Get Mystery Box with random crypto!

ወርቃማ ንግግሮች

የቴሌግራም ቻናል አርማ golden_speech — ወርቃማ ንግግሮች
የቴሌግራም ቻናል አርማ golden_speech — ወርቃማ ንግግሮች
የሰርጥ አድራሻ: @golden_speech
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.15K
የሰርጥ መግለጫ

ሰው የለበስክ ሰው እንጂ ልብስ የለበስክ ሰው አትሁን.. ሰውነት የአለም ምርጡ ጌጥህ እሱ ነውና።
አስተያየት እንቀበላለን.. @Golden_SpeechBot
https://youtube.com/channel/UCgP-E0miz3BhJ0YAGJ2zCHg

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 33

2022-07-16 17:15:40 “በቤተሰቡ መሀል በሠላም ያደረ ሰውነቱ በሙሉ ጤነኛ ሆኖ ያነጋ፤ የዕለት ጉርሱን ያገኘ ዱንያን በሙሉ ሰብሰቧታል።” ረሱል (ሰ•ዐ•ወ)
400 views14:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 17:15:18 በአላህ ጉዳይ ላይ ሰዎችን አትፍሩ በሰዎች ጉዳይ ላይ አላህን ፍሩ
ነብዩ መሀመድ ሰሉ አለይሂ ወሰለም
402 views14:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 20:22:29 በኢማም ማሊክ ዘመን ነው።
ባል እና ሚስት ከባድ ጭቅጭቅ ውስጥ ገብተው ሚስት ደረጃ ላይ ሆና ባል ደግሞ ከታች ምድር ላይ ሆኖ ስድብ እየተቀባበሉ ነው። (ፎቅ ድሮም ነበር)

የሚስቱን የስድብ ናዳ መቋቋም የተሳነው ባል ደግም ከዚህች ሴት ጋር አብሮ ላለመኖር ወሰነ'ና፦‹‹ከደረጃው ከወጣሽም፣ ከደረጃው ከወረድሽም፣ ደረጃው ላይ ቆመሽ ከቀረሽም ኒካችን ወርዷል ማለት ነው›› ብሎ ለፈትዋ እማይመች አይነት የኒካ ፍቺ መስፈርት አስቀመጠ።

የተወሰነ ቁማ አሰላሰለች። ደረጃውን ብትወጣ ባሏ ሊፈታት ነው፤ ደረጃውን ብትወርድም ሊፈታት ነው፤ ቆማ ብትቀርም መፈታቷ አይቀርም። አንድ ዘዴ ዘየደች'ና ከቆመችበት ደረጃ ላይ ዘላ ባሏ ላይ ሰፈረችበት።

እሷ ካላዩ ሁና ሁለቱም ወደቁ። በሚስቱ ብልኃት የተደመመው ባል ከስር ሁኖ እየተነፈሰ፦‹‹አቦ ፈትዋ! ወላሂ ኢማም ማሊክ ከሞቱ የመዲና ሙፍቲ ምናደርግሽ አንችን ነው››

ምንጭ፦
المستطرف في كل فن مستظرف
https://t.me/Golden_Speech
1.0K viewsedited  17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 16:18:59 «አንድ ቀን በእድሜው እጅግ የገፋ ሽፋሽፍቱ የወረደ ፣ ወገቡ የጎበጠ ፣ ሽማግሌ ዱላውን ተደግፎ እየተጎተተ የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ዘንድ መጣ ። የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ትንሽ ትልቅ ሳይል ኋጢያት የተባለን በሙሉ አንድም ሳያስቀር የሰራ ሰው እጣ ፈንታው ምንድን ነው!? አላቸው። ኋጢያቱ በምድር ላይ ላሉ ሰዎች በሙሉ ቢከፋፈል ሰዎችን የሚያጠፋ አይነት የዚህ አይነቱ ሰው ተውባ ይኖረዋልን? የአላህንስ ምህረት ያገኛልን!? አላቸው።

«ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) «ሰልመሃልን» አሉት።ሰውየውም «እኔማ ከአላህ በስተቀር አምላክ የሌለ ስለመሆኑና አንቱም የአላህ መልዕክተኛ መሆንዎትን እመሰክራለሁ። አላቸው።

« እርሳቸውም መልካምን ነገር ትሰራለህ! ከመጥፎ ነገር ትርቃለህ! በዚህም አላህ ሁሉንም ነገር በመልካም መዝገብ ላይ ይፅፍልሃል። አሉት። ሰውዬውም ክህደቴንና ጥመቴን ሁሉ!? አላቸው። እርሳቸውም አዎን! ክህደትህንና ጥመትህን ሁሉ አሉት። ሰውየው ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ ደስተኛ ሆኖ «አላሁ አክበር፣ አሏሁ አክበር እያለ ሄደ። ከአይን እስኪሰወር ድረስ ይህንኑ ቃል ይደጋግም ነበር።

«አሁን ጭንቀታችሁ ሲረግብ ይታየኛል። ኢንሻ አላህ ይረግባል። አላህ ሆይ ጭንቀታችንን እርቅልን ። የደስታ ኑሮም አኑረን።

https://t.me/Golden_Speech
https://t.me/Golden_Speech
1.1K views13:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 15:37:15 ~ የመጨረሻው እስትንፋስ በጭጋጋማ ክፍል = አስራ ስምንት በዓለማዊ መጠቃቀሚያና በስሜት ባህር የተዘፈቁ ሰዎች አንድ እለት አላህ መጥፎ አያያዝ የያዛቸው ጊዜ ወዮላቸው፡፡ ያኔ የመጪው ዓለም መጋረጃ.... ይገላለጥና ሁሉንም ነገር በዓይነ ሥጋቸው ሲመለከቱ ምን ይውጣቸው ይሆን? ~ ይህን አንኳር ሃቅ ኃያሉ አላህ በብዙ የቁርዓን አንቀፆች የገለጸው ሲሆን ቀጣዮቹ አንቀፆችም የሚያብራሩት ይህንኑ ነው።…
1.0K viewsedited  12:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 08:14:34 የረበና ሰላም በናንተ ላይ ይሁን አሁበኩም ፊላህ።

ትዳር ወይስ ስራ...

በሰው ሃገር ባይዋተር የሆንሺው ውድ እሄቴ ስለ አንቺ ሳስብ የማወራው የምፀፈው ሁሉም ይደባለቅብኛል። ብዙ እህቶች የእድሜ ገሚሳቸውን በአረብ ሃገር ተቀጥረው በማገልገል ነው የሚጨርሱት። ስራሽን ሃሳብሽን ሳላደንቅ የማላልፍበት መንገድ የለኝም አለማድነቅ አለማመስገን ንፉግነት ነውና። አዎን ከዛም አልፎ መታወር ነውና።....

ከርእሳችን ሳልወጣ ወደ ጥያቄው መልስ ይሆናል ያልነውን ሃሳብ እናጋራ ይህ ሃሳብ የኔ ብቻም አይደለም የአብዛህኞቹ መልስ ይህ ነበር። ታግባ የሚል ነው። እኔም ከዚህ ውስጥ ነኝ። ከስራ ይልቅ ትዳርን ነው ለሴት ልጅ የምመርጠው።


እድሜሽን በስራ ገፍተሽ አሁንም በስራ መወጠርሽ ከምን የመጣ ነው። ከስራ ይልቅ ትዳር መፈለጉ ላይ ትኩረት አድርጊ ጥሩ ወንድ የለም ታማኝ የለም በሚል ፈሊጥ ህይወትሽን በእንቶ ፈንቶ ሃሳብ ራስሽን አትግደይ። አንቺ ከአላህ ጋር እስከሆንሽ ድረስ ይህ ነገር አያሳስብሽም የኢማን ልቅናሽን ዘለበትሽን እንዳትለቂ የአላህ ፍቅርም በልብሽ ይንገስ ምን አልባት የሰው ፍቅር ቢመጣ ልብሽ አይናወጥምና። ልብሽን የአላህ ፍቅር ከተቆጣጠረው ስለ ሰው ፍቅር አላህ ይሆንልሻል። ስለ ሰው ፍቅርም ልክ እና ገደብ ያበጅልሻል ያሳይሻል።


ትዳር በመቅረቱም አትብሰይሰይ የአንቺ ያለው ይመጣል። ከሃገር ከገባሽ ቡሃላ ወደ ትዳርሽ ይሁን ዝንባሌሽ። ግዜ ህይወት ነው። አንቺ የቀናት ጥርቅም ነሽ ከትዳርሽ እርቀሽ ስራ ስራ ስትይ እድሜሽ ላይመለስ እያከተመ መሆኑን እሰቢበት እናም አግቢ። ወደ ትዳር ለመግባት ብዙ አመት የሰራሻቸው ገንዘቦችም አይከስሩብሽም ለሴት ልጅ ወደ ትዳር ለመግባት ወጪ ወይም ኢንቨስት አያስፈልግም እና ይህን እድል ለማን ታሳልፊያለሽ።

ወደ ስራው ከገባሽ ቡሃላስ ብትከስሪስ ተስፋ ቆርጠሽ ተናደሽ የማይሆን ወንድ ላይ ትዳሩን ልየው ብለሽ ልትገቢ ትችያለሽ እድሜሽም ሲሄድ ለመውለድ ብለሽ የማይሆ ጥምረት ታደርጊያለሽ። ወደትዳር ስትገቢ ምርጫሽን አስተካክይ ቤተሰብ የወደድልሽን በመልካም የሚያኖርሽን ስራ የማይንቀውን ትጉውን አብራችሁ መለወጥ የምትችይውን አግቢ። ትዳርሽን በመልክ እና በኡዝታዝ በሚል ፌዝ ሰዎች በመፈለግ እንዳታበላሺ መልክ ያለውም ካሰኘሽ ስራ የሚሰራ የማይንቅ አንቺን የሚያኖር ይሁን። ኡዝታዝም ካልሽ እየከሰበ የሚያኖሽ በኢልሙ እራሱንም የሚመክር የሚተገብር አይነት ይሁን። አለበለዚያ ግን ከማይሰራ ኡዝታዝ ወይም ቆንጆ የቀን ስራ የሚሰራን ምረጪ ገንዘብሽን ብሰጪው ያበዛልሻል። ልብሽን ብትሰስጪው ይንከባከብልሻል። አካልሽን ስትጪው ልጅ ይሰጥሻል። ስራ የሚሰራ ስልሽ ታዲያ ሶላቱ ላይ ኢማኑ ላይ ደካማ የሆነውን አይደለም። ወይም እየሰራ የሚቅመውንም አይደለም ለመለወጥ ጥሩ ትዳር ለመመስረት አስቦ ደፋ ቀና የሚለውን ቢሆን እንጂ በዛውም የሚወደድ ስራ ሰራሽ።...

አገር እንደገባሽ ስራ ለመጀመር የሃገርሽን ሁኔታ ወይም ፍላጎትና አቅርቦትን ስታጠኚ ገንዘብሽንም ትጨርሻለሽ ሳታውቂው በሰዎች ያልሆነ ያልወደድሺው ስራ ላይ ብትገቢ ራስሽን ነው የምትወቅሺው። ባልሽ ለሰውም ከሃገሩም ከስራውም ጋር ያስተዋውቅሻል።

ሁለት እረካኣ ስገጂ ዱኣ አድርጊ ከዛም አግቢ ነው የምንለው ወንድ ልጅ ነው ደግሞ ቤት አሳዳሪው መሪውም።

እንዳይበዛ ይበቃናል ሃሳብ መደጋገም እንዳይሆንብን አብዛሃኞቻችሁ መልካም ምርጥ ኮሜንት ሰጥታችኋል ሌሎችንም ይቀይርልን ይሆናል።

ወሰላም አለይኩም።
1.4K views05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 15:33:54 አንድ እህት ወደ ሃገር ልገባ ነው።

~ ሃገር ተገባሁ ቡሃላ ስራ ላስቀድም ወይስ ትዳር ልፈልግ የቱ ይሻላል ምክራችሁን ስጡኝ ትላለች።

ሃሳብ ልምድ ያላችሁ አካፍሉን ሃሳባቸውን እናቅልልቸው በኮሜንት መስጫው ግቡ

1.4K views12:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 14:26:20 ~ ስማ ወዳጄ

አንተ የውሳኔህ ውጤት ነህ ።
የሰው ልጅ ደስታውም፣ ጭንቀቱም፣ጥመቱም፣
መረጋጋቱም የሚመነጨው በራሱ ውሳኔና ምረጫ ላይ ነው።

ሙሀመድ አል-ገዛሊ

https://t.me/Golden_Speech
1.4K viewsedited  11:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 14:13:54 ነ ብ ዩ ( ሰ ዐ ወ ) አሉ…

አ ላ ህ እዝነትን ይወዳል ፤ ለአዛኞች የሚሰጠውን ደረጃና በጎ ነገር /ለማይተዛዘኑ ለማይተሳሰቡ/ ሰዎች አይሰጥም።

[ሙስሊም እንደዘገበው]
1.4K views11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 18:33:36 ~
የልብ ጉዞን ለማስረዳት የመልዕክተኛ ( ሰ 0.ወ) እንዲህ ይሉናል። አንድ ጉዳይ እነግራችኋለሁ በልባችሁ ያዙት። ዱንያ ለአራት ዓይነት ሰዎች ነች። አንደኛው ዓይነት አላህ ( ሱ. ወ)...

~ ገንዘብንና እዉቀትን ሰጥቶት በተሰጠው ችሮታም ጌታውን የሚፈራበት

~ ዝምድናወን የሚቀጥልበል

~ የአላህን መብት ዕውቅና የሚሰጥበት ባሪያ ነው።

ይህ ከፍተኛና በላጩ ደረጃ ነው።

ሁለተኛው አላህ ሱ ወ እውቀት ሰጥቶት ገንዘብ ያልሰጠው ባሪያ ነው:: እርሱም ከእውነት በሆነ ኒያ (ሃሳብ) ገንዘብ ቢኖረኝ እንደከሌ አይነት ሥራ እሠራ ነበር ይላል። ይህ ሰው በኒያው ከመጀመሪያው ዓይነት ሰው ጋር በምንዳ እኩል ናቸው”

(አሕመድና ቲርሚዚይ ዘግበውታል)

የልብ ጉዞው በተቡክ ዘመቻ ጊዜ መሣተፍ ያልቻሉት ሶሐባዎች የተጓዙት ጉዞ ነው:: እነርሱን አስመልክተው የአላህ መልዕክተኛም (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ነበር ያሉት፡

“በመዲና ዉስጥ ሰዎች አሉ፤ ጉዞን አትጓዙም፤ ወጭንም አታወጡም፣ ሸለቆን አታቋርጡም፡- እነርሱ መዲና ሆነው ከእናንተ ጋር ቢሆኑ እንጂ። (በአካል አብሮ መሆን) የከለከላቸው ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ነው።” (ቡኻሪ የዘገቡት)

ገጣሚው እንዲህ ይላል...
መካን ነይታችሁ ጉዞ ለወጣችሁ
እኛ በሩሓችን አለን ከኋላችሁ
አስቀረን ዑዝራችን አመለጠን ጉዞው
ችግር ያሰቀረውም የሄደው ያህል ነው።


ወንድሜ ሆይ! ይህንን የኬሚካል ውህድ በቀላሉ አይተኸው አትዘናጋ። በሥራ ንሰሃ ላይ ቅንጣት ያህል እንኳ ከጨመርክበት ወደ ወርቅነት ይቀይርልሃልና። ቀልብህን ለጉዘው የተገራ አድርገው።


https://t.me/Golden_Speech
https://t.me/Golden_Speech
2.0K viewsedited  15:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ