Get Mystery Box with random crypto!

🇪🇹 E.Z መረጃ 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ ezmerejaet — 🇪🇹 E.Z መረጃ 🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ ezmerejaet — 🇪🇹 E.Z መረጃ 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @ezmerejaet
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4
የሰርጥ መግለጫ

እንዴት አደርሽ ኢትዮጵያዬ ! 🇪🇹

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2022-10-31 13:40:45 የሀገር መከላከያ ሰራዊት የደረሰበት ግፍ ጥቅምት 24 ቀን ታስቦ እንደሚውል ተገለፀ

ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በሰሜን ዕዝ መከላከያ ሰራዊት ላይ የተፈፀመው ጥቃት ታስቦ እንደሚውል የኢትዮጵያ መንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል ።

ዕለቱ በኢትዮጵያ ክህደት እና ባንዳነት እንዳይደገም ለማስገንዘብ ታስቦ የሚከበር እንደሆነ ተገልጿል ። ቀኑ በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል ታስቦ እንደሚውል የተገለፀ ሲሆን ሁሉም የመንግሥት እና የግል ተቋማት ዝግጅት ማድረግ እንዳለባቸው ተገልጿል ።

ዕለቱ ጥቅምት 24  መቼም አልረሳም በሚል መሪ ቃል አራት ሰዓት ሲሆን ሁሉም በየአለበት በመሆን እንደሚከበር ተነግሯል ።
@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
5.7K viewsedited  10:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 11:39:10 240 ኩንታል ቡና በመዝረፍ በአዳማ ከተማ መጋዘን ውስጥ የደበቁ 12 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

ተጠርጣሪዎቹ የእርዳታ ድርጅት ሙሉ ዱቄት ከነተሳቢው ከአዳማና ሻሸመኔ ዘርፈዋል

በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ ከ10 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የተለያዩ ንብረቶችን ሲዘርፉ የነበሩ 12 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የወረዳው ፖሊስ አስታውቋል።የተለያዩ የግል እና የመንግስት ተሽከርካሪዎችን በመጠቀም ከሻሸመኔ ከተማ አንድ መንግስታዊ ያልሆነ የእርዳታ ድርጅት ሙሉ ዱቄት የጫነ ተሽከርካሪ ከነ ተሳቢው የዘረፉ መሆናቸውም ተገልጿል።

ግለሰቦቹ በተመሳሳይ በአዳማ ከተማ ሙሉ የእርዳታ ዱቄት የጫነ ተሽከርካሪ ከነተሳቢው ሰርቀው ሊሰወሩ ሲሉ ነው በቁጥጥር ስር ውለዋል።በተጨማሪም ተጠርጣሪዎቹ በባሌ ዞን ከሚገኘው ትራኮ ጣኢር ጅብሪል ከተባለ የቡና አምራች ድርጅት 240 ኩንታል ቡና ዘርፈው አዳማ ከተማ ባለ መጋዘን ውስጥ ደብቀው የተያዙ መሆናቸውን የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት ምክትል ዳይሬክተር ዋና ኢንስፔክተር ብርሃኑ ጫላ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

የተዘረፈው 240 ኩንታል ቡና ግምቱ ከ7 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጣ ነው።12ቱ ተጠርጣሪ ግለሰቦች የግለሰብ እና የመንግስት ተሽከርካሪዎችን የሰሌዳ ቁጥር እየቀያቀሩ የሚዘርፉ ሲሆን በግለሰቦቹ እጅ ከ20 በላይ የተለያዩ ተሽከርካሪዎች ሰሌዳ ተይዟል።

በቁጥጥር ስር በዋሉት ተጠርጣሪዎች ላይ በበቂ ሁኔታ በመረጃ የተጠናከረ የወንጀል ምርመራ ተደርጎ መዝገቡ ለአቃቤ ህግ መላኩን ዋና ኢንስፔክተር ብርሃኑ ጫላ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
5.9K views08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 11:39:10 ሞቃዲሾ
አልሸባብ ቅዳሜ'ለት በሞቃዲሾ ባደረሰው የአጥፍቶ ጠፊ የፈንጂ ጥቃት ከ100 በላይ ሰዎች እንደተገደሉ እና ሌሎች ከ100 በላይ የሚገመቱ ሰዎች እንደቆሰሉ የሱማሊያ ዜና ምንጮች ፖሊስን ጠቅሰው ዘግበዋል። አልሸባብ ጥቃቱን የፈጸመው በትምህርት ሚንስቴር ቅጥር ግቢ ውስጥ እና አቅራቢያ ባፈነዳቸው መኪና ላይ የተጠመዱ ፈንጂዎች ነው። የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ገልጸው፣ ፕሬዝዳንቱ መንግሥታቸው በአልሸባብ ላይ የሚያደርገውን ውጊያ ግን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
5.4K views08:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 11:38:51 መርጌታ ይሃንስ ባሕላዊ  መዳኒት ቀማሚ የምነሰጣቸው አገልግሎቶች በጥቂቱ ።
1,  መፍትሔ_ሥራይ (የጠላት ድግምት መሻሪያ) 0908104860
2,  ለቡዳ
3,  ለቁራኛ
4, #መጠብቅ (ከጠላት ከሚላክ ሟርት የሚጠብቅ)
5,  ለጋኔን
6, ለማንኛውም ዓይነት በሽታ መፍትሔ
7, ለራእይ (በህልም የሚያሳይ)
8,  ለፀር (ለጠላት)
9, ዓቃቤ_ርእስ (ጠላት እንዳይጎዳን የሚጠብቅ)
10,  ለዘኢያገድፍ (ለትምህርት የማያስጠፋ የማያስጥል)
11,ለመክስተ_ምስጢር (ትምህርት የሚያጎብዝ)
12, ለመፍትሔ_ሀብት(ሀብቱ በጠላት ድግምት ለተሰወረበት)
13, መስተፋቅር
14 ;ለግርማ_ሞገስ (ሰው እንዲያከብረን እንዲወደን)
15,ለመድፍነ_ፀር (ጠላት እንዳይናገረን እና እንዲፈራ
16, ለሌባ(እንዳንሰረቅ እንዳንዘረፍ የሚጠብቅ)
17, የትዳር አጋር ላጣ ወይም ላጣች
የሚያስገኝ
18,ለምስያጥ ለገበያ (ገበያ እንዲቀናን እንድናገኝ)
19; መስተኃድር (ከብት ቢጠፋብን ሳይበሉ በሰላም እቤታቸው
የሚያመጣ)
20, መንድግ(በገበያ ገንዘብ ማግኛ)
21, ለዓይነ_ጥላ (የፍራቻ መንፈስ ማስለቀቂያ)
22, ለልሳነ_ሰብእ
23, ለበረከት
24,ለእግረ_መልስ (ጥሎ ለጠፋ ሰው መመለሻ ማምጫ)
25,ምስሀበ_ነዋይ(ገንዘብ ማግኛ)
26,ጸሎተ_ዕለታት
27,ለጽሑፍ ለስእል ለከበሮ ለበገና ለክራር በእጂ ለሚሰሩ
28, ንባብ ስናነብ ቀልጣፋ የሚያረግ
29, ለከበሮ
30,ለመፍዝዝ (ጠላት እኛን ለማጥቃት ሲሞክር አጠገባችን ሲደርስ
መጣላቱን አስረስቶ አፍዝዞ የሚያስቀር የማያስመታ)
31, ለሙግት
32,ለሰላቢ
33,ለስንፈት ወሲብ
34,ዘኢያወርድ ( ለወንዶች በፆታዊ ግንኙነት ወቅት የዘር ፍሬ ቶሎ
እንዳይወርድ የሚያረግ አግዶ የሚያቆይ)
35, ለመደንግፅ (የተጣላን ሰው እኛን ሲያይ እንዲደነግጥ እንዲፈራ
የሚያረግ)
36,ለጥይት (ጥይት የማያስመታ)
37, ለዱላ( ዱላ የማያስመታ)
38,መንስኤ_እስኪት (ለወንድ የመራቢያ አካሉ ለደከመ ላነሰ)
39,ህገ_ጠብቅ (የትዳር አጋራችን ወደሌላ እንዳይሄድ የሚያስር
እንዳይዘሙት የሚከለክል)
40, ለአይነ_ሰብእ (ከሰው አይን የሚጠብቅ)
41;ለአዙሪት
42; ለአስቸጋሪና ተመላላሽ ሲህር
43;ለሪህ በሽታ
44;የመገጣጠሚያ ህመም
45;ለጉልበት ድርቀት
46;የባት ህመም
47;የወገብ ህመም
48;የአንገትና ትከሻ ህመም
49;የከረመ ደረቅ ሳል
50;ለደም ግፊት
51;የሆድ መረበሽ
52;የከፋ የሆድ ድርቀት
53;በመኝታ ሽንት ለሚያመልጠው
54;የአእምሮ ጭንቀት፣ ድብርት፣         ከሰው  መገለል፣እንቅልፍ ማጣት
55; እንቅልፍ መብዛት
56;የተለየ የቆዳ ህመም
57;ክብደት ለመቀነስ
58;የእንቅርት በሽታ
59;ራስ ምታት ከሚከተሉት ህመሞች ጋ
60; አይን አካባቡ ውጥረት ካለ
61; የሳይነስ ህመም
62;የሆድ ድርቀትና የሆድ ህመም
63;የወር አበባ ችግር ካለ
64;የወገብ መንሸራተት ካለ
65;ውጥረትና የአእምሮ ጭንቀት
66;ለከፍተኛ ራስ ምታት
67;ማስታወስ፣ንቃት፣ተነሳሽነት ለሌላቸው
68;ለድምፅ መታፈን
69;ከአጫሽነት ለመላቀቅ
70;ራስን ስቶ በስቃይ ለሚኖር
0908104860 ይደውሉልን
5.5K views08:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-31 09:04:24 ሩሲያ ዩክሬን ከጥቁር ባህር ወደቦች እህል ወደ ውጭ እንድትልክ ከተደረገው ስምምነት ራሷን አገለለች።

ሩሲያ ከዩክሬን ወደቦች የተከማቸ የምግብ እህል ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ በተመድና ቱርክ አሸማጋይነት ከዩክሬን ጋር ከደረስኩበት ስምምነት "ራሴን አግልያለሁ" ብላለች። ሩሲያ ቅዳሜ'ለት ውሳኔዋን ያሳወቀችው፣ "ዩክሬን ጥቁር ባሕር ላይ በነበሩ መርከቦቼ ላይ የድሮን ጥቃት ፈጽማለች፤ ከዩክሬን ወደቦች እህል የሚጭኑ መርከቦችም የጥቃቱ ዒላማ ሆነዋል" በማለት ነው።

ተመድ፣ አሜሪካ እና የአውሮፓ ህበረትን ጨመሮ በርካታ ሀገራት የሩሲያን እንርምጃ የተቃወሙ ሲሆን፤ ሩሲያ በበኪሏ እርምጃው በዩክሬን ግዴለሽ ተግባር የመጣ ነው ብላለች። የሩሲያና ዩክሬንን ስምምነት ተከትሎ፣ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለኢትዮጵያዊያን ተረጅዎች ከአንድም ሁለቴ በ10 ሺዎች የሚቆጠር ስንዴ ከዩክሬን ገዝቶ ወደ ኢትዮጵያ ማጓጓዙ ይታወሳል። የሩሲያ ውሳኔ ዩክሬን ምርቶቿን ለውጭ ገበያ እንዳታቀርብ እንቅፋት ይሆናልም ተብሏል።

via - Alain

@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
6.0K viewsedited  06:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-13 08:38:55
በትምህርትና ምዘና ላይ የሚደረግ አሉታዊ ዘመቻ ተቀባይነት የለውም -የአማራ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን

በትምህርትና ምዘና ላይ የሚደረግ አሉታዊ ዘመቻ ተቀባይነት የለውም ሲል የአማራ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ገለጸ፡፡

የክልሉ ኮሙኒኬሽን ጉዳዩን አስመልክቶ በስተላለፈው መልዕክት÷ በትምህርትና ምዘና ላይ የሚደረግ አሉታዊ ዘመቻ በእውቀት ላይ የተመሰረተ የሀገር አለኝታ የሆነ ትውልድ የማፍራት ርዕይን የሚጻረር ነው፡፡

ስለሆነም ድርጊቱ በሰው ልጅ ላይ ከሚፈጸም የዘር ማጥፋት ወንጀል ተለይቶ የሚታይ አይደለም ነው ያለው፡፡

መንግሥት ለዚህ ጉዳይ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት የምዘና ሥርዓቱ የትምህርት ጥራትን ብቻ ሳይሆን የተማረ ሰው ሃይልን ከፍታ በሚያስጠብቅ እና የምዘና ስርዓቱን ስብራቶች ለዘለቄታው በሚጠግን መንገድ የመጓዝ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑም አንስቷል።

በመንግሥት እየተወሰደ ያለውን የስርዓተ ትምህርት ለውጥም ሆነ የምዘና ሥርዓት ውጤታማነትን ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ አሠራሮችን መደገፍና ለተፈፃሚነታቸው መተባበር ለመንግሥት እና ለትምህርት አመራርና ተቋማቱ ብቻ የሚተው ተግባር አለመሆኑም ተጠቁሟል፡፡

በእውቀት የበለፀገ፣ አመለካከቱ ያደገ፣ በክህሎቱ የተካነ እና ውጤታማ የሆነ ትውልድ የመፍጠር ኃላፊነት የሁሉም ዜጋ እንደሆነ ማስገንዘቡንም ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በተመሳሳይ የምዘና ሥርዓቱ ያለበትን ትውልድ አጥፊ ችግር ለማረም በሚደረገው ጥረት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል፡፡

@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
3.0K views05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-12 20:22:13
" ፈተና አቋርጠው ለወጡ ተማሪዎች ምንም አይነት እድል አይሰጥም " - ትምህርት ሚኒስቴር

የትምህርት ሚኒስቴር ፈተና አቋርጠው ለወጡ ምንም አይነት እድል አይሰጥም ብሏል።

ሚኒስቴሩ ማምሻውን በሰጠው መግለጫው ፤ በአማራ ክልል በመቅደላ አምባ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ባህርዳር እና ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲዎች 12 ሺህ 787 ተማሪዎች ጊቢውን ለቀው መውጣታቸውን ገልጿል።

ፈተና አቋርጠው ለወጡ ተማሪዎች ሚኒስቴሩ ምንም አይነት እድል እንደማይሰጥ አሳውቋል።

@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
3.5K views17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-12 20:17:22 በስልጤ ዞን የአራት ዓመት ሴት ህፃን በጅብ ተበልታ ህይወቷ አለፈ

በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ ማዞሪያ ተብሎ ከሚጠራዉ የገጠር ከተማ የ4 አመት ሴት ህፃን በጅብ ተበልታ ህይወቷ ማለፉን የደቡብ ክልል ፖሊስ ሚዲያ ኮምኒኬሽ ዲቨዥን ሀላፊ ምክትል ኮማንደር ታጁ ነጋሽ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

መስከረም 27 ቀን ከምሽቱ 1 ሰዓት ገደማ በርካታ ልጆች በመጫወት ላይ የነበሩ ሲሆን ከመካከላቸው የ4 ዓመቷ ልጅ ጅቡ አንገቷን ይዞ ሲሮጥ እንደነበር ተገልጾል፡፡በሰዓቱ በአካባቢው የነበሩ እማጮች ድምፅ በማሰማታቸው ጅቡ ህፃኗን ጥሎ የሮጠ ቢሆንም የህፃኗን ህይወት ማትረፍ አልተቻለም ተብሏል፡፡

በደቡብ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ጅብ በሰዉ ላይ ጥቃት ሲያደርስ የሚስተዋል ሲሆን ህፃናት ከሌላዉ የህብረተሰብ ክፍል በበለጠ የጥቃቱ ሰለባ የሚሆኑት የሚደርስባቸዉ ጥቃት ለመከላከል አቅም የሌላቸዉ በመሆኑ ተመሳሳይ ጥቃት እንዳይከሰት ወላጆች ለህፃናት ልጆቻቸዉ ተገቢዉ ጥበቃ ማድረግ አለባቸው ሲሉ ኮማንደር ታጁ ነጋሽ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
3.6K views17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-12 19:26:20 በዛሬው የአዲስ ነገር መረጃ የተንቀሳቃሽ ምስል መረጃዎቻችን

አንፈተንም ብለው ጥለው ስለወጡት የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች

ጌታቸው እረዳ ምን አጋጠመው?

ኮማንድ ፓስቱ መግለጫ አወጣ ስለምን ጉዳዮች አነሳ የሚለውን የናስሳለን

በመቀሌው ፍንዳታ እነማን ተጎዱ

ሙሉ መረጃውን ይመልከቱ






4.1K views16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-12 18:08:30
#ተጠናቋል

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የመጀመሪያ ዙር የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ  የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና መጠናቀቁን አሳውቋል።

አገልግሎቱ ፤ " የፈተና ኩረጃና ስርቆት ከፍተኛ የፈተና ደንብ ጥሰት ናቸው። ህግ ይከበራል። " ብሏል።

ለስራው መጠናቀቅ አወንታዊ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ምስጋና አቅርቧል።

@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
4.9K viewsedited  15:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ