Get Mystery Box with random crypto!

ወርቃማ ንግግሮች

የቴሌግራም ቻናል አርማ golden_speech — ወርቃማ ንግግሮች
የቴሌግራም ቻናል አርማ golden_speech — ወርቃማ ንግግሮች
የሰርጥ አድራሻ: @golden_speech
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.15K
የሰርጥ መግለጫ

ሰው የለበስክ ሰው እንጂ ልብስ የለበስክ ሰው አትሁን.. ሰውነት የአለም ምርጡ ጌጥህ እሱ ነውና።
አስተያየት እንቀበላለን.. @Golden_SpeechBot
https://youtube.com/channel/UCgP-E0miz3BhJ0YAGJ2zCHg

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-01-29 05:56:00 የመቅሩርና የመስሩር ታሪክ


ክፍል አስራ አምስት


የመቅሩር የቀብር ውስጥ ምርመራ


የቀብር ውስጥ መርማሪ መላእክት መቅሩር ከተኛበት የቀብር ስፍራ እንዲነሳና አንዲቀመጥ አዘዙት። እዚህ ላይ የመቅሩር ሰውነት በአብዛኛው በእሳት የተቃጠለ ቢሆንም አሁን ግን ሙሉ አካሉ እንደነበር እንዲሆን ተደርጓል መቅሩርም በሁለት መላእክት መካከል መሆኑን ሲያይ ፍርሃትና መገረም አንድ ላይ ሆነው አስጨንቀውታል ከህልውና ውጭ ሆኖ ከቆየ በኋላ ተመልሶ የመነሳቱ ምስጢር እስካሁን ግልጽ አልሆነለትም።


ባለፉት ጥቂት ሰዓታት በእርሱ ላይ ምን እንደተፈጠረ ለማሰላሰል ሞከረ በመጀመሪያ በሚነድ እሳት ውስጥ እንደነበረና እሳቱ ግን እንዳላቃጠለው አስታወሰ ከዚያ በኋላ በእሳቱ መካከል የሞትን መልአክ እንደተመለከተውና ፍርሃት እንዳያድርበት በተስፋ እንዳበሰረው ትዝ አለው የእሳቱ ወላፈን ገና ገረፍ ሊያደርገው ሲጀምር ህሊናውን ሳተ እነሆ አሁን ደግሞ ወደ ህሊናው ተመልሶ በሁለት መላእክት መካከል ሆኖ መልስ እየሰጠ ይገኛል።


እርሱም “እናንተ እነማን ናችሁ? በማለት ጠየቃቸው
እኛ መርማሪ መላእክት ነን ሲል አንዱ መልስ ሰጠው
መቅሩር በድንጋጤ እንደማንቀጥቀጥ አደረገው:: ከዚያም እንዲህ ሲል ጥያቄ አቀረበ የፍርዱ ቀን ደረሰ እንዴ?

"አልደረሰም የፍርዱ ቀን ገና ነው አሁን ያለኸው በመቃብርህ ውስጥ ነው:: እኛ አሁን የምንጠይቅህ ሶስት ጥያቄዎች ብቻ ነው። ጌታህ ማን ነው? እለ አንዱ መልአክ……


መቅሩርም ሲመልስ ጌታዬ አላህ ነው እርሱም የሁሉም ነገር ፈጣሪ ነው " አለ


ለመሆኑ ኃይማኖትህ ምንድን ነው?


እኔ ሙስሊም ነኝ የምከተለውም የነቢያት ሁሉ ኃይማኖት
የሆነውን ራስን ለአላህ የማስገዛት መንገድ ነው አለ መቅሩር።


በአንድ ወቅት ወደ ምስራቅ / ሄደህ ስላገኘኸው ነቢይ ምን
ትላለህ? በእርሱስ ታምናለህ?


መቅሩር እንዴታ በሚገባ እንጂ አለ።


አላህ በእርግጥ መልዕክተኛው አድርጐ መርጦታል ብለህ ታምናለህን? አለ መልአኩ…

በሚገባ አንደኛው መልአክ ወደ መቅሩር ቀረብ ብሎ ተመልከት ወደ ፊት ለፊትህ ያለውን አለው
መቅሩር እንደታዘዘው ወደፊት ለፊቱ ሲመለከት ዓይኑ እስኪታክት ድረስ ማለቂያ የሌለው አረንጓዴ መናፈሻና በአበቦች አፀድ የታጀበ ቤተ መንግስት እንዲሁም ከዚህ በፊት ዐይቶት የማያወቅ ብዙ ውብ ነገር አስተዋለ
ከዚያም በአድናቆት እንደተሞላ ወደ መልአኩ ፊቱን መልሶ “ይህ ምንድን ነው? ሲል ጠየቀው…


“ይህማ መኖሪያህ የሆነው ጀነት ነው ሲል መልአኩ መለሰለት እደሰማ መቅሩር አልነበረውም።

ይህን ወሰን ደስታው መልአኩንም ጌታዬ አላህ ፀፀቴን ተቀብሎኛል ማለት ነው? ሲል ጠየቀው ከሁለቱ አንዳቸውም ለዚህ ጥያቄው መልስ አልሰጡትም። አንዱ መልአክ ወስኗል አለው "አላህ ወደ ነበርክበት ሞት እንድትመለስ ከዚያ በኋላ መላእክቶቹን ከማግኘቱ በፊት ወደ ነበረበት የተቃጠለ አመድነት ለመለወጥ እንደገና ህሊናውን ሳተ…


ይቀጥላል…
1.1K views02:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 10:25:20 ~ የጀሀነሙ መስሩርና የጀነቱ መቅሩር


~ ክፍል አስራ አራት


~ የመስሩር ስቃይ በመቃብር


መቅሩርም ሆነ መስሩር ከሞቱ በኋላ ህዋሳቶቻቸውን ገድሎ በድን አድርጓቸዋል ሁለቱም ሰዎች ፍፁም አዲስና የተለየ ዓለም ውስጥ ነው የገቡት፡፡ ሆኖም ልክ መቃብር ውስጥ እንደገቡ ስሜቶቻቸው ሙሉ በሙሉ ተመልሶላቸዋል። ሁለቱም ሰዎች በተመሳሳይ ጊዜ ህያው የነበሩና በተቀራራቢ ሰዓትም ሞትን የቀመሱ እንደመሆኑ በስሜቶቻቸው እየተፈራረቀ ያለው ለውጥ ለጊዜው ተመሳሳይ ነው፡፡ ልዩነቱ ከሁለቱ አንዱ እንደሞተና ከዚያም ተመልሶ በሕይወት እንደሚቀሰቀስ በሚገባ የተገነዘበ መሆኑ ነው።


መስሩር ባጋጠመውና እየተፈፀመ ባለው ነገር በጣም ተደንቋል። ባላሰበውና ባልገመተው ሁኔታ በሞት መዳፎች ተጨምድዶ አሁን ላለበት ሁኔታ በቅቷል። በሕይወት እያለ ሞት ሁሉንም ስሜቶቹን ገድሎ እስከወዲያኛው በዚያው የሚቀር ነበር የሚመስለው፡፡ አሁን ግን ጉዳዩ የተገላቢጦሽ መሆኑን ተገንዝቧል። ያ ድሮ ያስበው የነበረው ነገር በሀቅ ላይ ያልተመሠረተ እንደነበር ከማወቁም በላይ ስሜቶቹ በሙሉ በሕይወት ከነበረበት ጊዜ የበለጠ እጥፍ ድርብ ሆነው ነው ያገኛቸው አንድ ሙት የሆነ ሰው ዓይን ሳይኖረው ነገሮችን ሊመለከት እንደሚችልና ያለ ስሜት ህዋሳቶች ሁሉንም ነገር እንደሚገነዘብ ግልጽ ሆኖለታል።


መስሩር ይህን ሁሉ ነገር እያሰበ ባለበት ቅጽበት የመቃብሩ ግድግዳዎች ፍፁም ሊቋቋመው በማይችለው ሁኔታ አጣብቀው ያስጨንቁት ጀመር። በዚህ ጊዜ አስፈሪ በሆነ ድምፅ ጮኸ። ሆኖም ማንም ያንን ድምፅ ሰምቶ የሚደርስለት ሰው አልነበረም። በመቃብሩ ዙርያ ሳር የሚበሉ እንስሳትና ወፎች በሰሙት ድምጽ በመደንገጣቸው እንደመደንበር አሉ ፈጽሞ ባልጠበቀው ሁኔታም ሁለት አስፈሪ መላእክት ወደ መቃብሩ ውስጥ ገብተው ከእርሱ ጋር ተፋጠጠ የተገነዘበትን ጨርቅ ገፈው ቁጭ እንዲል ካደረጉት በኋላ ከመላእክቱ አንዱ እንዲህ ሲል ጠየቀው
መስሩር በዚህ ጥያቄ በጣም ተገረመ።


መልአኩ ሌላ ጥያቄ አስከተለ ኃይማኖትህ ምንድን ነው?


ነቢይህስ ማን ይባላል?

በእርግጥ መስሩር እነዚህን ጥያቄዎች መመለስ የሚችል አልነበረም። በዚህ ጉዳይ ላይ ምንም ዓይነት ዕውቀት የሌለው ከመሆኑም በላይ ያጋጠመው አስደንጋጭ ነገር በሙሉ ምላሱን እንዳይንቀሳቀስ ለጉሞታል። ከሁለቱ መላአክቶች አንደኛው ወደ እርሱ ቀረብ ብሎ እየጠቆመ ወደ አንድ አቅጣጫ ያሳየዋል። መስሩር እንደታዘዘው ሲመለከት ከፍተኛ የሆነ በቃላት ሊገለጽ የማይችል ነዲድ እሳት ተመለከተ ያ የተጋጋመ ቦታ ያሳደረበት ፍርሃት እውነቱን ለመናገር ደሙ በሰውነቱ ውስጥ የረጋ እስኪመስለው ድረስ ነው ያደነዘዘው


“ይህ ምንድን ነው?

በማለት የሞት ሞቱን ያሳየውን መልአክ ጠየቀው…
ይህማ ኢቃጥሉና በነበለባል ልሶ የሚያሰቃየው እሳት ነው ካለው በኋላ "አየኸው ይህ አንተ ዝንተ ዓለምህን ስትቃጠል የምትኖርበት የገሀነም እሳት ነው አላወቅኸውምን?


ጥያቄዬን አልመለስክልኝምኮ አለው።


መስሩር እየተረዳው የመጣው ጉዳይ እነዚህ መላእክት እየመረመሩት መሆኑን ነው ይህን ሲያስብ ታላቅ የድንጋጤ ብትር ጭንቅላቱን ፈለጠው ብዙ ጊዜ ለሚጠየቀው ጥያቄ መልሶችን ለመስጠት ሞከረ ግን አልተሳካለትም። ለነገሩ ምን ብሎ መልስ ሊሰጥ ይችላልን ለእርሱ ታላቁ ጌታውና ሲያመልከው የኖረው ወርቅን ነው እንዲሁም ተንኮልና ሴራ ሌሎቹ አማልከቶቹ ነበሩ።


ነቢያትን በተመለከተ ስለእነርሱ ምንም በጐ ነገር ሰምቶ አያውቅም መስማትም አይፈልግም አንድ ነገር ብቻ ያውቃል ይኸውም ነቢያት አመፀኞች እንደሆነ ነው በዚህም ድርጊታቸው ድሆች የበላዮቻቸውን እንዳያከብሩና ሰጥ ለጥ ብለው እንዳይገዙ ያደርጓቸዋል። መስሩር ከዚህ ሌላ ምንም የሚያውቀው ነገር ስላልነበረ ሰጥ ብሎ መቆየቱን መረጠ። ማን ያውቃል አንዳንድ ያልሆኑ ነገሮችን ብናገር መርማሪዎቹን አስቆጣቸው ይሆናል ብሎ ፈርቷል።


ይቀጥላል……
1.6K views07:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 21:27:08 ንጉሱ ሶስት ባለስልጣናቱን ጠርቶ ለእያንዳንዳቸው ጆንያ በማስያዝ ወደ ማሳ ሂደው የተለያዩ ጣፋጭ ፍራፍሬዎችን እንዲለቅሙ እና ማንንም እገዛ እንዳይጠይቁ አዘዛቸው።

ባለ ስልጣናቱ የንጉሱ ትዕዛዝ ግራ ቢያጋባቸውም የታዘዙትን ለመፈፀም ጆንያዎቻቸውን ይዘው ወደ ማሳው አቀኑ።

አንደኛው ጆንያውን ይዞ ወደ ማሳ በመግባት ንጉሱን ለማስደስት ጣፋጭ እና ልዩ የሆኑ ፍራፍሬዎችን ለቅሞ በጆንያው ሞላ።

ሁለተኛውም ንጉሱ ይህን ሁላ ፍራፍሬ ፈትሾ ያያል ብሎ ስላልገመተ ለምርጫ ብዙም ሳይጨናነቅ ያገኘውን ሁሉ ለቃቅሞ ጆንያውን ሞላ።

ሶስተኛው ደግሞ ጭራሹኑ ንጉሱ ጆንያውን ይፈትሻል ብሎ ስላልገመተ አሰስ ገሰሱን ሰብስቦ በጆንያው ሞላ።

በቀጣዩ ቀን ንጉሱ ባለ ስልጣናቱን ከነጆንያዎቻቸው እንዲቀርቡ አዘዘ። ከዝያም ወታደሮቹን ጠርቶ ሶስቱንም ባለ ስልጣናት ራቅ ወዳለ ቦታ ወስደው ለ 1 ወር እንዲያስሯቸውና ከጆንያዎቻቸው ውጭ ምንም አይነት ስንቅ እንዳይሰጧቸው ያዛል።

አንደኛው ባለስልጣን ቀድሞ የሰበሰበውን ጣፋጭ ፍራፍሬ እየበላ ለ1 ወር ያህል በድሎት ቆይቶ ተፈታ።

ሁለተኛውም ባለስልጣን ለምርጫ ሳይጨነቅ የለቀማቸውን ፍራፍሬዎች ሳይጥመ እየበላ ብዙ ተጎድቶ ወሩን አጠናቀቀው።

ሶስተኛው ግን በረሀብ ሞተ።

ተፈፀመ!

አንተም አሁን በዱንያ ማሳዎች ያሻህን እንድትለቅም ሙሉ ፈቃድ ተሰጥቶሀል። ግና ነገ የንጉሶች ንጉስ በቀብርህ እንድትታሰር የሞት ወታደሮቹን ሲልክብህ የለቀምካቸውን መልካም ፍሬዎች ብቻ ነው ይዘህ ምትታሰረው።

Sefwan Sheik Ahmedin
1.6K views18:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 12:34:20
ፉዶይል_ኢብኑ_ዒያድ ረሒመሁሏህ እንዲህ ይላሉ : -

"ምርጡን ዱቄት እያወጣ እንክርዳዱን እንደሚያስቀረው ወንፊት አትሁኑ ፣ ከአፎቻችሁ ጥበብን (ጥሩ ንግግርን) ታወጣላችሁ ፣ ውስጣችሁ ደግሞ ቂምና ጥላቻ ይቀራል።"

۞【صفة الصفوة【٤٥٧/١】۞
1.6K views09:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 00:43:06 የአደም ልጅ ሆይ! በእናትህ ሆድ ውስጥ አኖርኩህ፤ ከማሕፀን እንዳትበረግግም ቅርፊቶችን ከፊትህ ጋረድኳቸው።

የምግቦች ጠረን እንዳይረብሽህም ፊትህን ከናትህ ሆድ ወደ ጀርባዋ አዞርኩልህ። ከናትህ ሆድ ውስጥም ሁለት መደገፍያዎችን አበጀሁልህ። ለቀኝህ መደገፍያ ጉበቷን አድርጌ ለግራህ ጣፍያዋን አበጀሁልህ።

መቆምንም መቀመጥንም ከእናትህ ሆድ ውስጥ ሁነሁ ገራሁህ፤ ታድያ ይሄን ከእኔ ሌላ እሚችል አለ?

የመውጫህ ግዜ ሲደርስማ!
መልዓኩን ልኬ ከክንፎቹ በአንዱ ላባ ቀስ አድርጎ እንዲያስወጣህ አደረግኩ።

ሚያኝክ ጥርስ የለህ፣ እሚጨብጥ እጅ የለህ፣ እሚሮጥ እግር የለህ...ከእናትህ ደረት ስር በሁለት ቱቦዎች የሚፈሱ ንፁህ ወተቶችን በክረምት ሙቅ በበጋ ቀዝቃዛ አድርጌ አመነጨሁልኽ።

ወላጆችህ ሳትጠግብ እንዳይጠግቡ፣ ሳትተኛ እንዳይተኙ የሚያደርግ ፍቅርህን ዘራሁባቸው።

ጡንቻዎችህ ፈርጥመው ጉልበትህ የመጣ ግዜማ፤ በአመፅ ዘመትክብኝ። ጭራሽ እኔን አታፍረኝምም።

ይህም ሁኖ!
ስትጠራኝ እመልስሃለሁ፣ ስትለምነኝ እሰጥሀለሁ፣ ተፀፅተህ ወደኔ ብትመጣ እቀበልሃለሁ።
1.8K views21:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-25 07:25:55 ~ የመስሩርና የመቅሩር ታሪክ

~ ክፍል አስራ ሶስት


የመቅሩር ህልፈት


መስሩር በሞት ጣዕር ላይ በነበረበት ጊዜ መቅሩር በበኩሉ በአንድ የእንጨት ክምር ዙሪያውን ባለበት ምሰሶ ላይ ታስሮ የሚፈፀምበትን ይጠባበቅ ነበር፡፡ ቦታው ለእርሱ ተብሎ የተዘጋጀና የሞት ቅጣቱን የሚያገኝበት ሥፍራ ነው፡፡ እንዲሞት የተወሰነበት ተቃጥሎ ነው በመጀመሪያ የተጋጋመው እሳት እየተንቀለቀለ ዙሪያውን ሲከብበው ሲያይ በጣም ደንግጦ ነበር።

በኋላ ላይ ግን አንድ እንግዳ የሆነ ፍጥረት ከፊት ለፊቱ እንዳለ ሊመለከት ከፍተኛ መረጋጋት አደረበት ያ እንግዳም መልአክ ሲሆን እንዲህ አለው “አይዞህ አትፋራ ና ወደዚህ ከዚህ በኋላ ቅንጣት ስቃይ አይደርስብህም እንዲሁም
ተቃጥለህ አትሞትም።”

መቅሩር በለሆሳስ፡ “አንተ ማን ነህ? እለ

"እኔ ለአንተ የምስራች ልነግርህ የመጣሁ መልዕክተኛ ነኝ "ምንድን ነው የምትነግረኝ የምስራች?

አንተ በእርግጥ የሞት መልአክ ነህን?*

“አዎ

መቅሩር እንዲህ አለ "አሁን እስክሞት ከተቃጠልኩ አላህ ያደረኩትን ተውበት ተቀብሎኛል ማለት ነው?


መልአኩም ሲመልስ አንተ እስክትሞት ድረስ በእሳት አትቃጠልም - እሳቱ አንተ ያለህበት ከመድረሱ በፊት ነፍስህ እንድትወጣ ይደረጋል።


እኔ'ኮ በአላህ መንገድ ተቃጥዬ ብሞት ነበር ፈቃዴ
“ተስፋ አትቁረጥ! በመጪው ዓለም ጥሩ አቀባበል ይጠብቅሃል ስቃይ የሚባል ነገርም ያበቃል፡፡”


በዚህ ቅጽበት መቅሩር ሁሉም ነገር ግልጽ ሆነለት። ስሜቱን በቅጡ ሲያጤነው የጀነትን መልካም ሽታ አፍንጫው ሲያበስረው አስተዋለ።


ነገር ግን መልአከ ሞት ራሱን ለመቅሩር በገለፀበት ቅጽበት ነፍሱ አካሉን ተለይታ ህያው እንደሆነች የመልአኩን ማራኪና ውብ ፊት እያሰበች ነጐደች።


መቅሩርን ከነነፍሱ ለማጋየት ተዘጋጅቶ የነበረው የማቃጠያው ሠራተኛ አለቃውን በጩኸት በመጣራት ክቡር አለቃዬ ሆይ! ተከሳሹ ሰው ሞቷል ገና እሳቱ እርሱ ወዳለበት ሳይደርስ ነፍሱ ወጥታ ተዘርሯል” አለ፡፡


አለቃውም በመገረም “ስማ ይህ ሰው የሚያጋጥመውን አደጋ ገና ካሁኑ የፈራው ይመስላል። በድንጋጤ ራሱን ስቶ ይሆናል እንጂ እኔ በእውነት ሞቷል ብዬ አላምንም። ይልቁንስ ቀዝቃዛ ውሃ ፊቱ ላይ እርጭበትና ሲነቃ ጠብቀህ አቃጥለው። ከዚያ በኋላ አመዱንና የተራረፈውን አካሉን በወህኒ ቤቱ መቃብር ስፍራ ቅበረው አለው።


በተመሳሳይ ሰዓት መልአከ ሞት የመስሩርን ነፍስ ማውጣቱን አጠናቆ ስለነበር ሰውነቱ መወራጨቱን አቁሞ ፀጥ ብሎ ተጋድሟል። በዚህ ጊዜ ከደንገጡሮቹ አንዷ እሪታዋን አስነካችው። ሌሎቹም ተቀብለው ማልቀስ ሲጀምሩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እሷንና እዚያ የተሰበሰቡትን ሁሉ ክፍሉን ለቅቀው እንዲወጡ አዘዛቸው። ከእርሱም ጋር የደኅንነት ኃላፊውና የዘበኞቹ አለቃ ብቻ ቀሩ።


ሶስቱ ሰዎች ብቻቸውን መሆናቸውን ያረጋገጠው ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲህ አለ ፣ ሰዎች ታላቁ መሪያችን እንደሞተ ይናገራሉ ይህ አባባላቸው በፍጹም ትክክል አይደለም። እባካችሁ እርሱ አንድ የሆነ ቦታ መሄዱንና ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ይመለሳል ብላችሁ ንገሯቸው፡፡ አሁን አስከሬኑን ከወህኒ ቤቱ መቃብር ቦታ ውሰዱና ቅበሩት የመሪያችን በልዩ ሁኔታ በእብነበረድ የታነፀው መቃብር ቦታ ግን ክፍት እንደሆነ ይቆይ። ይህም ሰዎች በውስጡ ምንም ዓይነት አስክሬን አለመኖሩን ሲገነዘቡ እኛ ያልናቸውን ነገር እንዲያምኑን ያደርጋቸዋል።


ምሽቱ ለዓይን ያዝ ሲያደርግ የደኀንነቱ ኃላፊና የዘበኞቹ አለቃ የመስሩርን አስከሬን በጥንቃቄ ተሸክመው መቅሩር ከተቀበረበት አጠገብ ቆፍረው አጋደሙት የመቅሩር አስከሬን ተቃጥሎ የተረፈውና አመዱ) ከጥቂት ጊዜ በፊት በዚያ ቦታ ላይ አርፎ ነበር ይህ ሁሉ ድርጊት ሲከናወን ከሶስቱ ስዎች ውጭ ማንም ስለማያውቅ ምስጢርነቱ ፍጹም አስተማማኝ ነበር ማለት ይቻላል።


ምፀታዊ በሚመስል ሁኔታ መስሩርና መቅሩር በአንድ የመቃብር ቦታ የተቀበሩ ሲሆን በሁለቱም ላይ የመቃብሮቹ በሮች ክርችም ተደርገው በአፈር ተዘግተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የታላቁ መሪ የአገዛዝ ሁኔታ በተለመደው አኳኋን እንደሚቀጥል አዋጅ አስነገረ።…


ይቀጥላል ኢንሻ አላህ
1.7K views04:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-24 18:55:45 አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካቱ ለረመዷን አስቤዛ ማዘዝ ለምትፈልጉ እህት ወንድሞች ወደ ግሩፑ ይቀላቀሉ ሊንኩን ሸር አድርጉ ለሌሎች እንዲደርስ የምንልክባቸው አካባቢ ወሎ ደሴ ኮምበልቻ ሀይቅ ኩታበር
ሀርቡ አርጎባ ከሚሴ ወለዲ ጨፋ ሮቢት ሙሉ ለሙሉ…

የአስቤዛ የዎጋ ዝርዝር

1️ካርቶን ቴምር
~ የቆርቆሮው

2️/ዘይት 5️ሊትር

3️/ሱኳር 10 ኪሎ

4️/ሩዝ በስመቲ 5️ኪሎ

5️/መኮረኒ 5️ኪሎ

6️/ቡና 1 ኛ ደረጃ 5️ኪሎ

7️/ነጭ ዱቄት 25 ኪሎ

8️/የሾርባ አጃ 10 ኪሎ

9️/አሲር ፎስተር 1 ሀባ

10 /ወተት ኒዶ ትልቁ

11 /ወተት ኒዶ መካከለኛ

12/ወተት ኒዶ ትንሿ

13/ምስር ክክ 5 ኪሎ

14/ዲፍን ምስር 5 ኪሎ

15/ አድሩስ / እጣን በአንደኛው በሁለተኛው

16/ የሾርባ ገብስ

17/አንድ ኩንታል ጤፍ

18/ አንድ ኩንታል ማሽላ

19/ 25 ኪሎ ኖርማን ሩዝ


+971521630386
+971521630386

በቴሌግራም

@Ibnu_Mohammed
@Ibnu_Mohammed

የዋትስ አፕ ቻናላችን
https://chat.whatsapp.com/BBDjo0KpG031vWLtcBAaHo
1.6K views15:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-24 14:43:44 ~ የመስሩርና የመቅሩር ታሪክ

~ ክፍል አስራ ሁለት

የመስሩር ያልታሰበ ሞት


መስሩር ራቱን በልቶ እንደጨረሰ ብዙ መጠጥ ከመጐንጨቱም በላይ ተጨማሪ ወይን ይዞለት ወደመኝታው እንዲገባ አገልጋዩን አዘዘው። ወዲያው እርሱም ተከትሎት እየሄደ ሳለ ራሱን እንደመሳት በማድረግ ክፉኛ ማዞር ጀመረው፡፡ ከዚያም መንፈሱ በሙሉ ታውኮ አካሉም ድክምክም አለበት መስሩር በብዙ መከራ በአገልጋዩ እርዳታ ወደ መኝታ ቤቱ መግባት ቢችልም ከዚያ በኋላ ሊቋቋመው የማይቻል የሆነ ህመም ትከሻውን ቀስፎ ያዘው ህመሙ ጥቂት ቆይቶ ከትከሻው ወደ እጆቹ በኋላም ወደ ደረቱ ተሻገረ።


በደረቱ ዙሪያ በእሳት የጋለ አሎሎ ሲሽከረከር ይሰማዋል። ይህ ከሆነ ብዙም ሳይቆይ መላ አካላቱን መቆጣጠር አቅቶት መሬት ላይ ሲዘረር። ይህን ሁኔታ ያስተዋለው አገልጋዩ ኡኡታውን አቀለጠው ፣ በቅጽበትም በአገልጋዮች፣ ደንገጡሮችና በጥበቃ ሠራተኞች መኝታ ቤቱ ተወረረ። እነርሱም ገዢያቸውን እንደምንም ብለው ወደ መኝታው ላይ አውጥተው አስተኙት ይህ ከሆነ ብዙም ሳይቆይ በግዛቱ ውስጥ አሉ የተባሉ ጥበበኛ ሐኪሞችና የመድኃኒት አዋቂዎች በመኝታው ዙሪያ ከብበው ሁኔታውን በድንጋጤ ያስተውሉና መላ ይፈልጉ ጀመር።


የአለቃቸው ፊት እንደ በረዶ እየገረጣ በታላቅ ድምፅ ሲያጓራና ሲያቃስት የሚያደርጉት ጠፋቸው አንገቱን በስለት እንደሚቆረጥ ከብት ሲተነፍስ ያንቋርር ነበር፡፡
የሐኪሞቹ አለቃ ምን ዓይነት መጥፎ ሁኔታ ነው የገጠመን ታላቁ ገዢያችን ህሊናቸውን በመሳት ላይ ናቸው'ኮ' አለ
መስሩር ወደ መኝታ ቤቱ ከመግባቱ በፊት ጀምሮ የሌላ አዲስ እንግዳ አካል እንደተሸከመ ይሰማው ጀምሯል። የሆነ ያልታወቀ ፍጥረት በእርሱ መኝታ ቤት መገኘቱን እየተረዳ መጥቷል።


ይህ ፍጡር መልኩና ሁኔታው እንዲህ ያለ ነው ብሎ ለመናገር ይከብዳል። አንድ ነገር ብቻ በግልጽ ይስተዋልበታል። አዎ ፊቱ ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂያ ምልክቶችን ያዘለ መሆኑ ነው።


መስሩር ህሊናውን እንደሳተ ባለበት ሁኔታ እንዲህ በማለት ጥያቄ አቀረበለት ማን ነህ አንተ? እንግዳውም፡ እኔማ የመጣሁት የማይቀረውን የሞት ጽዋ እንድትጐነጭ ልጋብዝህ ነው : አለው።


የሁለቱን ምልልስ ማንም ሊሰማው አልቻለም። ይሁን እንጂ ይህ ያልታወቀ እንግዳ መስሩር ቀደም ሲል ሲጠጣው በነበረው የወይን ጠጅ ምትክ በኩባያ የተሞላ ሌላ ተዓምረኛ መጠጥ እንዲጠጣ ወደ እርሱ ሲዘረጋለት ማንም ሰው ሊሰማው የማይችል ነገር መስሩር አልጐመጐመ ምንድን ነው በውስጡ የያዘው ነገር?


እንግዳውም “አስካሁን ጉዳዩን አልተረዳኸውም ማለት ነው? ክቡር ገዢ! ይህማ የማይቀረውና ማንኛዋም ነፍስ የምትቀምሰው የሞት ጽዋ ነው። ይህን ሁኔታ ማንም ሊያስቀረው አይችልም:: ፍፃሜህ እንግዲህ ይህን ይመስላል። የትንሽ ሰከንዶች ጉዳይ ነው፡ ከዚህች ምድር ተለይተህ ወደ ሌላ ዓለም መጓዝህ ነው " አለው ማሾፍ በተቀላቀለበት አነጋገር የእንግዳውን ንግግር እንደሰማ ይህንን መስሩር መብረቅ እንደመታው ሰው ተሸማቀቀ ከዚያም እየተንፈራገጠ በመጮህ እኔ አሁን መሞት አልፈልግም::


እባክህ ልለምንህ ከፈለግህ ያለኝን ንብረት ሁሉ ውሰድ። ገንዘቤንም ጭምር የራስህ አድርገው፡ ለአንድ ወር ለአንድ ሳምንት ወይም ለአንድ ቀን እንኳን አዘግየኝ እባክህ "
የተሸፈነበትን ነገር ገልጦ መስሩር ፊቱን እንዲያየው አደረገው ፊቱ በቀላሉ ሊታይ (ሊታወስ) የሚችል ነው፡፡


መስሩርም ወዲያው የሞት ጣዕር ያጣድፈው ጀመር ያችን መራራ የሆነች ፅዋ ተጐነጨ። እየጐፈነነውም ቢሆን በግድ ዋጣት የመስሩር ነፍስ ከሰውነቱ ስትወጣ በጣም አስደንጋጭ በሆነ አኳኋን ነበር። ልክ አንድ ጉጥና ቅርንሤፍ የበዛበትን ግንድ ከትልቅ የጥጥ ክምር ውስጥ እንደመምዘዝ ያህል ነው።


መልአከ ሞት የመስሩርን ፊት በኃይል ያላጋው ጀመር። ከትንሽ ሰከንዶች በኋላ ነፍሱ ጉሮሮው ላይ ደረሰች እዚያ ሆና የመጨረሻ የሞት ሞቷን ልትታገል የወሰነች ይመስላል። ትግሏ ግን የተሳካለት አልሆነም። በመሆኑም ወደ ቀብራራው ገዢ አፍ አመራች ጨርሳ ልትፈፀም።

ኢንሻ አላህ ይቀጥላል…

https://t.me/Golden_Speech
https://t.me/Golden_Speech
1.5K viewsedited  11:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-23 06:09:18 የመስሩርና የመቅሩር ታሪክ

ክፍል አስራ አንድ

ህልሙ


መቅሩር ወደ ወህኒ ቤት እየተወሰደ ባለበት ሰዓት ዋናው ዳኛ በሌላ በኩል ከቤተ - መንግስቱ ሳይወጣ የሆነ ነገር በግድ እንዲጠጣ ከተደረገ በኋላ በተወሰኑ ሰዎች ተደግፎ ትንሽ ለመራመድ ሞክሯል በኋላ እንደተሰማው ከሆነ በጠጣው የተመረዘ መጠጥ ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ ከተሰቃየ በኋላ መሞቱንና የእርሱም ጉዳይ በዚያው ላይ ማብቃቱን ነው። ተቃጥሎ አንዲሞት የተላለፈበት ፍርድ
ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ተፈፃሚ አልሆነም።


ታላቁ ገዢም ወደ ዋናው ዳኛ ቤተሰቦች ዘንድ የሀዘን መግለጫ ይዘው የሚሄዱ ሰዎች የመረጠ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ እርሱን የሚተካ ሌላ ዳኛም ሾማል
መቅሩር በወህኒ ቤቱ ውስጥ ፍፁም እርካታ በመጐናፀፍ ተቀምጧል። እርሱን በእሳት በማቃጠል ሊቀጡት እንደማይፈልጉ ገምቷል። ለዚህም ነው ለሚጠብቀው ዘበኛ እንዲህ በማለት ጥያቄ ያቀረበለት፣ “ወንድሜ እነዚህ ስዎች በእሳት አቃጥለው ሊገድሉኝ አስበው ይሆን እንዴ?


ዘበኛውም እኔ አንተ ለምታነሳው ጥያቄ መልስ እንድሰጥ አልታዘዝኩም። እኔ ያንተ ጠባቂ እንጂ ጓደኛህ አይደለሁም። እኔና አንተ እንድናወራ ደንቡ ስለማይፈቅድልን ባታናግረኝ መልካም ነው"


መቅሩር በወህኒ ቤቱ ውስጥ ግራ በተጋባ ሁኔታ ለሶስት ቀናት ያህል ቆየ። ሦስቱን ቀናት በሁለት ዓይነት ስሜቶች ተወጥሮ ነው ያሳለፈው እንዳንድ ጊዜ በደስታ ይሞላል በሌላ ጊዜ ደግሞ ሀዘን ያጠላበታል።


ሰዎቹ እንደዛቱት በእሳት አቃጥለው የሚገድሎት ከሆነ እሰየው ነው ምክንያቱም ሁሉን ቻይ የሆነው አላህ ፀፀቱን ተቀብሎት በእርሱ መንገድ ሸሂድ (ሰማዕት) ሆኖ እንዲሞት ፈቃዱ ሆኖአል ማለት ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ሰዎቹ ዝም ብለው:: በእስር የሚቀጡት ከሆነ አላህ ፀፀቴን (ተውባዬን አልተቀበለውም ብሎ ያምናል።

መቅሩር ስላጋጠመው የመንፈስ ማወላወል ፈጣሪው አንድ ህልም በማሳየት ተውበቱን የተቀበለው መሆኑን በሚያረጋግጥ የምስራች እንዲያበስረው አጥብቆ መለመኑን ተያይዞታል። እንዳሰበውም በሶስተኛው ሌሊት አንድ ልዩ የሆነ ህልም ማየት ቻለ። በህልሙም ራሱን በደኖችና በአበቦች በተዋበ መናፈሻ ውስጥ እንዳለ ሆኖ ያገኘዋል። መናፈሻው በውስጡ ልዩ ልዩ ጣፋጭ የሆኑ ፍራፍሬዎች የሞሉበትና ጥርት ያሉ ምንጮች የሚገኙበት ነው፡፡


በዚያ ቦታ የረገጠው ነገር ሁሉ ምስክ የተርከፈከፈበት ስለሆነ የእግር ጣቶቹ እጅግ ማራኪ በሆነ ሽታ ይታወዳሉ እንዲሁም ተውበት ከማድረጉ በፊት አብራው የነበረችውና በኋላ የተለያት የቀድሞ ባለቤቱን የምትመስል ሴት ያያል። እርሷ ከፊት ለፊቱ እየተራመደች እሱም እየተከተላት ከአንድ ተራራ ጫፍ ላይ ከሚገኝ በውብ መናፈሻ የተከበበ ቦታ ደረሡ እዚያ ቦታ ላይ ግፈኛው መስሩር ከሚኖርበት ቤተ መንግስት እጅግ የላቀና በውበቱም ሆነ በምቾቱ ያማረ ቤተ መንግሥት ሴትየዋ በእጇ እያመላከተችው እንዲህ አለችው መቼ ነው ታዲያ ወደዚህ የምትመጣው?

እርሱም፡ ለመሆኑ አንቺ ማን ነሽ?

ጠየቃት
ከእንቅልፉ ባንኖ ነቃ መልሱን ሳትሰጠው እንደተሰወረችበት
ይህን ያየውን ህልም ከጥበቃው ሠራተኛ ንግግር ጋር ሲያያይዘው አንዳች የሆነ ትርጉም ሰጥቶታል- የጥበቃ ሰራተኛው “በእርግጥ ዛሬ ትገደላለህ ፀሎትህን በጊዜ አጠናቅ " ነበር ያለው።


መቅሩርም ይህን ህልም ካዬ በኋላ በህልሙ ውስጥ ስላየው ውብና የሚናፈቅ ነገር እያሰበ ለሚመጣበት ማንኛውም ዓይነት አደጋ ከዚያ በኋላ ግድ አልነበረውም።

ይቀጥላል…
1.8K views03:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-22 23:05:10
~

ሁሉም በጎ ነገር ሰደቃ ነው ።

ረሱል (ሰ ዐ ወ)
1.6K views20:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ