Get Mystery Box with random crypto!

ወርቃማ ንግግሮች

የቴሌግራም ቻናል አርማ golden_speech — ወርቃማ ንግግሮች
የቴሌግራም ቻናል አርማ golden_speech — ወርቃማ ንግግሮች
የሰርጥ አድራሻ: @golden_speech
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.15K
የሰርጥ መግለጫ

ሰው የለበስክ ሰው እንጂ ልብስ የለበስክ ሰው አትሁን.. ሰውነት የአለም ምርጡ ጌጥህ እሱ ነውና።
አስተያየት እንቀበላለን.. @Golden_SpeechBot
https://youtube.com/channel/UCgP-E0miz3BhJ0YAGJ2zCHg

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-07-05 07:16:32 1 ሰዎች ሞትን ቢረሱትም ሞት ግን ሰውን አይረሳም!

2 የሰውን ወንጀል አትከታተል የራስህን ወንጀል ትረሳለህና!

ሁሌም ስለራስህ ወንጀል አስብ!!
867 views04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 16:34:22
አጃዒብ ወገራዒብ!

ከዓለማችን አጥቢ ፍጡራኖች ትልቁ አሳ ነባሪ ወይም በፈረንጅኛው Whale የሚባለው በውቅያኖስ ውስጥ የሚኖር የአሳ ዝርያ ነው። በቅዱስ ቁርዓናችን ነቢዩላህ ዩኑስን (ዐለይሂ ሰላም) እንደዋጣቸው ቂሳው የተወሳለት ማለት ነው።

ይህ እጅግ ግዙፍና አጥቢ እንስሳ አስገራሚ የሆነ ባህርይ አለው ሴቷ አሳ ነባሪ ጡት ቢኖራትም እንደሌሎች እንስሳት ወይም የአሳ ዝርያዎች ለልጆቿ ጡቷን አታጠባም ይልቁንም ልጇ ጡት ሲፈልግ እዛው ወሀው ላይ ልጇ አጠገብ ትለቅለታለች ወተቱ ውሀው ላይ ይንቆረቆራል የአሳ ነባሪ ወተት high - fat content በፋት በቅባት በጣም የበለፀገ ስለሆነ እንደ ሌሎች ወተት ከውሀ ጋር አይቀላቀልም። ከዚያም ልጇ ከውሀው ላይ የረጨችውን ወተት ይጎነጨዋል።

አቡ ሙስዓብ
1.1K views13:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 08:10:57 "ሰዎችን በመሀይምነት እና አዝንጋቴ አትቀላቀላቸው በዒልም እይታና በንቃት ቢሆን እንጂ"
"ልጄ ሆይ በአላህ ላይ አደራህን (ከሱ አትራቅ) ከሱ ውጭ ያለው ነገር አይሸውድህ አገር አገሩ ሪዝቅም ሪዝቁ ነው (የሱ ነው)"

ደይደል ዓሪፊን ሱልጣነል ዐውሊያእ ጘውስ ሰይዲ ወመውላና አል ዐሪፍ ቢላህ መውላና ዐብድል ቃድር ከይላኒ/ጀይላኒ
1.1K views05:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-02 22:18:35 ኢፋዳ መጽሃፍን እንዳነበብኩት.................



በቅርቡ ከሀገር ካስመጣኋቸው መጽሃፍት መካከል አንዱ ኢፋዳ የተሰኘው የFuad Muna ልቦለድ መጽሃፍ አንዱ ነው ። ሁሉንም መጽሃፍ ት በወፍ በረር እየቃኘሁ 'የቱን ቀድሞ ላንብብ '' የሚለውን ባልወሰንኩበት በድንገት ኢፋዳን መጽሃፍን ጀመርኩ።

ኢፋዳ በ306 ገጾች ልዩ በሆኑ ምዕራፎች የተከፋፈለ መጽሃፍ ነው ። የምዕራፎቹ ክፍልፋይ ከሌሎቹ ለየት ያለ ፣ በቁጥር ሳይሆን በተመረጡ የዓረብኛ ፊደላት የተከፋፈለ ነው። የተመረጠው የአማርኛ ፎንት ለመጽሃፍ የተመለመደ ባይሆንም የሚያምር፣ትልቅ እና ደማቅ (BOLD) ነው ። ደማቅ እና ትልቅ መሆኑ ምናልባት የመጽሃፉን ገጽ በማብዛት የህትመት ወጪም ስለተወደደ ተጽእኖ ይፈጥራል የሚል ስጋት ፈጥሮብኛል። ቢሆንም ምናልባት ወጣቱ የሶሻል ሚዲያ ተጽእኖው ከንባቡ እያቃቃረው ስለሆነ እርሱን ታሳቢ በማድረግ ለመሳብ እና በቀላሉ ማንበቡን ለማበረታት ነው ብየ ወስጄዋለሁ ።

የመጽሃፉን ሰባ ገጾች ቀስ እያልኩ ያነበብኩ ቢሆንም ከ70 ገጽ ጀምሮ እስከ 306 ገጽ ያለውን 236 ገጹን ግን ትላንት ከተቀመጥኩበት ሳልነሳ ልጨርሰው ችያለሁ ። ይህን የነገርኳቸው የኔን ፈጣን አንባቢነት ለመግለጽ ሳይሆን የመጽሃፉን ስሜት ሰቅዞ ያዥነት ለመግለጽ መሆኑን እንድትረዱልኝ እፈልጋለሁ ። ዛሬ በማለዳ ስለ ኢፋዳ እንድከትብ ያደረገኝም እጅግ የተደሰትኩበት አዳሬን ሲያብሰስለኝ ያደረው ኢፋዳ መጽሃፍ ነው ።

ስለ መጽሃፉ ይዘት ዝርር ዳሰሳ በዚህ በፌስቡክ ገጽ ማቅረብ ባይቻልም ጠቅለል ያሉ ነጥቦችን አንስቼ ልቋጭ !

ኢፋዳ መጽሃፍ የልቦለድ መጽሃፍ ቢሆንም በገሃዱ ዓለም የምናውቃቸውን ስሞች እና በተወሰነ መልኩም ቢሆን የምናውቃቸው የሚመስሉ ታሪኮችን ተጠቅሟል። ኢፋዳ ታላቅ የሆነችው ኢስላማዊ ግዛት በታላቁ መሪ ኢማሙ አህመድ ከ500 አመት በፊት እንዴት እንደተመሰረተች እና ከተመሰረተች ከሁለት መቶ አመታት በኋላ እንዴት መፈራረስ እንደ ጀመረች እና ቀጣይ ደግሞ ማን ይታደጋታል ? የሚለውን ልብን በሚሰቅዝ መልኩ ይዞ የሚነጉድ ነው ። ኢማሙ አህመድ በታሪክ የምናውቀው ጀግናው ኢማሙ አህመድን የሚመስል እርሱ ራሱ ሳይሆን አይቀርም የሚያስብለን በሱ አምሳያ የተቀረጸ ጀግና ነው ።

በኢፋዳ መጽሃፍ ውስጥ በሶስት ዘመናት የነበሩ/ያሉ ባለታሪኮች ማለትም ከ500 አመታት በፊት ጀምሮ አሁን እስካለንበት ድረስ በተሰናሰለ መልኩ ቀርበዋል። ግዛቲቱን ከመሰረቱት ኢማም ጀምሮ መፍረስ እስከ ጀመረችበት ጊዜ ጀምሮ ዲናቸውን አፍቃሪ እና ተቆርቋሪ የሆኑ ጀግኖች በምን መልኩ እንደኖሩ ፣መፈራረስም እንዴት እንደጀመሩ ፣የመታደግ ተስፋቸውም ጭምር በሚገርም መልኩ ተዋቅሮ ቀርቧል ።

ከኢፋዳ ከወደድኩት ነገር ውስጥ የሴት ጀግኖች ሚና በኢስላም ውስጥ ምን ይመስላል የሚለውን በሚገባ ይዞ የቀረበ መሆኑ ነው ። መጽሃፉ ባለፈው የሚያስቆጭ ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱም በተስፋ የሚያነሳሳ ነው ። አይደፈሬ የሚመስሉ ሃቆችንም በሚገባ ያስቀመጠ ፣ ያሁኑን ትውልድ ክፍተትም የሚጠቁም ነው ።

ሌላኛው ኢፋዳ መጽሃፍ ታላቁን የአላህ ኪታብ ቁርዓንን እንድናፈቅር የሚያደርጉ ያ ትውልድ ከቁርአን ጋር የነበረውንም ትስስር በሚገባ የሚያሳይ ነው ።
በጥቅሉ ኢፋዳ መነበብ ያለበት መጽሃፍ ነው ። በተለይ ወጣቱ ከሶሻል ሚዲያ ጊዜያችሁ ቀንሳችሁ እንድታነቡት ግብዥየ ነው።

ፉአድ ሙና መጽሃፉን ከመጻፍ እና ከማሳተም ባሻገር መጽሃፉን ለማስተዋወቅ እና ለመሸጥ የተጠቀመበት መንገድ በራሱ ለሌሎች መጽሃፉ አሳታሚዎች ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ ሁኖ አግኝቼዋለሁ ።
ደራሲው በዚህ ሳይገታ የንባብ አድማሱን በማስፋት እንዲሁም ስራዎቹን ባለሙያዎች ሂስ እንዲያደርጉለት በመጋበዝ ከዚህ በላይ በርካታ ስራዎችን እንደሚያበርክትልን ተስፋ አደርጋለሁ ።

(አብዱረሂም አህመድ)
1.5K views19:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-02 00:39:12
ዘመናዊው ከእንቅልፍ የመቀስቀሺያ የአላርም ስርአት ከመጀመሩ በፊት አባቶቻችን፤በሚፈልጉት ሰዓት ይቀሰቅሳቸው ዘንድ የሚበሩ ሻማዎች ላይ ሚስማሮችን ይሰኩ ነበር።የሻማው አካል የሚቀልጥበትን ሰዓታት ስለሚያውቁ ሚስማሩን በተገቢው ቦታ ላይ ይሰኩ ነበር።ሻማው ቀልጦ ሚስማሩ የተሰካበት ቦታ ላይ ሲደርስም ሚስማሩ ከስር ወደ ተዘጋጀለት ድምፁ የጎላ እቃ ላይ ያርፋል።ያ ድምፅም የተኛውን ሰው የመቀስቀስ አቅም ነበረው።

የስሜት ህዋሳት በቀደመው ትውልድ ተገቢውን ትኩረት ተሰጥቷቸው፤በተገቢው መልኩም አገልግሎት ላይ ይውሉ ነበር።
1.4K views21:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 22:35:34
እና በዓሉ ዝምብሎ ትንሽ በዓል እንዳይመስልህ። አራት ቀን መሆኑ በራሱ ትልቅ በዓል እንደሆነ አመላካች ነው።
ደግሞም አትሰስቱ ብለዉናል ሸይኻችን ሲያስተምሩን። ነቢዩ ኢብራሂም የአብራካቸዉን ክፋይ ልጃቸውን ያህል ለማረድ ዝግጁ ሆነው አንተ በግ ተወደደብኝ ብለህ አትንቀጥቀጥ።

ትናንት ከትናንት ወዲያ ያላረድክ ዛሬም ነገም ፀሐይ እስክትጠልቅ ድረስ ማረድ ትችላለህ ተብለሃል።

ዒድ እና በግ
"የዒዱ በግ" ደስ የሚል ጉዞ ከተሰኘው መጽሐፌ ላይ ያንብቡ።
1.7K views19:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-29 21:53:40
#ሐጅ_የኢማን_ቤት

ይሕ እስልምናችን ግን ምን ዓይነት ነው?! እንዴት ነው የሚያምረው የሚገርመው! ትዕዛዝ (አምር) ኾኖ የሚመጣው ሰዎችን ከነፍሳቸው ለማስጠንቀቅ ብቻ አይደለም። ነፍሳቸውን እንዳይበድሉም ጭምር ነው። ለምሳሌ፦ ጹሙ እያለ ያዝናል አይደል? አትጹም ብሎም ያዝዛል! መጾም ከተከለከለበት ጊዜያት መካከል አንደኛው ቀን ላይ እንገኛለን። እነዚህ ኹለት ቀናት የመብላትና የመጠጣት ቀናት ናቸው። ብሉ፣ ጠጡ ብሎ የሚያዝ እምነት አለን፣ ሌላ ጊዜ ጹሙም ይለናል። ነፍስን መጉዳት ነፍስን በብርቱ ይዞ እንድትጎሳቆል ማድረግ ኢስላማችን ይከለክላል። በተቃራኒው ነፍስ ክፋት እንዳታበዛ በሚበቃት መልኩ መቆጣጠርም ያስፈልጋል። ነፍስን በመግራት ስም ከሰውነት ጎዳና ስናወጣት ገፍላ ውስጥ በመግባት መንገድ ልታስተን ትችላለች፤ ነፍስን ከዐቅሟ በላይም ስንከባከባት ታይቶ የማይታወቅ ነፍሲያ (ኢጎ) ውስጥ ትከተናለች።

እነ ኑሮ ተወዷል፣ እነ ችግርና ማጣት በአላህ ፈድልና በረከት ድባቅ የሚመቱባቸው ቀናት ናቸው። ሆዱ ስጋ ሳይገባ የሚያድር አማኝ የለም ማለት ይቻላል።

እየበላን፣ እየጠጣን በምላሹም አላህን በተክቢራ እያተለቅን ወዲህም እያመሰገንን በሰለዋት ደግሞ እየተመቻቸን እንቀጥላለና።

★ ዛሬ ሑጃጆች ጀመራት ላይ ናቸው። ድንጋይ ይወረውራሉ። ሐሳባቸው ሰይጣንን መውገራቸው ነው። አባታችን ኢብራሂም የጌታን ትዕዛዝ እንዳይፈጽሙ ሰይጣን ሊያግዳቸው ሲሞክር ከነፍሳቸው ጋር ታግለው ሰይጣንን ያበረሩበትን ትርክት የምናስታውስበት ክስተት ነው።

አላሁ አክበር ወሊላሂል ሐምድ
1.8K views18:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-29 18:04:04
ሰሀባዎች ዐረፋ ደርሶ ዒድ ከሰገዱ በኋላ ኡድሒያዎቻቸውን በማረድ ተጠምደዋል። አከባቢው ግርግሩ እና ትርምሱ የእርድ አጅሩን ለማግኘት በሚጣደፉ ሰሀባዎች ተሞልቷል።

ረሱል ሰዐወ ፍፁም እርጋታ በተሞላ ስሜት ውስጥ ሁነው ሁለት ቀንዳም በጎችን ይዘው ለማረድ ይዘጋጃሉ።

ሰሓባዎች ግራ ተጋብተዋል፤ "ኡድሒያ አንድ ሁኖ ሳለ እሳቸው እንዴት ሁለት ይይዛሉ" በሚል እየተብሰለሰሉ ነው።

ረሱል ሰዐወ በጉን አስተኙት፤ ቢለዋውን ከበጉ አንገት ላይም አሳርፈው ፍቅር እና ናፍቆት በቋጠረ አንደበት፦‹‹ጌታዬ! ይህ እርድ የኔ፣ የቤተሰቦቼ እና የእርድ አቅም ለሌላቸው የኡመቶቼ ኮታ ነው ተቀበለኝ›› ብለው ተክቢራት እያደረጉ አረዱት።

እንዴት ቢያፈቅሩን ይሆን ከቤተሰባቸው ተርታ ያሰለፉን!
1.7K views15:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-25 02:54:10 #ከቂያማ_ምልክቶች መካከል፦

1/ ዝሙት ይስፋፋል
2/ ወንዶች ሀር ይለብሳሉ
3/ ሙዚቃ እንደሚፈቀድ ይነገራል
4/ ሴቶች ዘፋኞች በአጫዋችነት ይያዛሉ
5/ መጥፎ ቃላቶችን መለዋወጥ ይበዛል
6/ ዝምድናን መቁረጥ በስፋት ይስተዋላል
7/ ታማኝ ሰውን እንደ ከዳተኛ መቁጠርና መወንጀል
8/ ከዳተኛን ማገዝና ማቅረብ
9/ ድንገተኛ ሞት መከሰት
10/ መስጅድን እንደ መተላለፊያ መንገድ መጠቀም
11/ ጥሪያቸው ወይም ተልእኮአቸው ተመሳሳይ የሆነ ሁለት ቡድኖች ይፋ ጦር ይማዘዛሉ (የአልይና የሙአውያ ውጊያን ያመለክታሉ)
12/ የዘመን መቀራረብ ወይም የጊዜ መፍጠን (በረካ ማጣት)
13/ ፈተናዎች ይደራርሳሉ፣ ተንኮል ይስፋፋል
14/ ኢልም ከህፃናት ይፈለጋል
15/ የመሬት መንቀጥቀጥ
16/ ሰውነታቸውን አግባብ ባለው ልብስ ያልሸፈኑ ሴቶች ይበዛሉ
17/ እውቀት የሌላቸው ሰዎች ህዝባዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ይወስናሉ
18/ ሰላምታ በትውውቅ ላይ ብቻ ይመሰረታል
19/ ውሸት መናገር ይስፋፋል
20/ የንግድ ቤቶች ተቀራርበው ይገነባሉ።
21/ ለሰይጣን አገልግሎት የሚውሉ ግመሎችና ለሰይጣን አገልግሎት የሚውሉ ቤቶች ይገነባሉ! ማለትም፦
1-አንድ ሰው ከሚጠቀምባቸው ውጭ ያሉ ግመሎች በስድ ሲለቀቁ ሰይጣን ይጋልባቸዋል።
2-ከመኖሪያ ቤት ውጭ ያሉ ትርፍ ቤቶች ለረጅም ጊዜ ሰው ሳይገባባቸዉ ከቆዩ የሰይጣን መኖሪያ ይሆናል።

22/ ሰዎች በመስጅድ ውበት ይፎካከራሉ በውስጡ ይመፃደቃሉ።
23/ ሺበታቸውን በጥቁር ቀለም የሚያጠቁሩ ሰዎች ይመጣሉ።
እነዚህ ሰዎች የጀነትን ሽታ እንኳን አያገኙም።
24/ ሰዎች አላህን የመታዘዝ ባህሪያቸው ይመነምናል። ለአኬራ መስራትም ይቀንሳል።
25/ ስስት ይስፋፋል፣ ሁሉም ሰው ግለኛ ይሆናል፣ አዋቂ እውቀቱን ለማካፈል ይሳሳል።
26/ ሰዎች አላማውን በማያውቁት ውጊያ ውስጥ ይሳተፋሉ (ይጋደላሉ)።
"ነፍሴ በእጁ በሆነው ጌታ እምላለሁ በሰዎች ላይ ይህ ዘመን ይመጣል። ገዳይ በምን ምክንያት እንደገደለ አያውቅም-ተገዳይ በምን ምክንያት እንደተገደለም አያውቅም።

27/ የህዝብ ገንዘብ ያለ አግባብ ይመዘበራል።
28/ አማና (ታማኝነት) ይጓደላል።
29/ ባል ሚስቱን እየታዘዘ እናቱን ይበድላል።
30/ በአባቶች ላይ እየተፌዘ (አባት ሳይከበር) ጓደኛ ይከበራል።
31/ በመስጅድ ውስጥ ጩኸት ይበራከታል።
32/ ተንኮሉ ተፈርቶ ሰው ይከበራል-ችሎታና ስነ-ምግር ግን የለውም።
33/ ፖሊስ ይበዛል፤ ይህም ማለት ወንጀል መበራከቱን ያመለክታል።
34/ አንድ ሰው በእውቀቱ አናሳ ሆኖ እና በባህሪውም ገና ያልተገራ ሆኖ ሳለ ድምፁ የሚያምር ሆኖ በመገኘቱ ብቻ ሶላት እንዲመራ (እንዲያሰግድ) ይደረጋል።

35/ ሚስት ባሏን በንግድና በስራ ላይ ትጋራለች።
36/ ብእር ይበራከታል፤ ድርሰት እና ህትመት ይስፋፋል።
37/ ልጅ መመኪያ መሆኑ ቀርቶ መተከዣና መቆጫ ይሆናል።
38/ የዝናብ እጥረት ይስተዋላል።
39/ መኪና ይፈለሰፋል። "ከኡመቶቼ መካከል ወደ መጨረሻዉ የሚመጡት ሱሩጅ ወይም (መኪና) ላይ ይሳፈራሉ።
የመጎጎዣ አይነት ነው በመስጅድ በሮች ያቆሙታል (ይወርዳሉ) ሴቶቻቸው ግን የለባሽ እርቃን ናቸው።
40/ ፊትና በመብዛቱ ሳቢያ ሞትን መመኘት።
41/ ኢራቅ ማእቀብ ይጣልባታል - ምግብ እና እርዳታ ትከለከላለች።
42/ በመቀጠልም ሻም (ሶሪያ፣ ሊባኖስ፣ ዩርዳኖስ እና ፍልስጤም) ምግብና እርዳታ ይከለከላሉ ማእቀብ ይጣልባቸዋል።
43/ የነብዩ ሙሐመድ (ሰ•ዐ•ወ) ከዚህ አለም በሞት መለየት እንደ አንድ የቂያማ ቀን መድረስ ምልክት ተወስዷል።
44/ በይተል መቅደስ (እየሩሳሌም) በሙስሊሞች ቁጥጥር ስር መግባት።
45/ በጅምላ ጨራሽ በሽታም ሆነ ጦርነት የሰው ህይወት መጥፋት።
46/ ሙስና፣ ማጭበርበርና የዋጋ ንብረት እያየለ መምጣት።
47/ በአረቦችም ሆነ በሌሎች ወገኖች ቤት ውስጥ ጣልቃ ገብነት እና ፊትና (መከራ) ይስተዋላል።
48/ በሙስሊሞች እና በሮማውያን (አውሮፓ እና አሜሪካ) የጋራ ስምምነት ይፈረማል።

አውፍ ኢብን ማሊክ (ረ•ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ (ሰ•ዐ•ወ) እንዲህ ብለዋል፦
•የቂያማ-ቀን• ከመድረሱ በፊት ስድስት ነገሮች ይከሰታሉ፦
> የኔ ሞት
> ከዚያም በይተልመቅዲስ ይከፈታል
> ከዚያም ሁለት ሞት እውን ይሆናል
> አንድ ሰው መቶ ዲናር ቢሰጠው እንኳን ምንም አይመስለውም
> ከዚያ በኋላ ደግሞ ፊትና ይከሰታል።
> ከዚያም በናንተና በነጮች መካከል ስምምነት ይኖራል። ይከዷችሁል። ሰማኒያ (80) አላማ ይዘው ይመጣሉ እያንዳንዱ አላማ ደግሞ 12 ሺህ (ንዑስ አላማ) አለው።

ያአላህ! እዘንልን ከምናውቀውም ሆነ ከማናውቀውም ፊትና ጠብቀን፣ በዲናች አትፈትነን! በዲናችን ላይ የመጣውን ፊትና አንሳልን ያረብ!
ሙባረክ
2.6K views23:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-24 20:57:09 ሚስት ባሏን እንዴት ከሲጋራ ሱስ ማላቀቅ እንደምትችል እያሰበች ግራ ተጋብታ መፍትሔ ፍለጋ ትብሰለሰላለች። በጤናው ላይ ጉዳት እንደሚያደርስ የሰጠችው ምክር አላሳምን ብሎት በሐሳብ ትባትላለች። እያቦነነ ለሚያጨሰው ሲጋራ የሚያወጣው ገንዘብ የእሱ ብቻ ሳይሆን የቤተሰቡም ድርሻ እንዳለበት ነግራ በየቀኑ አምስት ዶላር እንዲሰጣት ጠየቀች። ከሱስ አልላቀቅ ስላላት ሌላ ዘዴ መቀየሷ ነበር።

በቀን አስር ዶላር ለመክፈል ዝግጁ መሆኑንና ሰላም ብቻ እንድትሰጠው ነግሯት በየቀኑ አስር ዶላር እየከፈለ ማጨሱን በመቀጠሉ ተደሰተ።

የሚሰጣትን አስር አስር ዶላር ፊት ለፊቱ ማቃጠሏን ቢመለከትም ለብዙ ቀናት ታግሷታል። አሁን ግን ውስጥ ውስጡን ይከነክነው ይዟል
"ገንዘቡን ያለ አግባብ እያቃጠልሽ በከንቱ እየባከንሽው ነው" ሲል ኮነናት።
"ሁለታችንም በተለያየ መንገድ ገንዘብ እያቃጠልን ነው" አለችው።

አሰበ። ከዚያም ስህተቱን በሚገባ ተረዳ። ምን ያህል ትልቅ ስህተት እንደሰራ ታወቀው ወደ አፉ የላካትን ሲጋራ በረጅሙ ሳበና በአፍ በአፍንጫው ቀዳዳ እያንቦለቦለ ሚስቱን ፈትቶ ማጨሱን ቀጠለ።

እንደዚህ ዓይነት ሰውም አለ ለማለት ነው።
2.0K views17:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ