Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Construction

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethioengineers1 — Ethio Construction E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethioengineers1 — Ethio Construction
የሰርጥ አድራሻ: @ethioengineers1
ምድቦች: የውስጥ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.69K
የሰርጥ መግለጫ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ ከዲዛይን ,ቅየሳ ጀምሮ እስከ ፊኒሺንግ ሁሉንም
👷‍♂እናማክራለን
🏢ዲዛይን እናደርጋለን
📚ሙያዊ ድጋፍ እና እገዛ እናደርጋለን
🏗በጥራት እና በጊዜ ፍጥነት እንገነባለን
📲 0953138434(eng sintayehu melese) ወይም
ለሃሳብ እና ኣስተያየት
@Ethiocon143bot ይጠቀሙ

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 35

2022-05-10 14:10:03 #ሲሚንቶ
*** *
"የሲሚንቶ ፋብሪካዎች አከፋፋይ ወኪሎቻቸውን ከግብይት ሥርዓቱ እንዲያስወጡ ታዘዙ

ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርቶቻቸውን የሚያከፋፍሉላቸውን ወኪሎች (ኤጀንት) ከገበያ ሥርዓት ውስጥ አስወጥተው ምርታቸው በቀጥታ እንዲሸጡ አዘዘ፡፡ ሚኒስቴሩ ለአሥር የሲሚንቶ ፋብሪካዎች በጻፈው ደብዳቤ ፋብሪካዎቹ ያስወጧቸውን የሲሚንቶ አከፋፋይ ኤጀንቶች ብዛትና ስም ዝርዝር በደብዳቤ እንዲያሳውቁትም አሳስቧል፡፡"
ሪፖርተር

#እትዮ_ኮንስትራክሽን
3.7K viewsENG Sintayehu Melese, 11:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-08 12:08:13 ተቋራጭን ከሳይት ስለማባረር/Expel right/

በዚህ ጽሁፍ ተቋራጭን ከግንባታ ስፍራ/ሳይት የማባረር መብት ለማን የተሰጠ ነው?በየትኛው ህግ?በምን ሁኔታ?በየትኛው የውል አይነት?በዚህ ጊዜ ማን ምን መስራት አለበት?የሚሉትን በአጭሩ ለመጠቆም እንሞክራለን፡፡
#ይህ መብት ያለው የትኛው አካል ነው? የሚለውን በተመለከተ ተቋራጭን ከግንባታ ሳይት/ከግንባታ ስፍራ ለማባረር መብት ያለው አሰሪው ነው፡፡ስለዚህ መብቱ የግንባታው ባለቤት ወይም የአሰሪው ነው፡፡ስለዚህ ይህን መብት ተቋራጮች ሆኑ አሰሪ ያልሆነ ሌላ አካል ተግባራዊ ሊያደርገው አይችልም ማለት ነው፡፡
#በየትኛው ህግ? ለሚለው ምላሹ በፍትሀብሄር ህጉ እና በጀኔራል ኮንዲሽነን ኦፍ ኮንትራክት ነው፡፡በዝርዝር ሲታይ፡-
-በግንባታ ውሎች በተለይ ጀኔራል ኮንዲሽነን ኦፍ ኮንትራክት መጠቀም የተለመደ ነው፡፡እነዚህ ጀኔራል ኮንዲሽኖች በራሳቸው ህግ አይደሉም፡፡እዚህ ላይ አንዳንድ የህግ ባለሙያዎች እንደ መመሪያ እና ህግ ስለሚቆጥሩት ይህ የግንዛቤ ክፍተት መታረም ይኖርበታል፡፡የግንባታ ውል ተዋዋዮች በስምምነታቸው እነዚህን ጀኔራል ኮንዲሽኖች የውሉ አካል ሲያደርጓቸው በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 1731 መሰረት በተዋዋዮች መካከል እንደ ህግ ሆነው ይቆጠራሉ፡፡እዚህ ላይ ሌላው ጉዳይ ስፔሻል ኮንዲሽን ኦፍ ኮንትራክት ተብለው የሚቀመጡት ከጀኔራል ኮንዲሽኑ ድንጋጌዎች የተፈጻሚነት ቅድሚያ ይኖራቸዋል፡፡ለምሳሌ ከነዚህ ጀኔራል ኮንዲሽኖች ውስጥ የሲቪል ግንባታ ስራዎች ቋሚ የውል መተዳደሪያ/Standard condition of contract for the construction of civil work projects/ አንዱ ነው፡፡ይህ ጀኔራል ኮንዲሽን በከተማ ልማት ሚኒስቴር በኩል የተዘጋጀ ሲሆን ይዘቱ በዋናነት ከFIDIC 1987 version የተወሰደ ነው፡፡በአብዛኛው MoWUD 1994 ተብሎ ይጠራል፡፡ሆኖም ዋናው ነጥብ ተዋዋዮች ጥቅም ላይ ያዋሉትና የውላቸው አካል ያደረጉት የትኛውን ጀኔራል ኮንዲሽን እንደሆነ መለየትና ማወቅ የግድ ይላል፡፡
-ከዚህ አንጻር MoWUD 1994 ክሎዝ 63 ተቋራጭን ከግንባታ ስፍራ/ሳይት የማባረር መብትን አስመልክቶ በዝርዝር አስቀምጦታል፡፡በዚህ ድንጋጌ መሰረት በዋናነት አማካሪ መሀንዲሱ ለአሰሪው የተቋራጩን እንደውሉ ያለመፈጸም ሲያሳውቅ በተለይም ተቋራጩ ስራውን እንደተወው አማካሪው ሲያስታውቅ፣ተቋራጩ በአማካሪ መሀንዲሱ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው ለ28ቀናት ስራውን ሳይጀምር ሲቀር፣በመሀንዲሱ ተቀባይነት የላቸውም የተባሉ የግንባታ ቁሳቁሶችን በ28 ቀናት ውስጥ ከሳይት ያላስወጣ እንደሆነ፣በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ እየተሰጠው ስራውን በውሉ አግባብ ለመፈጸም ፈቃደኛ ያልሆነ እንደሆነ፣አማካሪ መሀንዲሱ እየከለከለው የስራውን ክፍል ለሌላ ተቋራጭ አሳልፎ የሰጠ እንደሆነ ወይም ተቋራጩ የከሰረ እንደሆነ አሰሪው የ14 ቀን ማስጠንቀቂያ በመስጠት ተቋራጭን ከግንባታ ስፍራ/ሳይት ማባረር የሚችል ይሆናል፡፡በዚህ ጊዜ ውሉ ይቋረጣል ማለት ነው፡፡/Termination of contract/
-በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3288 አና ተከታዮቹ ላይ የተደነገገውም ተቋራጩ የውል ግዴታውን ባልፈጸመ ጊዜ የግንባታ ባለቤት ለሆነው ለአስተዳደር መስሪያ ቤት የግንባታ ስራውን ከተቋራጩ ለመንጠቅ እና ውሉ ሳይቋረጥ ስራው በስራ መሪ ስር ሆኖ እንዲቆይ ለማድረግ መብት ይሰጠዋል፡፡እንዲሁም ውሉ ሊሰረዝ የሚችልበት ፈቃጅ የውል ቃል በግንባታ ውሉ ላይ ያለ እንደሆነ አሰሪው ቀሪውን ስራ ለሌላ ተቋራጭ በጨረታ ወይም በስምምነት በማሰራት እንዲጠናቀቅ ማድረግ ይችላል፡፡/የፍ/ህ/ቁ 3291(1) በዚህም ምክንያት አሰሪው ለተጨማሪ ወጭ/Additional cost/ የተዳረገ እንደሆነ ከተቋራጩ ላይ ለመጠየቅ እንደሚችል የፍ/ህ/ቁ 3291(2) በግልጽ መብት ይሰጠዋል፡፡ሆኖም በውል ህግ ላይ አሰሪው የተቋራጩን ግዴታ በሚያከብድ ሁኔታ ቀሪውን ስራ ማከናወን እንደሌለበት የሚያስገነዝበውን ግዴታውንም ማክበር አለበት፡፡
#በየትኛው የውል አይነት? ለሚለው በዋናነት የአስተዳደር መስሪያ ቤት የግንባታ ውሎችን በሚመለከት ሊተገበር የሚችል ነው፡፡ በግል የግንባታ ውሎች/private construction contract/ በተለይ ከፍ/ህ/ቁ 2610 እና ተከታዮቹ እንዲሁም ከፍ/ህ/ቁ 3019 እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች ውስጥ ተቋራጭን ስለማባበር አስመልክቶ ግልጽ ድንጋጌ አለመኖሩ ይህ መብት ለግለሰቦች ለመተግበር አስቸጋሪ የመሆኑን ሁኔታ ታሳቢ ተደርጐ በህግ አውጭው በማወቅ/ፐርፐዝሊ/ የተተወ ይመስላል፡፡ተዋዋዮች የግንባታ ውል ሲዋዋሉ ጀኔራል ኮንዲሽን ቢጠቀሙና በዚህም ስለተቋራጭ የማባረር መብት ድንጋጌ ቢኖረውስ የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል?ይሄን እንዴት ይተገብረዋል የሚለው ጉዳይ እንዳለ ሆኖ ውሉ ግን ለተዋዋዮች ህግ ስለሚሆን በተቻለ መጠን ሊተገበር ይገባዋል የሚል እሳቤ አለኝ፡፡
#በዚህ ጊዜ ማን ምን መስራት አለበት? ለሚለው በዋናነት በ MoWUD 1994 ክሎዝ 63(2) ላይ እንደተቀመጠው በግንባታ ሳይት ላይ የተገኘ ቁሳቁስ በሙሉ በዝርዝር መመዝገብና ዋጋ ወጥቶለት መጠኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡በተቋራጩ የተሰራው ስራ መጠን/level of work done/ በትክክል መታወቅና በዝርዝር መመዝገብ አለበት፡፡ተቋራጩ ያለበት እዳ/ከወሰደው የቅድሚያ ክፍያ ውስጥ ያልመለሰው ማለት ነው/ መታወቅ አለበት፡፡ለተቋራጩ የተከፈለው የስራ ክፍያ ሊታወቅ ይገባል፡፡እነዚህን የሂሳብ ሁኔታዎች አመዛዝኖ እና ዋጋ አስቀምጦ ተቋራጩ የሚከፈለው ገንዘብ ካለ እንዲከፈለው ለአሰሪው የሚመልሰው ገንዘብ ካለም እንዲመልስ ሂሳብ የማስተሳሰብና ሪፖርት የማቅረብ ሀላፊነቱ የአማካሪ መሀንዲሱ ነው፡፡በዚህ ረገድ አማካሪ መሀንዲሶች ብዙ ጊዜ እንደዚህ አይነት ሪፖርት ስለማያቀርቡ የግንባታ ክርክሮች ያልተሸከፉ ይሆኑና ለፍርድ ቤቶች ለትክክለኛ ፍትህ አሰጣጥ አስቸገሪ ሁኔታ ይፈጥራሉ፡፡
#አሰሪው ይህን መብቱን ለመጠቀም ሀይል መጠቀም የሚችልበት ግልጽ ፈቃጅ ህግ ግን የለም፡፡
#በመጨረሻም አሰሪና ተቋራጮች ለግንባታ ጥራት በመስራትና ለትክክለኛ እና እውነተኛ ነገር በመተባበር የኮንስትራክሽኑ ዘርፍ እድገት እንዲያሳይ ማገዝና አለመግባባቶችን በስምምነት መፍታት ቢችሉ ጠቀሜታው ለሀገርም ለራሳቸውም ነው፡፡በአሰሪና ተቋራጭ ክርክር ብዙ ትምህርት ቤት እና የጤና ተቋም እንዲሁም ሌሎች መሰረተ ልማቶች ግንባታቸው ተቋርጦ ማህበረሰቡን ከተጠቃሚነት የሚያዘገይበት ሁኔታ ወደፊት ተቀርፎና ተቃልሎ ማየት የዘወትር ምኞታችን ነው፡፡


By: Gubaie Assefa
https://t.me/ethioengineers1
4.5K viewsENG Sintayehu Melese, 09:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-08 12:08:13
#ጥቆማ

የአድቫንስድ ኳንቲቲ ሰርቬይንግ ስልጠና ለመውሰድ የሚፈልጉ ተጨማሪ ተማሪዎች ክላስ የሚጀመርበት ቀን በአንድ ሳምንት እንዲራዘም በጠየቁን መሰረት ሚያዝያ 30/2014 ለመጀመር አቅደን የነበረውን ክላስ ወደ ግንቦት 07/2014 ያዛወርን መሆኑን እየገለጽን ምዝገባው ከግንቦት 7 በኋላ የማይቀጥል መሆኑን እናስታውቃለን፡፡

0911439855 for details

ሚያዝያ 29/2014
3.5K viewsENG Sintayehu Melese, 09:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-07 19:36:10 #በመላው_ዓለም_የምትገኙ_ውድ_አድማጮቻችን...

በውሃልክ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን እየተዘጋጀ በኢትዮጵያውያን ቤተ-ሬዲዮ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የዓየር ሞገድ ላይ በዛሬው ዕለተ ቅዳሜ ሚያዝያ 29/14 ዓ.ም ከጠዋቱ 2 እስከ 3 ሰዓት በተደመጠው ውሃልክ የኮንስትራክሽን ፕሮግራማችሁ….

በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ላለፉት ሁለት ዓመታት የኮቪድ ወረርሽኝ እና የሎክዳውኑ ተፅእኖ እንዲሁም ከፀጥታ ጋር በተያያዙ ችግሮች መነሻነት በኮንስትራክሽን ኢንደስትሪው ላይ የተፈጠረው ተፅእኖ ቀላል እንዳልነበር ይታወቃል።

ይኸው ዓለም ዓቀፍ ችግር በአገራችን የኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ ላይ የሚኖረው ተፅእኖ እስከምን ድረስ ነው?፤ መሠል ሁኔታዎች ሲያጋጥሙስ በተቋራጮች በኩል የኮንትራት ውል የማቋረጥ፣ የማራዘም ብሎም የካሳ ጥያቄዎች ወዘተ ፍላጎት ቢኖር ሕግን የተከተሉ የማሻሺያ ርምጃዎች ሊኖሩ ይችሉ ይሆን? እየተባባልን ከእንግዳችን አቶ ጀማል አሊ ጋር እንደተለመደው በልክ እና በቁም-ነገር ተጨዋውተናል።

በመሆኑም በተለያዩ ግለ ምክንያቶቻችሁ የዛሬው ፕሮግራም ያመለጣችሁ አድማጮች የዝግጅቱን ፍሬ-ነገር ዳግም ታደምጡልን ዘንድ ስንጋበዛችሁ፤ አንደሁልጊዜው ሁሉ ደስ እያለን ነው።

#የውሃልክ_ሕንፀት በውሃልክ_መሠረት!
#ሕይወትን በኮንስትራክሽን እንገንባ!
#ውሃልክ_ሚዲያ_እና_ኮሚዩኒኬሽን።
4.4K viewsምታቸው@ጌታቸው @የዓይንዋጋ ቸኮል ልጅ, 16:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-01 20:18:26
● New Class Schedule Starting May 07 / 2022
● ሚያዝያ 29 / 2014 የሚጀምር አዲስ ኘሮግራም


0911890392 / 0944186744

https://t.me/BeGetEngineering
7.0K viewsBelay #1, 17:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-01 13:58:53
𝙵𝚘𝚞𝚗𝚍𝚊𝚝𝚒𝚘𝚗 𝚋𝚘𝚕𝚝 -

𝙵𝚘𝚞𝚗𝚍𝚊𝚝𝚒𝚘𝚗 𝚋𝚘𝚕𝚝𝚜 𝚊𝚛𝚎 𝚊𝚗𝚌𝚑𝚘𝚛 𝚋𝚘𝚕𝚝𝚜 𝚞𝚜𝚎𝚍 𝚝𝚘 𝚌𝚘𝚗𝚗𝚎𝚌𝚝 𝚜𝚝𝚛𝚞𝚌𝚝𝚞𝚛𝚊𝚕 𝚊𝚗𝚍 𝚗𝚘𝚗-𝚜𝚝𝚛𝚞𝚌𝚝𝚞𝚛𝚊𝚕 𝚎𝚕𝚎𝚖𝚎𝚗𝚝𝚜 𝚝𝚘 𝚌𝚘𝚗𝚌𝚛𝚎𝚝𝚎.

https://t.me/ethioengineers1
6.9K viewsENG Sintayehu Melese, 10:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 21:05:04 ተቋራጮችን ከመንግስት ግዢ አቅራቢዎች ዝርዝር ማገድ

[Suspension from Suppliers List]

በመንግስት ግዢ ወቅት በሚፈፀሙ የስነ-ስርዓት ግድፈቶች ምክንያት ጥቅሜ ተነክቶብኛል የሚል አቅራቢ ወይም ተጫራች ለግዢ ፈፃሚው የመንግስት አካል ወይም ለአቤቱታ አጣሪው ቦርድ አቤቱታ የማቅረብ መብት እንዳለው የአዋጁ አንቀፅ 70(1) እንዲሁም የመመሪያው አንቀፅ 43 ይገልፃሉ፡፡ ነገር ግን አቤቱታ የማይቀርብባቸው ጉዳዮችም እንዳሉ አንቀፅ 70(2) እና 44 በዝርዝር ያስቀምጣሉ፡፡

ነገር ግን የዚህ ፅሁፍ አላማ በግዢ ፈፃሚ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ለኤጀንሲው በሚያቀርቡት አቤቱታ ላይ ተመሰረቶ ኤጀንሲው ተቋራጮችን ከተጫራቾች ወይም ከአቅራቢዎች ዝርዝር ሊያግድ ስለሚችልበት ሁኔታዎች ለመወያየት ስለሆነ ተጫራቾች ስለሚያቀርቡት አቤቱታ እና ስለአፈታት ስርዓቱ በሌላ ፅሁፍ እመለስበታለው፡፡

የግዢ ፈፃሚ የመንግስት መስሪያ ቤት በተጫራቾች ወይም በአቅራቢዎች ሕገ-ወጥ ተግባር ወይም ሕጋዊ ጥቅሜን የሚነካ ተግባር ተፈፅሞብኛል ብሎ ሲያምን በአዋጁ አነቀፅ 12 መሰረት ለተቋቋመው የመንግስት ግዢና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ አቤቱታውን ማቅረብ እንደሚችል አንቀፅ 76(1) እንዲሁም የመመሪያው አንቀፅ 48(1) ይደነግጋሉ::

አንቀፅ 15(7) በዕጩ ተወዳዳሪዎችና በአውራቢዎች ላይ የመ/ቤቶች የሚያቀርቡትን አቤቱታዎች መርምሮ ውሳኔ መስጠት የኤጀንሲው አንዱ ተግባር መሆኑን ይገልፃል፡፡

በዚህም መሰረት ኢጀንሲው አቤቱታ ሲቀርብለት አቤቱታ ለቀረበበት ወይም ለተከሳሽ ዕጩ ተወዳዳሪ ወይም አቅራቢ አቤቱታ መቅረቡንና የአቤቱታዉን ይዘት የሚገልፅ ማስጠንቀቂያ በመላክ ያሳውቃል፡፡ ይህም የተከሳሽ በአስተዳደር ዉሳኔ አሰጣጥ ላይ የመሰማት መብቱን እነዲጠበቅ ይረዳል፡፡ ይህ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ የደረሰው ‹ተከሳሽም› በ5 የስራቀናት ውስጥ የፅሁፍ መልሱንና የሰነድ ማስረጃዎችን ለኤጀንሲው ማስገባት እንዳለበት ከመመሪያው አንቀፅ 48.3 ንባብ መረዳት ይቻላል፡፡

ኤጀንሲውም አቤቱታውን በተቀበለ በ15 የስራ ቀናት ውስጥ መርምሮ ውሳኔ በመስጠት ለተከራካሪዎቹ በፅሁፍ ማሳወቅ እንዳለበት የአዋጁ አንቀፅ 76(4) ከመመሪያው አንቀፅ 48.4 ጋር ይገልፃሉ፡፡ ለአቤቱታውም ሊሰጡ የሚችሉት ዉሳኔዎች አቤቱታውን ውድቅ ማድረግ፤ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ መስጠት፤ ወይም ዕጩ ተወዳዳሪውን ወይም አቅራቢውን በመንግስት ግዢ ላይ እንዳይሳተፍ ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ከተወዳዳሪነት ወይም ከአቅራቢነት ማገድ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

ስለዚህ ተቋራጮች በቀረበባቸው አቤቱተታ ጥፋተኛ ሆነው ከተገኙ ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ በማንኛውም የመንግስት ጨረታ ላይ እንዳይወዳደሩ ሊታገዱ ይችላሉ ማለት ነው፡፡

ተጫራቾች ከማንኛውም የጨረታ ውድድር ሲታገዱ በተለምዶ በጥቁር መዝገብ ወይም “Black List” ውስጥ ገቡ ይባላል፡፡ ዋናው ነገር ደግሞ ምን ምን ዓይነት ጥፋቶች ናቸው ተጫራቾችን በጥቁር መዝገብ እንዲገቡ የሚያደርጓቸው? የሚለው ነው፡፡

እነዚህም ነጥቦች በመመሪያው አንቀፅ 48.5.1 እና 48.5.2 ላይ በዝርዝር ተቀምተጠዋል፡፡ በአንቀፅ 48.5.1 እንደተዘረዘሩትም የጨረታ ግምገማውን ውጤት ለማበላሸት ወይም ለመለወጥ አስበው ለግዢ ሰራተኞች ሙስና መስጠት፤ የውሸት ወይም ተቀባይነት የሌላቸውን መረጃዎች በማቅረብ ማጭበርበር፤ የኤጀንሲው እግድ እያለባቸው በግዢ ላይ መሳተፍ/መወዳደር እንዲሁም ተጫራቾች ወይም አቀራቢዎች በዉሉ ከተገለፀው ጥራት የወረደ ዕቃ፤ ስራ፤ ወይም አገልግሎት በማጭበርበር ወይም ከገዢ ሰራተኞች/ባለስልጣናት ጋር በመመሳጠር ያቀረቡ እንደሆነ ኤጀነሲው ከሁለት ዓመት ጀምሮ እስካልተወሰነ ጊዜ ድረስ በማንኛውም የመንግስት ግዢ ላይ እንዳይሳተፉ ሊያግዳቸው ይችላል::

ከእነዚህም ምክንያቶች በተጨማሪ ተጫራቾች ፍትሃዊ የዋጋ ወድድር ጥቅምን ለማሳጣት ከተወሰኑ ተጫራቾች ጋር በመመሳጠር የዋጋ ተመን ካወጡ/ከጣሉ፤ የግዢ ባለሙያዎች ወይም የግዢ ፈፃሚ መንግስት መ/ቤት ሰራተኞች ላይ የአካል ጉዳት ለማድረስ የዛተ/ያስፈራራ ወይም ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ወይም በኤጀነሲው የተጣለበት እግድ ከተነሳበት ቀን ጀምሮ በሁለት ዓመታት ዉስጥ ሌላ ማንኛውም ከአቅራቢዎች ዝርዝር ሊያሳግድ የሚችል ጥፋት የፈፀመ እንደሆነ በተመሳሳይ ከሁለት ዓመት ጀምሮ እስካልተወሰነ ጊዜ ድረስ ሊታገድ ይችላል ማለት ነው፡፡

በአጭሩ ሙስና፣ ማጭበርበር፣ መመሳጠር፣ ወይም ዕግድን ጥሶ በጨረታ ላይ መወዳደር ተጫራቾችን/አቅራቢዎችን ከአቅራቢነት ዝርዝር ሊያሳግዳቸው ይችላል ማለት ነው፡፡

በሌላ በኩለ ደግሞ አንቀፅ 48.5.2 ላይ እንደተገለፁት ከመንግስት ጋር የግዢ ውል የተዋዋለው አቅራቢ በዉሉ የተገለፁትን ዕቃዎች፡ ስራዎች ወይም አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ባለማቅረቡ ምክንያት የግዢ ፈፃሚው መ/ቤት ቀጥተኛ ወይም ተዘዋዋሪ ጉዳት [Direct or Consequential Loss] ያጋጠመው እንደሆነ ወይም የመ/ቤቱን ስራ ያጓተተ ወይም ያፋለሰ እንደሆነ አቅራቢው ከአቀራቢዎች መዝገብ ላይ ከስድስት ወር እስከ ሁለት ዓመት ድረስ ሊታገድ ይችላል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ የጨረታ ውድድር እንዳሸነፈ በመ/ቤቱ የተገለፀለት አቅራቢ ውሉን ለመዋዋል ባለመቻሉ ወይም እምቢተኛ በመሆኑ ምክንያት መ/ቤቱ በዉሉ የተገለፀውን ዕቃ፣ ስራ ወይም አገልግሎት ከሌላ አቅራቢዎች ለመግዛት ሲል ጉዳት ያጋጠመዉ ወይም ስራዉን ያጓተተ ወይም ያፋለሰ እንደሆነ እነዲሁም የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው አቀራቢ በሶስት ዓመት ውስጥ ሌላ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ሊያስጥ የሚችል ጥፋት ፈፅሞ ከተገኘ ኤጀንሲው አቅራቢውን ከአቀራቢዎች መዝገብ ላይ ከስድስት ወር እስከ ሁለት ዓመት ድረስ ሊያግደው ይችላል፡፡

ከአቀራቢዎች ዝርዝር መዝገብ ላይ ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ መታገድ ውጤቱም በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ተጫራቹ ወይም አቅራቢው በማንኛውም የመንግስት ግዢ ላይ መወዳደር አይችልም፡፡ እነዚህ በኤጀንሲው የሚጣሉት የዕግድም ይሁን የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ቅጣቶች ግዢ ፈፃሚውን የመንግስት መ/ቤት በአቅራቢው ወይም በተጫራቹ ምክንያት የደረሰበትን የገንዘብ ኪሳራ ከመጠየቅ አያግደውም፡፡Written By: Girum Getu----Assistant Lecturer @ Wolkite University; School of Law
LL.M Candidate in Construction Law and Dispute Resolution @ Bahir Dar University School of Law

https://t.me/ethioengineers1
6.7K viewsENG Sintayehu Melese, 18:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-26 20:28:36 1. How is a reinforcement bar in hardened concrete structure exposed to corrosion??
ሙሉ በሙሉ ጥንካሬውን ያገኘ የ ኮንክሪት ስትራክቸር ውስጥ ያለ ወይም የተሰራበት reinforcement bar እንዴት ሊዝግ ይችላል? በምን ምክንያቶችስ ሊሆን ይችላል?

3 መሰረታዊ የሆኑ ሁኔታዎች reinforcement ባራችንን በበቂ ሁኔታ ጥንካሬውን ባገኝ የ አርማታ ስትራክቸር ውስጥ ባለበት ሊያዝጉት ይችላሉ (corrosion እንዲፈጠር ሊያደርጉት ይችላሉ)

1,የመጀመሪያው carbonation ይባላል

:- እንደሚታወቀው concrete strongly alkaline nature አለው። ይህም የሆነበት ምክንያት Ca(OH)2 ስላለው። pH value ደግሞ about 13 ነው።
:- due to this high alkalinity nature ኮንክሪቱ reinforcement ባሩን ከ corrosion ለመከላከል a thin passivating layer በባሩ ዙሪያ በመፍጠር ብረቱን ከዝገት ይከላከላል። ይህም process passivation በመባል ይታወቃል።
:- as we know CO2 በራሱ reactive አይደለም። ግን in the pressence of moisture( እርጥበት) ወደ dilute carbonic acid ይቀየራል። ከዛም concrete form ያደረገውን passivating layer መብላት ወይም ማፈራረስ ይጀምራል። በመጨረሻም PH value ን ወደ 8.3 - 9 ያደርሰዋል። ልክ PH value ከ 11 ማነስ ሲጀምር ብረቱ በቀላሉ መዛግ ይጀምራል።

2,ሁለተኛው ደግሞ chloride attack ነው

:- በተመሳሳይ መንገድ ልክ carbonation passivating layer ን ማፈራረስ እንደሚችል chloride attack ም ያንን በበለጠ ማድረግ ይችላል።
:- chloride attack is more serious reason than any other
:- in the presence of water and oxygen, chloride can destroy the passivating layer and leads to corrosion.
:- chloride በቀላሉ ወደ ኮንክሪቱ ሊገባ ይችላል። ለምሳሌ በ cement,water,aggregate and sometimes from admixtures or from environment by diffusion.

3,ሶስተኛው በ electrochemical process ነው

:- ይሄኛው ደግሞ when there is a difference in electrical potential along the steel reinforcement in concrete.
:- ብረቱ ውስጥ አንደኛው part anode ሌላኛው part ደግሞ cathode ሲሆን ነው።

★ በስተመጨረሻም corrosion of reinforcement ለመከላከል ምን አይነት measurement መውሰድ እንዳለብን እንድትወያዩበት እጋብዛለው።

https://t.me/ethioengineers1
7.9K viewsENG Sintayehu Melese, 17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-26 20:28:35
#ይመዝገቡ #ይሰልጥኑ

የሲቪል ኢንጂነሪንግ፣አርክቴክቸር፣ ኮተምና ኢንቲሪየር ዲዛይን ሶፍትዌርዎችን የትም ሆነው መማር ይችላሉ ከ ሰርተፊኬት ጋር፡
Megenagna
Marathon Building , 6th Floor, Office No 614


@BelayChane

Join @BeGetEngineering
6.4K viewsENG Sintayehu Melese, 17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-19 09:55:25
DPC or damp proof course is very important in structures to stop the moisture from entering the walls. DPC is usually provided at plinth level.

An effective damp proofing material should have the following properties;

1-It should be impervious.
2-It should be strong and durable and should be capable of withstanding both dead as well as live loads without damage.
3-It should be dimensionally stable.
4-It should be free from deliquescent salts like sulfates, chlorides, and nitrates.

The materials commonly used to check dampness can be divided into the following three categories:

Flexible Materials: Materials like bitumen felts (which may be hessian based or fiber/glass fiber-based), plastic sheeting (polythene sheets), etc.

Semi-rigid Materials: Materials like mastic, asphalt, or a combination of materials or layers.

Rigid Materials: Materials like first-class bricks, stones, slate, cement concrete, etc.
The practical visualization can be viewed in the attached picture.

https://t.me/ethioengineers1
10.1K viewsENG Sintayehu Melese, 06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ