Get Mystery Box with random crypto!

ወርቃማ ንግግሮች

የቴሌግራም ቻናል አርማ golden_speech — ወርቃማ ንግግሮች
የቴሌግራም ቻናል አርማ golden_speech — ወርቃማ ንግግሮች
የሰርጥ አድራሻ: @golden_speech
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.15K
የሰርጥ መግለጫ

ሰው የለበስክ ሰው እንጂ ልብስ የለበስክ ሰው አትሁን.. ሰውነት የአለም ምርጡ ጌጥህ እሱ ነውና።
አስተያየት እንቀበላለን.. @Golden_SpeechBot
https://youtube.com/channel/UCgP-E0miz3BhJ0YAGJ2zCHg

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-03-09 21:52:12
ከምድር በላይ ከፍ ብለው፤ሰባት ሰማያትን ተሻግረው፤ በሃሳብ ከፍታ የሚሰቅለንን ሂዳያ አመጡልን።ከግርዶሹ ባሻገር ስላሉ ምስጢራትም እንድናይ አስቻሉን።በሰባት አጥንቶች ተደፍተን በመንፈስ ሰባት ሰማያትን እንድንዘልቅ ሆንን።በርሳቸው ከፍ አልን።በርሳቸው የእውነትን ቁልፍ ጨበጥን።

ጀዘሏሁ ዓና ሙሐመዳ

ወሰለሏሁ ወሰለመ ዓላ ሰይዲና ሙሐመድ
278 views18:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 14:56:17 «እንቅፋቶችና ፈተናዎች ልክ እንደ ሙቀትና ብርድ ጊዜያት ተፈራራቂ ናቸው። አንድ ባሪያ እነዚህ ፈተናዎች እንደማይቀሩለት ካወቀ በሚያጋጥሙት ጊዜ አይቆጣም፣ አይጨነቅም፣ አይተክዝምም»። {ኢብኑ ተይሚያህ}
568 views11:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 21:40:43 "ድሎት በድሎት እንደማይገኝ የሁሉም ህዝቦች ሊቃውንት የተስማሙበት ጉዳይ ነው።እረፍትን የመረጠ እረፍት ያመልጠዋል።ደስታና ጥፍጥና አስቸጋሪ ሁኔታዎችን በመወጣትና በትግል ላይ የተመረኮዘ ነው።
የሚያስጨንቅ ጉዳይ የሌለበት ደስታ የለውም።ወድቀት ላላየ ድሎት ፤ድካምን ላልተመከተም ሰው እፎይታ የለም።
ይልቁንስ ባሪያ ጥቂት ሲለፋ በረጅሙ ያርፋል።የትዕግስትን ሸክም ለሰዓታት ሲሸከም ወደ ዘልዓለማዊ ህይወት ይመራዋል።
የፀጋ ባለቤቶች ያሉበት ሁኔታ በሙሉ የሰዓታት ትዕግስት ውጤት ነው።"

ኢብኑል-ቀይም አል-ጀውዚያህ
684 views18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 11:30:13
በሻሻነትን ለፊታችን፤ኑርን ለልባችን፤ደስታን ለቀናችን የሚመልስልን ሰለዋት በነቢ ላይ ይውረድ።
ከአዕምሯችን ጭንቀትና ጥበትን የሚያጠፋ፤ልባችንን በውዴታ የሚያሰፋ ሰለዋት በነቢ ላይ ይውረድ።
اللهم صل وسلم على سيدنا محمد
628 views08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-25 16:07:01 ስራው ኢማራት ውስጥ ላለ ነው።
ኢትዮጵያ ውስጥ ላለ አይደለም
103 views13:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-25 15:03:03 ስራ ዲባይ ውስጥ ደመወዝ 1300

ቆሚ ስራ ነው

@Ibnu_mohammed
242 viewsedited  12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 07:19:53 የምድር ብርሃን


ምድር ቀደም ሲል እንደተገለፀው ከጌታዋ በሆነው መለኮታዊ ብርሃን ተሞልታለች። መጽሐፍቱ የተገለጡ ሲሆን ነቢያትና ምስክሮችም ቀረቡ። በዚህ ወቅት ለሁሉም ወገን አድሎ ላይደረግ ፍጹም : በእውነት ላይ የተመሰረተ ፍርድ ይሰጣል። ፍርዱም እንደመሆኑ እንዳች ስህተት አይፈጠርም።

መቅሩር ከአላህ በሆነ ብርሃን ተጥለቅልቋል። በዚህ ወቅት ባገኘው ተስፋ ሰጪ ሁኔታ ደስታው ያሻቀበ ሲሆን ፍርሃቱም
ተወግዶለታል ምድር በያዘቻቸው ፍጡራን የተጨናነቀች ሲሆን ፍጡር የተባለ ሁሉ በመርማሪዎቹ መላዕክት ፊት ከሊቅ አስከደቂቅ ቀርቧል ለአላህ ረቢ ባለሟል የሆኑት መላእክት አጅግ ግዙፍ የሆኑ የምርመራ መጽሐፍትን (ኪታቦችን) በፍጡራኑ ፊት ይዘው ቀርበዋል። ሁሉም ፍጥረታት ድምፃቸውን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሱና ፍርሃት ባጀበው ትህትና እየተሸበቡ መጥተዋል በዚህ ታላቅ ቀን መልአኩ ጅብሪል (ገብርኤል) ከአጽናፍ እስከ አጽናፍ የሚደርሱትን ክንፎቹን ዘርግቶ ፍጡራን እያዩት በታላቅ ግርማና ብርሃን ታጅቦ ብቅ አለ።


በእርሱ መምጣት የተገረመው ፍጥረት ማጉረምረምና ሹክሹክታ ፀጥ ሲል ጅብሪል እንዲህ አለ የሚያሰማው በዛሬው ቀን ታላቅነትና ንግስና ለማን ነው? በዚህ ጊዜ ልቦች ሁሉ በድንጋጤ ላንቃዎች ሥር ደረሱ ከዚያም ፍጡራን ሁሉ በአንድ ድምጽ የሁሉም የበላይና አቻ ለማይገኝለት አላህ ነው አሉ ጅብሪል ቀጠለና የሚከተለውን ተናገረ በምድር ዓለም እያላችሁ የክብር ፣ የታላቅ ዘርና ፣ የሀብት ባለቤቶች እንዲሁም እናንተ ነገስታትና ልዑላን ሆይ! ከእናንተ መካከል ዛሬ ታላቅ የሚሰኘው እርሱ በጽድቅ ሕይወት የኖረና አላህን ፈሪ የነበረው ነው ኃያሉ አላህ መልካም ምግባር እንዲሁም የልብ ንፅህና የታላቅ ዕድል ባለቤት ለመሆን መስፈርቶቼ ናቸው በማለት አዋጅ ተናግሯል።


መቅሩር በሰማው ነገር ስጋቱ ሁሉ እንደ ጢስ በንኖ ስለጠፉለት ሀሳቡን ሁሉ ወደ ጅብሪል ክብርና ማራኪ ገጽታ በማዞር በድማሜ ተውጦ ያስተውለው ጀመረ ከዚያም ለራሱ እንዲህ አለ…

የጌታዬ ባለሟል የሆነው ጅብሪል እንዲህ ታላቅ ግርማና እፁብ ድንቅ የሆነ ውበትና ገጽታ ካለው የእርሱና የአጽናፈ ዓለሙ ፈጣሪ ግርማ
ታላቅነት ምን ሊሆን ነው?


የፍትህ ሚዛን በቀረበ ጊዜ የሰው ዘር በሙሉ ከጌታው ፊት ሥራውን ሊያስመዝን ተሰበሰበ ነቢያትና ደጋግ ምስክሮች ቀርበው የምርመራው ሂደት ተጀመረ።


በዚህ ቅጽበት መቅሩር ታላቅ በሆነ የምርመራ ፍርሃት መንጠርጠር በመጀመር አላህ ተውበቱን ካልተቀበለው ኪሣራ ላይ እንደሚወድቅና የምርመራውን ሚዛን እንደማይደፋለት በመገንዘብ ቶሎ ቶሉ የጌታውን ስም በጭንቅ እየጠራ ከዚህ ጉድ እንዲሰውረው
ይማፀን ገባ በመስሩር ልብ ውስጥ የገባው መርበትበት በአንድ ታላቅ ደን ውስጥ በጨለማ ከሚፈጠር መብረቅና ጉርምርምታን ያዘለ ዝናብ ነው፡፡ አሁን እንግዲህ ከሚያመጣው ፍርሃት በእጅጉ የበለጠ ለማይቀረው የፍርድ ሂደት ጌታው ፊት መቆሙ እርግጥ ሆኖበታል ከእንግዲህ የሚደብቀውና ሰውሮ ሊያስቀረው የሚችለው ምስጢር አይኖረውም በአንድ ወቅት ተፈጥሮ በአሮጌዋ ምድር ሲኖር ነበር። ከዚያም እንዲሞት ተደረገ አሁን ደግሞ እነሆ ስለ ኃጢያቶቹና ጥፋቶቹ ዋጋውን በታላቁ ችሎት ፊት ለመቅረብ
ተዘጋጅቷል። ሊቀበል በምድረ ዓለም እያለ አላህ ክፉውንም ሆነ መልካሙን የሰውን ልጅ ሥራ እያሰመዘገበ እንደሚያስቀምጥ አያውቅም ነበር፡፡ እርሱ ታላቅ ትኩረት ይሰጣቸው የነበሩት ስልጣኑ ግዛቱ የወርቅ ሀብቱና ስሜቶቹ ነበሩ ከዛሬ በፊት የሠራቸው ኃጢያቶችና ግፎች ለጥፋቱ ምክንያት ሆነው ዋጋ ያስከፍሉኛል ብሎ ከቶም ጠርጥሮ አያውቅም መላእክቱ፡ ለሰው ልጆችና ለአጋንንቶች የምርመራ መጽሐፍቶቻቸውን ማደል ጀመሩ መስሩር መጽሐፉን ከጀርባው በኩል ተሰጠ። ይህ መጽሐፍ እንግዲህ ወደዚህች ዓለም ከመጣና ለአቅመ አዳም ከደረሰ ጀምሮ በሞት መዳፎች እስኪጨመደድ ድረስ ያሰላፋቸውን መልካምና ክፉ ምግባሮቹን አንድም ሳያስቀር ፍንትው አድርጐ በማስረጃ እያስደገፈ ያሳያል።

ይቀጥላል…
270 viewsedited  04:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 19:32:58 ሁሉን ነገር ሲረሳ የእርሱም ጉዳይ ተረሳ


ለመሆኑ ይህ የትንሳኤ ቀን (ዕለተ ቂያማ ከተከሰተ ስንት ጊዜ ሆነው አስር ሺህ ወይስ ሃምሳ ሺህ ዓመታት አለፉ? ይህ ሁሉ ጊዜ በእርግጥ እንደ አንድ ቀን ብቻ ይቆጠራል ማለት ነው ምንም እንኳን ይህን ሁሉ ነገር ማሰቡና ማውጣት ማውረዱ ዋጋ ያለው ነገር ባይሆንም ጉዳዩ በመስሩር አእምሮ መመላለሱ አልቀረም።


በመሰረቱ የቀንና የሌሊት መፈራረቅ እንዲሁም የፀሐይና የጨረቃ መተካካት በዓለማዊ ሕይወት የሰው ልጅ ጊዜንና ቀናትን ለመስፈር የሚጠቀምባቸው ምልክቶች ቢሆኑም ዛሬ ግን ፀሓይ ብርሃኗን ተነጥቃ እንደአሮጌ ጨርቅ ተጨማድዳ ከተጣላች በኋላ ጊዜን መለካት ትርጉም ሊኖረው አልቻለም በመሆኑም ጊዜ ከእንግዲህ ብዙም ረብ ያለውና ግምት ሊሰጠው የሚችል ዋነኛ ጉዳይ አይሆንም፡፡
መላእክትም ታላላቅ የሆነ አካላቸውንና ብሩህ የሆኑ ግዙፍ ክንፎቻቸውን እያርገበገቡ ክፍት በሆኑት የሰማያት ደጃፎች በኩል ወደ ምድር መውረዳቸውን ቀጥለዋል ይህም ቢሆን ታዲያ በፍርሃትና በትህትና ስሜት ተሞልተው ይታዩ ነበር።



የዚህም ዋነኛው ምክንያት አላህ የተቆጣበት ቀን በመሆኑ ነው ፣ መላእክት ብቻ ሳይሆኑ ፍጥረት የተባለ በሙሉ የአላህን በታላቅ ሁኔታ መቆጣት አውቋል:: ለእርሱ ጥራትና ልዕልና የተገባው ጌታ) ከዚያ በኋላ ተመልሶ እንደዚያ ባለ ሁኔታ በማይቆጣበት አኳኋን ታላቅ የሆነው ቁጣው ነድዷል
ይህን በመሰለ አስጨናቂ ቀን በበዳዮች ላይ የሚደርስ ቅጣት እጥፍ ድርብ እንደመሆኑ ይህን በማሰብ የሚመጣው ስነልቦናዊ ቅድመ ቅጣቱ (መርበድበድና በፍርሃት መራዱ እንደዚሁ በጣም ከባድ ነው፡፡


በዚያ ሁሉ ጽልመት የዋጠው ሁኔታ አንድና ብቸኛው የብርሃን ምንጭ ከመልአክት አካል የሚገኘው ብርሃን ነው እነርሱም ከሰማያት ቀበሌዎች ከወረዱ በኋላ በሰልፍ በሶፍ ተሰድረውና አንገታቸውን ደፍተው በፀጥታ ቆሙ የሰው ልጅ እነዚያ ታማኝና ቅን የአላህ አገልጋዮች የሆኑት መላእክት ቀኑ ይዞት የሚመጣውን ነገር በመፍራት አንገት መድፋታቸውን ሲያስተውል ብርክ ይዞ ያንጠረጥረው ጀመር።



በጭንቅና ስቃይ ብዛት ጐላ ብሎ የሚታየው የነበረው የሰው ልጅ ጅኖችና የዱር አራዊቶች በቢሊዮኖች የሚቆጠር ድምፅ አላህ ፊት መቆማቸውን ሊያስተውሉ ከትንሽ ሹክሹክታ በስተቀር ሁሉም ፀጥ ረጭ አለ እርሱም እጅግ በጣም ሩህሩህ የሆነው የልቅና ጌታ ነው።
ሰማያት ቀስ በቀስ እንደሽንኩርት እየተላጡ ተፈረካክሰው አለቁ እንዲሁም የድሮዋ ምድር ከአገልግሎት ውጪ በመሆን አንዴ በንና ጠፋች። ከመጀመሪያው ጀምሮ እስከ ዓለም ፍፃሜ የተፈጠረ ፍጡር ሁሉ በአዲሷ ምድር አንድም ሳይቀር ተሰበሰበ።


ይች ምድር አዲስ እንደተኮላ ብር የነፃችና ጥርት ያለች ስትሆን በእርሷም አንዳችም ዓይነት ኃጢያት አልተፈፀመባትም አዲሷ ምድር በፀሐይ አለመኖር ለረዥም ዘመናት ሸፍኗት ከቆየው ፍፁም ፅልመት ተላቅቃ በጌታዋ ብርሃን እነሆ እንደገና ወገግ አለች። ዛሬ ከጥንቷ ፀሐይም ሆነ ጨረቃ ያልሆነ ልዩና አዲስ በሆነ ብርሃን ሁሉም ነገር በግልጽ ይታይ ጀምሯል ይህም ጽልመት የተወገደው ብሩክ በሆነው መለኮታዊ ብርሃን በመሆኑ አጠቃላዩን ሁኔታ (ትዕይንት) ብርሃን በሰለጠነበት ሂደት የተቃኘ አደረገው፡፡


በዚህ ቅጽበት ግን አንድ አሳዛኝ ሁኔታ በአንድ ግለሰብ ላይ ተፈጠረ ይኸውም የታሪካችን መዋቅር ከሚሽከረከርባቸው ግለሰቦች አንዱ የሆኑት የቀድሞው ቅምጥል አለቃ መስሩር ዓይናቸው የታወረ መሆኑ ነው፡፡ ኃያሉ አላህ ከሌሎች ከሃዲያን ላይ ብርሃናቸውን በመውሰድ እውር እንዳደረጋቸው ሁሉ መስሩርም የዚህ እጣ ተቋዳሽ እንዲሆን ተደረገ
በዚህ ክስተት ወቅት መስሩር እጅግ ከመደንገጡና ከመፍራቱ የተነሣ ቃላት ሊገልጹት በማይቻል ሁኔታ መጮህ ጀመረ። ይሁን እንጂ ድምጹ ከደረቱ ሳይወጣ ለራሱ ብቻ በሚሰማ ሁኔታ ባክኖ ቀረ እነሆ ከዚህች ሰዓት በኋላም ዘላለማዊ በሆነው ኩነኔ (ቅጣት) ውስጥ እንደገባ ሙሉ በሙሉ አረጋገጠ።


ከዚያም እንዲህ ሲል አጉተመተመ ጌታዬ ሆይ ለምንድን ነው እውር አድርገህ የቀሰቀስከኝ? እኔ በምድረ ዓለም ሳለሁ በእርግጥ ዓይናማ የነበርኩ ሲሆን?


ይቀጥላል…
413 views16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 19:14:47
~

አንዳንድ ጊዜ ጽጌረዳዎች በድንጋዮች መካከል ይበቅላሉ ደስታም እንዲሁ ነው በሀዘን መካከል መንገዱን ያበጃል!
435 views16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 05:32:26 የመላእክት መታየት


ምድር በልቧ (በሆዳ) ውስጥ አንድም ፍጠር እስከማይቀር ድረስ ሙሉ በሙሉ ሙታንን በማውጣት መትፋት ቀጥላለች በዚህ ዓይነት ሁኔታ የሙታን ትንሳዔ ቀጥሎ የሰው ዘር ጂኖች ሰይጣናት የዱር አራዊት፣ ከብቶችና አእዋፋት ሁሉም በአንድ ምድር ላይ ተሰባስቦ ሲራኮት አጠቃላዩ የአጽናፈ ዓለሙ ህልውና ማክተምና መውደም የመጨረሻውን ደረጃ እየያዘ መጣ…


ምድር በደረሰው ከፍተኛ የፀሐይ ሙቀት ስብርብር ብላ በአቧራ ተውጣለች ከዋክብቶች ረግፈው የተበታተኑ ሲሆን ፀሐይ ደግሞ ሙቀቷ ሁሉ ጠፍቶ ተበታትና እንድትወድቅ ተደርጓል በዚህ ሂደት ላይ የፀሐይ ቀለም ከቢጫ አንፀባራቂነት ወደ ቀይነት ከዚያም ወደ ጥቁርነት ተቀየረ ከዚያም ኃይለኛ ፍንዳታ ከደረሰባት በኋላ ተበታተነች በዚህ ወቅት ሰማዩን እንዴ ፍልጥ በመተርከክ የመጨረሻ ሞቷን ሞተች ከዚያ በኋላ በሁሉም የአጽናፈ ዓለሙ ክፍል ውስጥ ጨለማው እየበረታ መጣ ከዚያ በፊት ከዋክብትና ጨረታ ረግፈው ስለነበር ምድር በጽልመት ተዋጠች፣ ፍጥረት የተባለ ባለበት ቦታ እንደተገተረ ሲሆን አንዳች እንቅስቃሴ አልነበረም።


መስሩር በገዛ ላቡ ሲጠመቅ እንዳልነበር ሁሉ አሁን ደግሞ ብርድ በሆዱ ውስጥ ገብቶ ያንጠረጥረው ጀምሯል የዓመዳይና በረዶ ክምር ምድርን እየሸፈናት ሲሆን ቅዝቃዜዋም አይጣል የሚያሰኝ ሆኖአል በዚህ ሁሉ መዓት የታወከው መስሩር የእውር ድንብሩን መቅሩርን ለማየትና ነገሮችን ለመለየት ቢሞክርም ፈጽሞ የሚቻል አልሆነም
ይህን በመሰለ ጭንቅና ጽልመት መሐል ሰማያት ተሰነጣጥቀው ወደቁ መለኮታዊው መስተዳድር በዚህ ሁሉ ድርጊት እያወጀ ያለው ያለፈው አጽናፈ ዓለሙን ሲመራና ሲገዛ የነበረው ደንብና ሥርዓት ሁሉ ያለቀለት መሆኑን ነው
ሰማያት ሲሰነጣጠቁ የነበረው ሂደት በመጀመሪያ እንደ ቀለጠ ነሀስ በሚመስል ሁኔታ ሲሆን ቀጥለው ደግሞ ብርማ መልክ በመያዝ ወደ ሚያስፈራ በጫማ መልክ ከተቀየሩ በኋላ ተጠቅልለውና ተሰነጣጥረው በመጨረሻ ቀይ መልክ በመያዝ ወደቁ…


ሰማያት በተሰነጣጠቁበት ጊዜ ደጃፎቿ በመከፋፈታቸው
እያወደሱና እያጠሩት ቢሆንም በመፈፀም ላይ ባለው ሁኔታ ግን መላአክት ወደ ምድር ብቅ ማለት ጀመሩ፡፡ እነርሱም አላህን በፍርሃት መዋጣቸው አልቀረም መስሩር ልቡ የድንጋጤ ከበሮ መደለቁን እንደቀጠለ ሲሆን ሊመጣ የሚችለውን መጥፎ ጉድ እየመጣ አጣጥፎ መጠባበቅ ብቻ ሆኗል እጣ ፈንታው ያም ቢሆን በዚህ ዓይነት ግራ የሚያጋባ ድብልቅልቅ ምን ያህል ጊዜ እንዳሳለፈ ለመገመት አልቻለም:: ሌላው ቀርቶ ሰማይ ተሰነጣጥቆ ከወደቀ በኋላ እንኳን ምን ያህል ጊዜ እንደተቆጠረ ለመገመት አዳጋች ሆነበት…

ይቀጥላል…
355 views02:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ