የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሀኪምና መምህር ዶ/ር ሙሐመድ ከድር የዕውቅና ሽልማት ተበረከተላቸው ********* የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሀኪምና መምህር ዶ/ር ሙሐመድ ከድር ለህክምና ሙያና ትምህርት እድገት ላደረጉት አስተዋፅኦ ከኢትዮጵያ ሀኪሞች ማህበር የዕውቅና ሽልማት ተበረከተላቸው። የኢትዮጵያ ሀኪሞች ማህበር 60ኛ ዓመታዊ ኮንፈረንሱን ከየካቲት29_መጋቢት01/2016ዓ.ም በአ.አ ያካሔደ ሲሆን፣ዶ/ር ሙሐመድ ከድር በህክምናው ዘርፍና በመማር ማስተማር ሒደቱ በርካታ ምሁራንን በማፍራት ለሀገራቸው ያደረጉትን አስተዋፅኦ በመጥቀስ የዕውቅና ሽልማት አበርክቶላቸዋል። የጎንደር ዩኒበርሲቲ ህክምና ት/ቤት ዳይሬክተር ዶ/ር ሙሉጌታ አያሌው በበኩላቸው የህክምና ማህበሩ ስለሰጠው እውቅና አመስግነው፣ዶ/ር ሙሐመድ ከድር የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህ/ጤ/ሳይንስ ኮሌጅ ህክምና ማስተማር ከጀመረበት ጊዜ ጀምረው ከተማሪነት እስከ አንጋፋ መምህርነት እያገለገሉ እንደሚገኙ ገልፀዋል፤ ለወደፊቱም ከፍተኛ አስቸዋፅኦ ለሚያደርጉ አንጋፋ መምህራን ለስራቸው ክብር ተመሳሳይ ዕውቅና ይሰጣል ብለዋል። ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች ቻናል https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0 Share share ለተጨማሪ መረጃ ╔═══════════╗ @ethiouniversity1 @ethiouniversity1 @ethiouniversity1 ╚═══════════╝ 13.7K views16:31