2022-10-11 12:26:50
አሸባሪው ህወሓት በቆቦ ከተማ በርካታ ንጹሃን ዜጎች መግደሉን ዘጋርዲያን የዓይን እማኞችን ዋቢ አድርጎ ዘገበ
አሸባሪው ህወሓት በአማራ ክልል ዳግም ወረራ በፈጸመበት ወቅት በቆቦ እና አካባቢዋ በርካታ ንጹሃን ዜጎችን መግደሉን የዓይን እማኞችን ጠቅሶ ዘጋርዲያን የተሰኘው የእንግሊዙ ጋዜጣ አጋልጧል።
በሽብር ቡድኑ አማካኝነት መሳሪያ ባልታጠቁ 17 ንጹሃን ላይ ግድያ የተፈጸመው ከቆቦ ከተማ ወደ አዲስ አበባ በሚወስደው መንገድ ላይ መሆኑንም የዓይን እማኞቹ ለዘጋርዲያን ገልጸዋል።
አሸባሪው ህወሓት በአማራ ክልል በቆቦ ከተማ ዳግም ወረራ በፈጸመበት ወቅት ይቃወሙኛል ብሎ ያሰባቸውን በርካታ ንጹሃን ዜጎችን መግደሉን የዜና ምንጩ ዘግቧል።
በነሃሴ ወር አሸባሪው ቡድኑ በቆቦ ከተማ ወረራ ባካሄደበት ወቅት በንጹሃን ዜጎች ላይ የግድያ ወንጀል ብቻም ሳይሆን የንብረት ላይ ዘረፋ መፈጸሙንም ነዋሪዎች ለዘጋርዲያን ተናግረዋል።
በአሸባሪ ቡድኑ የተፈጸመው የንጹሃን ግድያ ቤት ለቤት በተካሄደ አሰሳ ጭምር እንደሆነ ሰባት የዓይን ምስክሮችን ጠቅሶ ዘጋርዲያ በዘገባው አስነብቧል።
@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
6.1K viewsedited 09:26