Get Mystery Box with random crypto!

ወርቃማ ንግግሮች

የቴሌግራም ቻናል አርማ golden_speech — ወርቃማ ንግግሮች
የቴሌግራም ቻናል አርማ golden_speech — ወርቃማ ንግግሮች
የሰርጥ አድራሻ: @golden_speech
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.15K
የሰርጥ መግለጫ

ሰው የለበስክ ሰው እንጂ ልብስ የለበስክ ሰው አትሁን.. ሰውነት የአለም ምርጡ ጌጥህ እሱ ነውና።
አስተያየት እንቀበላለን.. @Golden_SpeechBot
https://youtube.com/channel/UCgP-E0miz3BhJ0YAGJ2zCHg

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-06-24 03:05:12

~ ሰዓትህን አስተካክል


ዉድድሩ ከመጀመሩ በፊት ሁሉም ተወዳዳሪ ሰዓቱን እንዲያዘጋጅ ያስፈልጋል። ለግዜ ትልቅ ትኩረት መስጠት ግድ ይለዋል እያንዳንዷ ደቂቃ ብሎም ሰከንድ እሽቅድድም ትልቅ ዋጋ አላት የምንኖራት ትንሽም ጊዜ ላይ የአሸናፊነት ተአብ አርግዘናል።

ምናልባትም በአንድ ሰከንድ ልዩነት ውድድሩን ልትሸነፍ ትችላለህ. . ምንም ዓይነት ሰዓት ያለ ጥቅም አታጥፋ መፀፀት በማይጠቅምበት የቂያም እለት ከከፍተኛ ፀፀት ትድን ዘንድ።


“ሰዎችንም ቅጣቱ የሚመጣባቸውን ቀን አስፈራራቸው። እነዚያም የበደሉት “ጌታችን ሆይ! ወደ ቅርብ ጊዜ ድረስ አቆየን። ጥሪህን እንቀበላለንና
መልዕክተኞቹንም እንከተላለና” ይላሉ” (ኢብራሂም 44)

~ የቅጽበት ዋጋ

በቅጽበት ዋጋ ጉዞው ተራዘመ፣ መዳረሻው ርቆት በጅጉ አዘገመ፣ የተሠካችን ሾህ ለመንቀል ሲላፋ፣ ቅፍለት ተሰወረ ካይኑ ርቆ ጠፋ።


የዚህ ግጥም መነሻ ታሪክ እንዲህ ነው..

“አንድ ሠው ጭው ባለ በረሃ በባዶ እግሩ እየሄደ ነበር ፤ የሚሄድበትን አቅጣቱጫ አያውቅም መንገዱ ጠፍቶበት ዋልሏል ከሩቅ ርቀት አንድ ቅፍለት ተመለከተ የመዳን ተስፋዉን ቅፍለቱ ላይ አደረገ በባዶ እግሩ እየተቻኮለ ይሮጥ ጀመር በአይኑ ቅፍለቱን እየተከተለ ሩጫዉን ቀጥሏል በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ ላይ ባለበት እግሩ ላይ እሾህ ይሰካበታል

እሾሁን ከእግሩ ለመንቀል ለቅጽበት ያህል ዓይኑን ከቅፍለቱ ነቀለ። ከቅፅበት በኋላ ቀና ብሎ ሲመለከት ተስፋ የጣለበት ቅፍለት ከዕይታው ተሰወረ።

በቅጽበትዋ እየተፀፀተ ሞተ።"

ወንድሜ ሆይ! ባለ ታሪኩ ዐይኑን ወደ እሾሁ በመመለስ ያሳለፋት ቅጽበት ህይወቱ ላይ ያደረሰችዉን ተፅዕኖ አስተውል። ቅፍለቱ ከዓይኑ ተሰውሯል። ጊዜያችንን በሙሉ የዱንያን እሾሆች በመመልከት ስለተጠመድን ሰዎች ምን ትላለህ? ምን ያህል ሕይወታችን ይባክን ይሆን?!

እንዲህ ዓይነቱ ሰው የቂያማ ዕለት ጀነት ከዕይታው ትሰወራለች።
አላህ ይጠብቀን ከምንጠቀምበት ያድርገን ያ ረብ!
2.2K views00:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-22 22:38:59
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] በጧት እና በማታ ተከታዩን ዱዓ ማድረግ አይተዉም ነበር: ‐
«አላህ ሆይ! ነውሬን ሸፍንልኝ። ከሚያስፈራኝ ነገር አማን አድርገኝ። ከፊትለፊቴም፣ ከኋላዬም፣ ከቀኜም፣ ከግራዬም ከበላዬም ከሚመጣ [አደጋ] ጠብቀኝ። ከበታቼ በኩል ከሚመጣ አደጋም በልቅናህ እጠበቃለሁ።»
አሕመድ እና አቡዳዉድ ዘግበውታል።
:
ነፍሳችንንም ሆነ ቤተሰባችንን በዱዐና በዚክር ጥላ ሥር እናድርግ!
2.0K views19:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-22 07:39:36
ዛሬ ላይ ብዙ ሀብቶች የሀሳብ፣ የጭንቀትና የሰላም ማጣት ምንጭ ሆነዋል፤ ሰው ዉድ መኪና ይዞ ወጥቶ እንዳይሰረቅብኝ የት ላቁም ብሎ ይብሰለሰላል፣ ስለ ደህንነቷ ይጨነቃል፡፡
ሞላም ጎደለ ዱንያ ላይ እንከን የሌለው ነገር የለም፡፡ ካለህ ብዙ አትፈንጥዝ፤ ከሌለህም ብዙ አትተክዝ፡፡
ጠንክረህ ሥራ። አላህን የሰው እጅ ከማየት የሚጠብቅህን ያህል ሪዝቅ ለምነው፤ ጤናን ለምነው፡፡
ሆስፒታል ከሚተኙበት የስፖንጅ ፍራሽ ይልቅ እቤት የሚተኙበት የገለባ ፍራሽ ምርጥ ነው፤ ታመህ ትንፋሽህ ከሚያጥር ሪዝቅህ ቢያጥር ይሻላል፡፡

ወዳጄ! ያለህበት ሁኔታ የቱን ያህል ቢከፋም ካንተ በባሰ ሁኔታ ዉስጥ ያለ ሰው መኖሩን ላፍታም ቢሆን እንዳትዘነጋ፡፡ ከሁሉም በላይ በአላህ ተደሰት፡፡ እሱን ካለህ አህያህን ቆስቁሰህ ዉጣ፡፡ መንገድ ላይ የምታገኘዉን ሁሉ በሙሉ ፈገግታ ሰባሐል ኸይር በል።

ሰባሐል ኸይር

ይለናል ውዱ መካሪያችን መሀመድ ሰኢድ Abx
5.1K views04:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-21 02:23:40 "ብር ወይስ ጊዜ ሚሰጣችሁን ባል ነው ምትወዱት።" ተብለው ተጠየቁ አሉ ሴቶች።

ብር በጊዜ ሚሰጠንን ብለው መለሱ።
ABX
2.2K views23:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-21 01:32:22
~


الحج أشهر معلومات فمن فرض فيهن الحج فلا رفث ولا فسوق ولا جدال في الحج وما تفعلوا من خير يعلمه الله وتزودوا فإن خير الزاد التقوى واتقون يا أولي الألباب


ሐጅ (ጊዜያቱ) የታወቁ ወሮች ናቸው፡፡ በእነርሱም ውስጥ ሐጅን (እንዲሠራ) ነፍሱን ያስገደደ ሰው በሐጅ ውስጥ ሴትን መገናኘት ማመጽም ክርክርም የለም፡፡ ከበጎም ሥራ የምትሠሩትን ሁሉ አላህ ያውቀዋል፡፡ ተሰነቁም፤ ከስንቅም ሁሉ በላጩ ጥንቃቄ (አላህን መፍራት) ነው፡፡ የአእምሮዎችም ባለቤቶች ሆይ! ፍሩኝ፡፡

~ [ አል-በቀራህ - 197 ] ~
2.1K viewsedited  22:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-21 01:03:22 ሳይወለድ የሞተው ነብይ ማነበር?!
1.6K views22:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-20 01:07:07 ኸሊፋው ዑመር (ረዐ) አንድ ቀን ሰዎችን ሰበሰበ። ወደ ሚንበሩም ወጣና እንዲህ አለ፦

«እኔ በጃሂሊያ ዘመን ለአዳዴዎቼ ፍየል አግድላቸው ነበር።እፍኝ ተምርን ወይም ዘቢብን ይከፍሉኝ ነበር። ለቀናት እርሷን አየተመገብኩ የምቆይ ሰው ነበርኩ።»

ብሎ ንግግሩን ጨርሶ ከሚንበሩ ከወረደ በኋላ ዐብዱረሕማን ኢብኑ ዐውፍ (ረዐ) ፦ «ያ አሚረል ሙእሚኒን! ራስህን ከማቃለል ውጭ ምንም አልጨመርክም!»አለው።

ዑመርም አለው ፦ « የዐውፍ ልጅ ሆይ! ወየውልህ! ለብቻዬ ስሆን ነፍሴ የሙእሚኖች መሪና የረሱል ኸሊፋ መሆኔን ነገረችኝ ፤ ስርአት ላሲዛት ፈልጌ ነው!» (አጥጦበቃቱል ኩብራ 3/293)

አላህ ዑመርን ስራውን ይውደድለት፤በጀነትም ከርሱ ጋር ያጎራብተን!

ነፍስያ እንዲህ ነች፤ መቀጣት ያስፈልጋታል።

ቤትህ ስትገባ «አንተኮ የኡማው መከታ ነህ!» «ኡስታዝ ነህ!» «ለኡማው ተሰቃይተህ»፣ «ሀይላንድ ተንጠልጥሎብህ»፣ «አንተ የጀነት ሙሽራ»፣ «በቁስልህ ኡማው ተፈወሰ!» ፣ «የሙስሊሙ ተቆርቋሪ»፣ «ባለ ራእይ አክቲቪስት» ትልሀለች። በዚህ ሰአት የዑመርን መድሀኒት መጠቀም ፍቱን ነው።

ወጣ ብለህ ለሰዎች «እኔኮ ሊስትሮ እየሰራሁ ያደግኩና የቀን ስራ እየሰራሁ ጉርሴን ስለቅም የነበርኩ ሰው ነኝ» ማለት ግድ ይላል።

እኔም በፃፍኩት እናንተም ባነበባችሁት ተጠቃሚዎች ያድርገን!
2.1K views22:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-20 00:15:30 በጎንደር ከተማ ጥቃት የደረሰባቸውን ሙስሊሞች የሚያቋቁመው ኮሚቴ በሚጠበቅበት መጠን እንዳልተንቀሳቀሰ ተገለጸ

ሃሩን ሚዲያ ሰኔ 9/2015

በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ በ2014 ሚያዝያ ወር ጥቃት የደረሰባቸውን ሙስሊሞች ለማቋቋም የተመሠረተው ኮሚቴ በሚጠበቅበት መጠን እንዳልተንቀሳቀሰ የገለፀው የጎንደር ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ነው።

ምክር ቤቱ ለኮሚቴው በላከው ማብራሪያ ላይ በጎንደር ከተማ ከሚያዝያ 18-21/2014 በተሰነዘረው ሀይማኖትን መሰረት ያደረገ ከፍተኛ ጥቃት ጉዳት የደረስባቸውን ሰዎች መልሶ ለማቋቋም የጎንደር ከተማ አስተዳደር 13 አባላት ያለው ኮሚቴ በማዋቀር ወደ ስራ እንደተገባ አስታውሷል።

ይኸው ኮሚቴ ግንቦት 29/2015 ለጎ//ከ/እስ/ጉ/ም/ቤት ባደረገው ጥሪ መሠረት በከተማው ከንቲባ ጽ/ቤት ቢሮ በተደረገ ውይይት ላይ ከአንድ አመት በላይ የነበረውን እንቅስቃሴ ሪፓርት አቅርቧል። በዚህ ሪፓርት ላይ ተጎጅዎችን ቤታቸው በመሄድ ከመጎብኘት ጀምሮ መልሶ ለማቋቋም የሚሆን ገንዘብ ለማሰባሰብ ከፍተኛ ጥረት እንደተደረገ የተጠቀሰ ሲሆን፣ ከጎንደር ከተማ ነዋሪዎች 2,097,077 (ሁለት ሚሊዮን ዘጠና ሰባት ሺህ ሰባ ሰባት ብር) እንደሰበሰበ ተገልጿል።

በዚህ ሪፖርት ላይ በከተማው በተሰነዘረው ሀይማኖትን መሰረት ያደረገ ጥቃት ተገድለው በኃይማኖት ሥነ-ሥርዓት የተቀበሩ ሰዎች 20፣ ማዘጋጃ ቤት የተቀበሩ ሰዎች 10፣ ከባድና ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች 500፣ ቤት ቃጠሎ የመኖሪያ ቤቶች ከፍተኛ ቃጠሎ ያስተናገዱ ሰዎች 150 ሲሆኑ፤ የንብረት ውድመት የደረሰባቸው ከ150 በላይ የንግድ ድርጅቶች ሱቆች፣ የተቃጠሉ የሞተር ብስክሌት፣ ባጃጅ እና መኪና ከ130 በላይ እንዲሁም 2 መስጂዶች ሲወድሙ፣ 13 መስጅዶች ከባድና ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው ተዘርዝሯል።

የጉዳቱ መጠን ይህ መሆኑ እየታወቀ መልሶ ለማቋቋም የተሰየመው ኮሚቴ ከአንድ አመት በላይ ከቆየ በኋላ የቀረበው ሪፖርት ለተቋቋመለት አላማ ትኩረት ሰጥቶ በሚጠብቀው ልክ እንዳልተንቀሳቀስ ኮሚቴው ሰበሰብኩት ያለው ገንዘብ ተጨባጭ ማሳያ ነዉ ሲል ም/ቤቱ አስታውቋል። ስለሆነም የተሰበሰበዉ የገንዘብ መጠን ከደረሰው ከፍተኛ ውድመት አንፃር ሲነፃፀር ፈፅሞ የማይመጣጠንና ጎንደርንም የማይመጥን ነው ብሎታል።

ምክር ቤቱ በማብራሪያው አሁንም በከተማው በጥቃቱ ምክንያት የሞቱና ከባድና ቀላል ጉዳት የደረሰባቸዉን ቤተሰቦች መልሰው እንዲቋቋሙ፣ የተጎዱ እና የተቃጠሉ መስጊዶች እንዲሰሩና እንዲታደሱ፣ ንብረታቸው ሙሉ ለሙሉ እና በከፊል ሀብት ንብረት የተዘረፈባቸው ግለሰቦች መልሰው እንዲቋቋሙ፣ በነበረውን ግርግር ያለ አግባብ የታሰሩ14 ሙስሊሞች የተፋጠነ ፍትህ እንዲያገኙ እንዲደረግ ሲል ጠይቋል።

ሀሩን ሚዲያ

በቴሌግራም፥ https://t.me/harunmedia
በዩቲዩብ ፥ http://bit.ly/3MXs17j
1.8K views21:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 18:50:01 የጅብ ልጅ ሞት ! ተረት = ረት
==========
ጅብ ልጅ ይሞትበትና ለአንኩዮ አህይት ልጄ ሞቷልና አላቅሱኝ ሲል መርዶ ነጋሪ ላከ ።

ተረጂዎቹም እንግዲህ ሰምተን ብንቀር ይጣላናል ብንሄድም ይበላናል እንዴት ብናደርግ ይሻለናል ብለው ምክር ጀመሩ ። ነገር ግን ቀርተን ከሚጣላን ሄደን ቢበላን ይሻላል ብለው ተነስተው ልብሳቸውን አሸራርጠው ሄዱ ።
ከለቅሶው ቦታ እንደደረሱ አንድኛዋ ብድግ አለችና

ምን አጥንት ቢሆን ይሰበራል ጥረረስዎ
ምን ጨለማ ቢሆን እሾክ አይውጋዎ
ምን ጥቁር ቢበሉ ነጭ ነው ክስዎ
ያንን ጎራ ዞሮ ይሰማል ድምጥዎ
አሁን የርሶዎ ልጅ ምን አገኘብዎ
እያለች ሙሾ ታወርድ ጀመር
እሱም ቀበል አለና …
አንቺስ ደግ ብለሻል
መልካም አልቅሰሻል
ይህ ሁሉ አዘንተኛ ምን ይብላ ብለሻል ።
ሲል መለሰላት
እንዳልማራቸው ባወቁ ግዜ እንግዲህ አለቀቀንም ምን ማድረግ ይሻለናል ብለው እነእንኩዮ አህይት ምክር ጀመሩ ።
አንዲት እናቷ የሞተችባት ውርጭላ ከነርሱ ጋር ነበረችና ይቺን እንስጥና እንገላገል ብለው ሲነጋገሩ ግልገሏ አህያ ሰምታ ምነው እኔ ውርጭላ ማን ይዞኝ በሩጫ ብላ ብላ ተነስታ ትታቸው በሩጫ እልም አለች ።
ከዚህ ቡሃላ ጭንቀት ያዛቸውና መቼስ ምን ይደረግ ብለው ለምቦጫችንን ሰጥተው እንሂድ ብለው ተማከሩ ወዲያ በል እንግዲህ የላይ የላይ ለንቦጫችንን ውሰድ አሉት እሱም እንዳመላከቱት ለምቦጭ ለምቦጫቸውን ገነጣጠለና ለቀቃቸው ።
በሶስተኛው ቀን ደግሞ እስቲ ዛሬ ሳልስቱ ነው ና መቃብሩ ላይ ደርሰን አያ ጅቦ ጠይቀን እንምጣ ብለው ቢሄዱ አያ ጅቦ ቀደሞ ከመቃብሩ ላይ ሲያለቅስ ደረሱ ።

አያ ጅቦም ድዳቸውን ገልፍጠው ባየ ግዜ ለካ ለኔ ሀዘን ለናንተ ሰርግና ምላሽ ሆኖላችሃልና የኔ ልጅ ትናንት ሞቶ ዛሬ እናንተ እየሳቃችሁ የመጣችሁት በምን ምክንያት ነው ብሎ ተቆጣና ለወገኖቹ እረ በሉ እያንዳንዷን እየዘረጠጣችሁ ጣሉልኝ አላቸው ።
ከዚህ ቡሃላ የጅብ ወገን የአህያን ልጅ እየገነጣጠለ ጣለ ይባላል ።
☞ ባለጋራን ቆቅ ሆነው ካልጠበቁት ምንም ቢለማመጡት ማጥቃቱን አይተውም ።
☞ አንድነት ሀይል ነው ።
አያ ጅቦም ሳታማህኝ ብላ የተባለው ለዚህ ነበር ።
፥ ብዙ መልእክቶችን እንዳስተላለፈ ተስፋ አለኝ!
2.2K views15:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 22:17:18
~ ወዱዱዮ

ወንጀል እየሰራሁ እሱን እያመፅኩት።
አጥፍቻለሁ ብየ ምህረት ከጠየኩት።
በእግሬ ተንበርክኬ ከልብ ከለመንኩት።

"እልፍ" ሀጢያት ቢኖረኝ እሱ ይቅር ይለኛል።
"እኔ"እያመፅኩት በመሀሪነቱ አዝኖ ያኖረኛል።

1.1K views19:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ