Get Mystery Box with random crypto!

🇪🇹ኢትዮ University

የሰርጥ አድራሻ: @ethiouniversity1
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 126.79K
የሰርጥ መግለጫ

Promotion ለምትፈልጉ ....🌀 @Euads🌀
@hilwauniversity
Use this for idea and question @ethiouniversity1bot

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2024-03-25 13:10:14
#BahirDarUniversity

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለዘጠኝ ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል።

የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ ምሁራኑ በየመስኳቸው የነበራቸውን ልዩ አበርክቶ በመገምገም የፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷቸዋል።

የፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው ምሁራን፦

1. ሙሉጌታ አድማሱ ደለለ (Bio Systems Engineering)
2. ታምራት ተስፋዬ ይመር (Biorefinery Engineering)
3. አስማማው ጣሰው ወልዴ (Animal Production)
4. መላኩ አለማየሁ ወርቄ (Horticulture)
5. የሻምበል መኩሪያው ቸከኮል (Animal Nutrition)
6. አቻምየለህ ጋሹ አዳም (Land Governance)
7. ምርኩዝ አበራ አድማሱ (Plant Pathology)
8. ታደሠ መለሠ መራዊ (Curriculum and Instruction)
9. አስራት ዳኘው ከልካይ (Curriculum and Instruction)

ቦርዱ የምሁራኑን የማስተማር ሥራ፣ የምርምር ተሳትፎ፣ የማህበረሰብ አገልግሎት እና በተቋማዊ ጉዳይ ያላቸውን አስተዋፆ በመገምገም የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ማፅደቁን ከተቋሙ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
13.1K views10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-25 00:02:40
ከ 128 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል የተባለዉ የመጀመሪያው የኒወክለር ህክምና ማዕከል ስራዉን መጀመሩ ተነግሯል

በኢትዮጵያ በተለይ በግሉ የጤና ዘርፍ የመጀመሪያው እንደሆነ የተነገረለት የኒዉክለር ህክምና ማዕከል ስራዉን መጀመሩን ያስታወቀው ፓዮኔር ዲያግኖስቲክስ ማዕከል ለአጠቃላይ ግንባታው ከ 128 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ አድርጎበታል።

በ 72 ሚሊዮን ብር የኒዉክለር ህክምና መሳሪያ ወጪ የተደረገበት ሲሆን ለሀገሪቱ የመጀመሪያው እንደመሆኑ መጠን ህክምናውን ለማግኘት ይወጣ የነበረዉን ከ 100 ሺህዎች በላይ ገንዘብ ወጪ ማስቀረት መቻሉ ተሰምቷል።

በመንግሥት ደረጃ ከ 10 ዓመት በፊት የተጀመረ ቢሆንም አሁን ላይ ህክምናውን የሚሰጥ ማዕከል አለመኖሩ ተገልጿል ።

የኒውክለር ህክምና እጅግ አነስተኛ መጠን ያለው ጨረር የሚያመነጭ ንጥረ ነገርን (ራዲዮፋርማሲዪቲካል) በመጠቀም ለታካሚዎች የምርመራና የህክምና አገልግሎት የሚሰጥበት የህክምና ዘርፍ ነዉ።

በሁሉም የህክምና ዘርፎች ተፈላጊ የሆነዉ የኒዉክለር ህክምና በተለይ በካንሰር ፣ በልብ እና በነርቭ ታካሚዎች ላይ እጅግ ጉልህ አስተዋጾ እንዳለው ይነገራል።(ካፒታል)

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
14.6K views21:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-24 19:29:18
#AdigratUniversity

በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁና በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት በ2014 ዓ.ም ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድባችሁ መማራችሁ ይታወቃል።

ይሁን እንጂ በ2013 ዓ.ም ከዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ስትወጡ ያልጨረሳችሁት የተወሰኑ የትምህርት ዓይነቶች መኖራቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

በመሆኑም ከዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ስትወጡ ያላጠናቀቃችሁት ትምህርት ያላችሁ ተማሪዎች በዚህ ሴሚስተር እንድታጠናቅቁ ከመጋቢት 28 እስከ 30/2016 ዓ.ም ባለው ግዜ መመዘገብ ትችላላችሁ ተብሏል።

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
14.0K views16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-24 13:25:26
ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት አዳዲስ የአጭር ጊዜ ስልጠናዎች ለመስጠት ስርዓተ ትምህርት አዘጋጅቷል።

ኢንስቲትዩተ የሁለት መደበኛ ስልጠና ስርዓተ ትምህርት ክለሳም አድርጓል።

12 ሙያዎች ፍላጎትን መሰረት ያደረገ የአጭር ጊዜ ስልጠናዎች ለመስጠት አዲስ ስርዓተ ትምህርት መዘጋጀቱን የኢንስቲትዩቱ ስልጠናና አቅም ግንባታ ዘርፍ ም/ዋ/ዳይሬክተር ሀብታሙ ክብረት ገልጸዋል፡፡

ኢንስቲትዩቱ በዓለም ባንክ EASTRIP ፕሮጀክት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ያካሔደውን የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት መሰረት በማድረግ የስርዓተ ትምህርት እና የመማሪያ ሰነድ ማዘጋጀቱን ጠቁመዋል።

ስርዓተ ትምህርት ከተዘጋጀላቸው ሙያዎች መካከል፦

- የውጭ ቋንቋዎች ስልጠና (እንግሊዘኛ፣ አረብኛ እና ፈረንሳይኛ)
- የትኩስ መጠጥ አገልግሎት (Bartender Service)፣
- የመጠጥ አግልግሎት (Barista Service)፣
- የሥጋ ቤት አገልግሎት (Butchery)፣
- ጤናና ውበት (Wellness and Spa Service) ይገኙበታል፡፡

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
15.0K views10:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-24 13:24:39 የኢትዮጵያ AI ጠበብቶች ሀገር በቀል የሆነ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በመጠቀም ድንቅ የተባለ መተግበሪይያ ሰሩ።

መተግበሪይው እንግሊዘኛ ለመፃፍ grammar ትክክል ነው አይደለም ብሎ መጨነቅ ያስቀረ ነው የተባለለት ነው ከዛም በተጨማሪ አማርኛ በእንግሊዘኛ መጻፍ የሚያስችል ነው።

አገልግሎቱን ለማግኘት ከነጻ የሙከራ ጊዜ በሁዋላ ክፍያ እንደሚኖረው የድርጅቱ ሀላፊ ተናግረዋል።
14.0K views10:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-23 19:06:57
#BahirDarUniversity

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም አዲስ ለተመደቡ እና በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ለተከታተሉ ተማሪዎች ጥሪ አደረገ።

በዚህም በ2016 ዓ.ም አዲስ የተመደቡ Freshman ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስትከታትለው ቆይተው የማለፊያ ውጤት በማምጣት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተመደበ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው ከመጋቢት 26 እስከ 28/2016 ዓ.ም መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል።

የምዝገባ ቦታውም ፦
➤ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሰላም ግቢ
➤ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በግሽ አባይ ግቢ ነው ተብሏል።

በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታቸውን አቋርጠው ለአንደኛ ዓመት የመጀመሪያ ሴሚስተር ለመልሶ ቅበላ የሚያበቃ ውጤት ያላቸውና የመልሶ ቅበላ ፎርም የሞሉ ተማሪዎች ምዝገባ መጋቢት 30/2016 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዛሬ ያወጣው ጥሪ በማካካሻ መርሐ ግብር (Remedial Program) በ2016 ዓ/ም አዲስ የተመደቤ ተማሪዎችን #አይመለከትም ተብሏል።

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
17.2K views16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-22 21:00:27
#HawassaUniversity

በ2016 ዓ.ም ለስፔሻሊቲ ስልጠና በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ሬዚደንት ሐኪሞች ምዝገባ መጋቢት 18 እና 19/2016 ዓ.ም እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ምዝገባ ለማድረግ ኦፊሺያል ትራንስክሪፕት በኢሜይል registrar@hu.edu.et ወይም በፖ.ሳ.ቁ. 05 አስቀድሞ ማስላክ ይጠበቅባችኋል።

የምዝገባ ቦታ፦
በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሬጅስትራር ቢሮ

ተመዝጋቢዎች ከዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ ሬጅስትራር እና ድኅረ ምረቃ ትምህርት ቤት “Admission” እና “Acceptance” ደብዳቤ መያዝ ይኖርባችሀኋል።

ማንኛውም ተመዝጋቢ አስቀድሞ ይሠራበት ከነበረ ተቋም ክሊራንስ ማቅረብ ይጠበቅበታል።

ኦረንቴሽን መጋቢት 20/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
14.3K views18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-22 15:47:02
#Update

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ ማድረጋቸውን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በቅርቡ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡

የፀጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች በስተቀር በአብዛኛው የአገሪቱ አካባቢዎች የተማሪዎች ምዝገባ መጠናቀቁም ተገልጿል።

የፈተናው ሕትመት በቀጣይ ቀናት እንደሚጀመር ለኢሳት የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥም አረጋግጠዋል፡፡

ለ3ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተናው፤ ዘንድሮ ለተፈጥሮ ሳይንስ እና ማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስኮች ለእያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች እንዲሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑ አይዘነጋም፡፡

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
15.8K views12:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-21 19:07:25
#ክፍትየስራማስታወቂያ

ቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ መስኮች መምህራንን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

➤ የሥራ መደብ፦ በተለያዩ ሙያ መስኮች
➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 23
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ 2ኛ ዲግሪ
➤ የሥራ ቦታ፦ ቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ
➤ የማመልከቻ ጊዜ፦ ማስታወቂያው ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ባሉት አምስት ተከታታይ የሥራ ቀናት

አመልካቾች ስትመዘገቡ የትምህርት እና የሥራ ልምድ ማስረጃ ዋናውና የማይመለስ ኮፒ ማቅረብ ይጠበቅባችኋል፡፡

በኢሜይል ለመመዝገብ፦ 𝘒𝘥𝘶𝘩𝘳𝘥@𝘬𝘥𝘶.𝘦𝘥𝘶.𝘦𝘵

ለተጨማሪ መረጃ፦ +251252401076

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
18.0K views16:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-21 10:37:16
#AddisAbabaUniversity

በ2016 ዓ.ም ለስፔሻሊቲ ስልጠና አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የተመደባችሁ ሬዚደንት ሐኪሞች የድኅረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (GAT) ማክሰኞ መጋቢት 17/2016 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

ምዝገባ እስከ ሰኞ መጋቢት 16/2016 ዓ.ም ቀን 6፡00 ሰዓት በኦንላይን https://portal.aau.edu.et. እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
17.4K views07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ