Get Mystery Box with random crypto!

🇪🇹ኢትዮ University

የሰርጥ አድራሻ: @ethiouniversity1
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 126.79K
የሰርጥ መግለጫ

Promotion ለምትፈልጉ ....🌀 @Euads🌀
@hilwauniversity
Use this for idea and question @ethiouniversity1bot

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2024-03-16 10:29:17 ለ ሬሜዲያል!! ቅናሽ

Remedial Tutorial በልዩ ሁኔታ ገፅ ለገፅ በ Video ሙሉ Chapter ከነ ጥያቄዎቹ ጭምር ተሰርቷል።

ለ Remedial ተማሪዎች Maths እና Physicsን ከ 9-12 ሙሉ ቲቶሪያል በ 250 ብር ብቻ መመዝገብ ይችላሉ። ለ Social ተማሪዎች Maths ብቻ 150 ብር ከፍላችሁ ማግኘት ይችላሉ ።

ከሌሎቹ በተለየ መልኩ የተዘጋጀ ቲቶሪያል ስለሆነ ምንም ሳትጨነቁ ፈተና ትሰራላችሁ ።

ለ Freshman ተማሪዎች MidExam  እና Final Exam መስራት እና አሪፍ ውጤት ለማምጣት የኛን ቲቶሪያል በ 300 ብር ያገኛሉ።

ለመመዝገብ @Euads ላይ አካውንት ወስዳችሁ መመዝገብ ይችላሉ።

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
14.1K views07:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-16 06:04:41
#WachemoUniversity

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ሬዚደንት ሐኪሞች ምዝገባ መጋቢት 9 እና 10/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ተመዝጋቢዎች በንግስት እሌኒ መታሰቢያ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በመገኘት የሥራ ቅጥር መፈፀም እንዳለባችሁ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

ለምዝገባ እና ለሥራ ቅጥር የሚያስፈልጉ አስፈላጊ ሰነዶችን ከላይ ከተያያዘው የዩኒቨርሲቲው መልዕክት ይመልከቱ።

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
15.0K views03:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-14 13:45:04
በ2016 ዓ.ም ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ የአንደኛ ዓመት እና የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ የካቲት 20 እና 21/2016 ዓ.ም መካሔዱ ይታወቃል፡፡

ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ሳትመዘገቡ የቀራችሁ ተማሪዎች እሰከ ነገ መጋቢት 6/2016 ዓ.ም ብቻ መመዝገብ እንደምትችሉ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
17.8K views10:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-13 17:22:04
#DebreMarkosUniversity

ደብረ ማርቆሰ ዩኒቨርሲቲ ለ2016 ዓ/ም ነባር እና አዲስ አንደኛ ዓመት መደበኛ ቅድመ-ምረቃ እና የሬሜዲያል ተማሪዎች ጥሪ አድርጓል፡፡

በዚህም መሠረት የምዝገባ ጊዜዉ እንደሚከተለዉ ተገልጿል፦

- የ1ኛ ዓመት 2ኛ ወሰነ ትምህርት ነባር ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርት ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ያላችሁ ነባር ተማሪዎች ከመጋቢት 16-17/2016 ዓ.ም

- በ2016 ዓ.ም የተመደባችሁ አዲስ ገቢ ፍሬሽማን እና የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ከመጋቢት 16-17/2016 ዓ.ም

ማሳሰቢያ:
* ለነባር 1ኛ ዓመት ተማሪዎች እና የሪሚዲያል ትምህርት ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ያላችሁ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄደዉ #በየነበራችሁበት ካምፓስ መሆኑን እናሳዉቃለን፡፡

* በሀገር አቀፍ የማለፊያ ዉጤት ያመጣቹህ አዲስ የአንደኛ ዓመት(ፍሬሽማን) ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄደዉ #በዋናዉ ግቢ መሆኑን እናሳዉቃለን፡፡

* የ2016 ዓ.ም አዲስ ገቢ የሪሜድያል ተማሪዎች በስማችሁ ቅደም ተከተል መሰረት ስማችሁ ከA-G የሚጀምር የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች እና ስማችሁ ከA-H የሚጀምር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በቡሬ ካምፓስ #የምትመዘገቡ ሲሆን ሌሎች ደግሞ በዋናዉ ካምፓስ የምትመዘገቡ መሆኑን እናሳዉቃለን፡፡

* አዲስ ገቢ ተማሪዎች በሙሉ የ8ኛ ክፍል ካርድ፣ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት እና የ12ኛ ክፍል ሰርቲፊኬት ዋናውና ኮፒው እንዲሁም ስምንት 3x4 የሆነ ጉርድ ፎቶግራፍ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡

በተለያየ ምክንያት ትምህርታችሁን አቋርጣችሁ የመልሶ ቅበላ ፎርም የሞላችሁ 1ኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡


@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
19.1K viewsedited  14:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-13 16:48:30
ለትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና አቻ ግመታ አገልግሎት ፈላጊዎች በሙሉ!

የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና አቻ ግመታ አገልግሎት ፈላጊዎች የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት ባላችሁበት ሆናችሁ ከዚህ በታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ https://neta.gov.et ካመለከታችሁ በኋላ፡-

1. መስፈርቱን የምታሟሉ፡-

1.1. በSMS መልእክት የምትመጡበት ቀነ ቀጠሮ ይደርሳችኋል ነገር ግን ከቀነ ቀጠሮው በፊት ወደ ባለሥልጣን መ/ቤቱ ብትመጡ አገልግሎት መስጠት የማንችል በመሆኑ እንዳትጉላሉ እናሳስባለን፤
1.2. ቀነ ቀጠሮ መቀየር ቢያስፈልጋችሁ በSMS/በኢ-ሚይል/በስ.ቁ(+251) 0111 26 14 52 /(+251)0111 26 16 23 በመደወል አዲስ ቀነ ቀጠሮ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

2. መስፈርቱን ለማታሟሉ፡-

2.1 . ያላሟላችሁት ማስረጃ ወይም ምክንያት በSMS መልእክት የሚደርሳችሁ በመሆኑ ሳታሟሉ መምጣት የለባችሁም፤

2.2 . ያላሟላችሁት ማስረጃ ካላችሁ በድጋሚ እንድታሟሉ እና ማሟላታችሁ ተረጋግጦ በSMS መልእክት ሲደርሳችሁ ብቻ እንድትመጡና እንዳትጉላሉ እናሳስባለን፡፡
3. በሀገር ውስጥ ተምራችሁ የትምህርት ማስረጃችሁን ለማረጋገጥም ሆነ በውጭ ሀገር ተምራችሁ የአቻ ግመታ ለማሰራት በኦንላይን ካመለከታችሁ በአካል ብትመጡ የማናስተናግድ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
15.5K viewsedited  13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-13 11:48:29
#MaddaWalabuUniversity

በ2016 ዓ.ም ለቀዶ ሕክምና እና ለማህፀንና ፅንስ ሕክምና ስፔሻሊቲ መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ሬዚደንት ሐኪሞች ምዝገባ መጋቢት 12 እና 13/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

በተጠቀሱት ቀናት ብቻ በዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር (ጎባ ካምፓስ) በአካል በመገኘት ምዝገባ አድርጉ የተባለ ሲሆን ትምህርት መጋቢት 16/2016 ዓ.ም እንደሚጀምር ተገልጿል።

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
15.9K viewsedited  08:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-12 19:31:24
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሀኪምና መምህር ዶ/ር ሙሐመድ ከድር የዕውቅና ሽልማት ተበረከተላቸው
*********
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሀኪምና መምህር ዶ/ር ሙሐመድ ከድር ለህክምና ሙያና ትምህርት እድገት ላደረጉት አስተዋፅኦ ከኢትዮጵያ ሀኪሞች ማህበር የዕውቅና ሽልማት ተበረከተላቸው።

የኢትዮጵያ ሀኪሞች ማህበር 60ኛ ዓመታዊ ኮንፈረንሱን ከየካቲት29_መጋቢት01/2016ዓ.ም በአ.አ ያካሔደ ሲሆን፣ዶ/ር ሙሐመድ ከድር በህክምናው ዘርፍና በመማር ማስተማር ሒደቱ በርካታ ምሁራንን በማፍራት ለሀገራቸው ያደረጉትን አስተዋፅኦ በመጥቀስ የዕውቅና ሽልማት አበርክቶላቸዋል።

የጎንደር ዩኒበርሲቲ ህክምና ት/ቤት ዳይሬክተር ዶ/ር ሙሉጌታ አያሌው በበኩላቸው የህክምና ማህበሩ ስለሰጠው እውቅና አመስግነው፣ዶ/ር ሙሐመድ ከድር የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህ/ጤ/ሳይንስ ኮሌጅ ህክምና ማስተማር ከጀመረበት ጊዜ ጀምረው ከተማሪነት እስከ አንጋፋ መምህርነት እያገለገሉ እንደሚገኙ ገልፀዋል፤ ለወደፊቱም ከፍተኛ አስቸዋፅኦ ለሚያደርጉ አንጋፋ መምህራን ለስራቸው ክብር ተመሳሳይ ዕውቅና ይሰጣል ብለዋል።

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
13.7K views16:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-12 13:41:15
#JimmaUniversity

ጅማ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ሬዚደንት ሐኪሞች ምዝገባ መጋቢት 5 እና 6/2016 ዓ.ም. መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ተመዝጋቢዎች ከምዝገባ ቀናት አስቀድመው የመጀመሪያ ዲግሪ ኦፊሽያል ትራንስክሪፕት ለጅማ ዩኒቨርሲቲ ዋና ሬጅስትራር በፖ.ሳ.ቁ. 378 ማስላክ ይጠበቅባችኋል፡፡

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
14.2K views10:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-11 21:34:41
በመውጫ ፈተና ኩረጃና ሌሎች የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ ተሰረዘ
....................................................
መጋቢት 2/2016ዓ.ም (ትሚ) በመውጫ ፈተና ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት፣ መኮረጅና የተለያዩ የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ መሠረዙን የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ መጋቢት 2/2016 ዓ.ም ለሁሉም የመንግስትና የግል ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል።

የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙት 114 (አንድ መቶ አስራ አራት) ተፈታኞች ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ መሠረዙንና የሚወሰዱ ተጨማሪ እርምጃዎች በቀጣይ የሚገለጽ መሆኑ በደብዳቤው ተመልክቷል ።

ከየካቲት 6-11/2016 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የመንግስት ተቋማት በተሰጠው ሁለተኛ ዙር የመውጫ ፈተና 119, 145 ተፈታኞች ተፈትነዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ጥራትን ለማረጋገጥ ከጀመራቸው ሪፎርሞች አንዱ የሆነው መውጫ ፈተና ተመራቂዎች በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው ተገቢውን እውቀትና ክህሎት መቅሰማቸውንና ብቁ መሆናቸውን ዒላማ ያደረገ በመሆኑ ፈተናው በጥብቅ ዲስፕሊን የሚመራ ነው።

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝
16.4K views18:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-11 19:21:25
ትምህርት ሚኒስቴር "ለትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥና ለአቻ ግመታ" የወጣ መመርያ ፀድቆ ሥራ ላይ መዋሉን አስታውቋል፡፡

ሥራ ላይ ከዋለ አንድ ሳምንት ያለፈው መመርያው፤ የኃይማኖት ነክ ተመራቂዎች የትምህርት ማስረጃ የምዘና አገልግሎት እንደማያገኙ መገለፁን ሪፖርተር ጋዜጣ የደረሰውን ሰነድ በመጥቀስ ዘግቧል፡፡

የትምህርት ማስረጃ ለማረጋገጥ መሟላት ያለባቸው፦

- የሚረጋገጠው ማስረጃ ትምህርት ማጠናቀቁን ለማረጋገጥ የተጠየቀበት ማመልከቻ፣
- አስፈላጊ መረጃዎች በባለሥልጣኑ የመረጃ ቋት ውስጥ አስቀድሞ ማስመዝገብ፣
- የከፍተኛ ትምህርት የመግቢያ ሰርተፊኬት ማቅረብ፡፡

የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ማስረጃ ለማጣራት መሟላት ያለባቸው፦

- የመጀመሪያ ዲግሪ ትራንስክሪፕት፣
- የከፍተኛ ትምህርት የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ መግለጫ ሰርተፊኬት፣
- የዲፕሎማ ትራንስክሪፕት፡፡

የድኅረ ምረቃ ዲግሪ የትምህርት ማስረጃ ለማረጋገጥ መሟላት ያለባቸው፦

- የሁለተኛ ዲግሪ የምስክር ወረቀት፣
- የመመረቂያ ጽሑፍ፣
- የመጀመሪያ ዲግሪ ትራንስክሪፕትና ሌሎችም ይጠቀሳሉ፡፡

በባለሥልጣኑ ዕውቅና ከተዘጋ ተቋም የተዘዋወሩ ተማሪዎች የትምህርት ማስረጃቸው ተቀባይነት እንደማያገኝ ሰነዱ ያብራራል፡፡

የምዘና አገልግሎት ምስክር ወረቀት የጠፋበት ግለሰብ ሁሉንም መሥፈርቶች በድጋሚ በማሟላት ምትክ የምዘና ምስክር ወረቀት እንደሚሰጠው መመርያው ይገልጻል፡፡

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
14.9K views16:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ