Get Mystery Box with random crypto!

በስልጤ ዞን የአራት ዓመት ሴት ህፃን በጅብ ተበልታ ህይወቷ አለፈ በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ ማዞ | 🇪🇹 E.Z መረጃ 🇪🇹

በስልጤ ዞን የአራት ዓመት ሴት ህፃን በጅብ ተበልታ ህይወቷ አለፈ

በስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ ማዞሪያ ተብሎ ከሚጠራዉ የገጠር ከተማ የ4 አመት ሴት ህፃን በጅብ ተበልታ ህይወቷ ማለፉን የደቡብ ክልል ፖሊስ ሚዲያ ኮምኒኬሽ ዲቨዥን ሀላፊ ምክትል ኮማንደር ታጁ ነጋሽ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

መስከረም 27 ቀን ከምሽቱ 1 ሰዓት ገደማ በርካታ ልጆች በመጫወት ላይ የነበሩ ሲሆን ከመካከላቸው የ4 ዓመቷ ልጅ ጅቡ አንገቷን ይዞ ሲሮጥ እንደነበር ተገልጾል፡፡በሰዓቱ በአካባቢው የነበሩ እማጮች ድምፅ በማሰማታቸው ጅቡ ህፃኗን ጥሎ የሮጠ ቢሆንም የህፃኗን ህይወት ማትረፍ አልተቻለም ተብሏል፡፡

በደቡብ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ጅብ በሰዉ ላይ ጥቃት ሲያደርስ የሚስተዋል ሲሆን ህፃናት ከሌላዉ የህብረተሰብ ክፍል በበለጠ የጥቃቱ ሰለባ የሚሆኑት የሚደርስባቸዉ ጥቃት ለመከላከል አቅም የሌላቸዉ በመሆኑ ተመሳሳይ ጥቃት እንዳይከሰት ወላጆች ለህፃናት ልጆቻቸዉ ተገቢዉ ጥበቃ ማድረግ አለባቸው ሲሉ ኮማንደር ታጁ ነጋሽ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

@Ezmerejaet
@Ezmerejaet