸው በፊት በሐጅ ስርዓት( መናሲከል ሐጅ) ዙሪያ በዑለሞች ስልጠና እንደሚሰጣቸው ተገልጿል። በዘንድሮ አመት ሐጅ ለማድረግ ዕቅድ ያላቸው ቀድመው የጉዞ ሰነዳቸውን ( ፓስፖርታቸውን) ከወዲሁ ዝግጁ እንዲያደረጉ ተጠይቋል።
...
የዘንድሮ የሐጅ ጉዞ መስተንግዶ ክፍያ ከውጪ የገንዘቦች ምንዛሪ አኳያ የተወሰነ ጨማሪ እንደሚኖረው የታወቀ ሲሆን ከቀናት በኃላ ይፋ እንደሚደረግ ታውቋል።
...
መረጃው የኢ/እስ/ጉ/ጠ/ም/ቤት ነው።
___________
በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.2K views10:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 20:40:37 ጉዞ ወደ ኢስላም! የቀድሞው የካቶሊክ ቄስ ለ20 አመት የተደረገ ከባድ ትግል || Harun media


1.9K views17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ