Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ eotcy — ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
የቴሌግራም ቻናል አርማ eotcy — ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
የሰርጥ አድራሻ: @eotcy
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.36K
የሰርጥ መግለጫ

መንፈሳዊ ቻናል እንጋብዛቹ
@EOTCY
ምን አይነት ነገሮችን ነው የሚፈልጉት?
➢ የተለያዩ ትምህርቶችን
➢ መጣጥፎችን
➢ መንፈሳዊ ግጥሞችን
➢ ተከታታይ ትምህርቶችን
➢ ብሒለ አበው
➢ ወይስ ዜና ቤተክርስቲያን
አሁኑኑ ይቀላቀሉን የኦርቶዶክስ ተዋህዶን ቀጥተኛ አስተምህሮ ያገኙበታል👇👇👇
@EOTCY

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 12:49:30
ኦርቶዶክስ ከግሪክኛ ቃላት «ኦርቶ» (የቀና፣ ርቱዕ፣ ትክክለኛ) እና «ዶክስ» (ትምህርት) የመጣ ቃል ነው።

በተለያዩ እምነቶች ወይም ርዕዮተ ዓለሞች ውስጥ «ኦርቶዶክስ» የተባሉት ወገኖች ሊኖሩ ይችላሉ። በዋናኛነት ኦርቶዶክስ የሚባሉት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖትን ስርአት የሚከተሉት ናቸዉ ማለትም፦

አምስቱ ኦርዬንታል አብያተ ክርስቲያናት

-የኢትዮጵያ/የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን

-የግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን

-የአርመን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን

-የሶርያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን

-የህንድ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን

ምሥራቅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን -
- ግሪክ ኦርቶዶክስ
- ሩስያ ኦርቶዶክስ
_የዩክሬን ኦርቶዶክስ ወ.ዘ.ተ....
@eotcy
238 viewsBᵉⁿᵒⁿ, edited  09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 20:13:53 . መ-ቁ-ጠ-ሪ-ያ
+========+========+========+
መቁጠሪያ በመሠረቱ ቃሉ መ-ቁ-ጠ-ሪ-ያ ነዉ ራሱ ቃሉ።
አባቶቻችን እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስን 41 ጊዜ፣
በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስን 41 ጊዜ፣
ኪርያላይሶን ክርስቶስ 41 ጊዜ፣
አምላኬ አምላኬ 41 ጊዜ
ስምዓነ አምላክ 41 ጊዜ፣
አድኅነነ ከመዓቱ ይሰዉረነ በምሕረቱ በእንተ ማርያም ወላዲቱ 41 ጊዜ ይቆጥሩበታል።

በሁለተኛ መቁጠሪያ መግረፊያም ጭምር ነዉ።
በጥንታዊቷ ቤተክርስቲያናችን ከሚገኙና ሰይጣን ዲያብሎስን ከምንዋጋበት መሳሪያዎቻችን መካከል አንዱ መቁጠሪያ ነዉ።

በአንተ ጠላቶቻችን እንዋጋቸዋለን በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን።
መዝ.፵፫ (፵፬)፥፭
መቁጠሪያ ለሰዉ ልጅ በጣም በጸሎት ጊዜያት ከሚያስፈልጉት ዉስጥ አንዱ ነዉ።

ምክንያቱም ከዛሬ መቶ ሃያ አመት በፊት የነበሩ አባቶች በመቁጠሪያ ጸሎት በመጸለይ ኃይለ አጋንንትን በመቀጥቀጥ ድል ያደርጉ፤ ሥጋቸዉንም ለነፍሳቸዉ ያስገዙ ነበር።

መናፍስት በሕይወታቸዉ ዉስጥ እንዳይገባ ትከሻቸዉን፣ ጀርባቸዉን፣ ማጅራታቸዉን፣ ራሳቸዉን፣ እግራቸዉን፣ ባታቸዉን፣ ሆዳቸዉን፣ ክንዳቸዉን፣ በመቁጠሪያዉ ይመቱታል። ራሳቸዉን የሚመቱት ጥልቅ የሆነ መንፈሳዊ ሕይወት ግንዛቤ ስላላቸዉ ነዉ።

የሚመቱት ክፉ መናፍስት ጸሎቶቻቸዉን እንዳያስታጉል ድካም እንዳያመጣባቸዉ እግራቸዉን እንዳይዝ ቁርጥማት እንዳይሆን የብርድ በሽታ እንዳይሆን ነርቭ እንዳይሆን ግንዛቤ ስላላቸዉ ነዉ።
አሁን ግን ይሄ መንፈሳዊ ዉጊያ ተረስቶ መቁጠሪያ ለቆራቢ ነዉ።

መቁጠሪያ ለምንኩስና የበቁ ሰዎች ነዉ እየተባለ ይገኛል። ይህ ፍጹም ስህተት ነዉ።
በመጽሐፍ ቅዱስ 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ፱፥፳፯ ላይ ያለዉን ቃል እንመልከት።

ነገር ግን ለሌሎች ከሰበክሁ በኋላ ራሴ የተጣልሁ እንዳልሆን ሥጋዬን እየጎሰምሁ አስገዛለሁ።
@eotcy
እየጎሰምሁ ሲል እየተንቀጠቀጥኩ ማለቱ ግልጽ ነዉ። ስለዚህም መቁጠሪያን በመጠቀም ከዉስጥ ያደፈጠ ጠላት መያዝና ማቃጠል ከሰዉነታችንም እንዳይገባባ ማስጨነቅ እና ማባረር እንችላለን።
@eotcy
243 viewsᵇᵉⁿᵒⁿ 🅸🅽 , edited  17:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 07:45:59 ማህበረ ቅዱን ምን እየሰራ ነው

#ከ80 ሺ በላይ አዲስ አማኒያን !

ደስ የሚል ነገር ስለሆነ ላካፍላቹ

"ማህበረ ቅዱሳን በትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎቱ ከ80ሺ በላይ ኢ አማንያንን አስተምሮ በማጥመቅ የሥላሴ ልጅነትን እንዲያገኙ ማድረጉን አስታወቀ፡፡

በትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ለ4,556 ካህናት፣ 2,494 ሰባክያነ ወንጌል እና በሐዋርያዊ ተልዕኮ ጉልህ ድርሻ ላላቸው 379 የጎሳ መሪዎች በተለያዩ ርዕሶች ከአንድ ሳምንት እስከ አንድ ወር ድረስ ቆይታ ያላቸው ስልጠናዎች ተሰጥቷል፡፡ ለዚህም ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል፡፡

የሐዋርያዊ ተልእኮን ተደራሽ በማድረግ በጋሞ ጎፋ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ከፋ፣ ቤች ሸኮ፣ ሸካና ምእራብ፣ ወላይታ፣ ጌደዎና በሌሎች አኅጉረ ስብከቶች 80,317 አዳዲስ አማንያን ሥርዓተ ጥምቀት እንዲፈጸምላቸው ተረድጓል፡፡ ለሐዋርያዊ አገልግሎቱም 8,126,008.00 ብር ወጪ ተደርጓል ፡፡
@eotcy
ሐዋርያዊ ተልእኮ በስፋት በሚፈጸምባቸው አካባቢዎች ለአዳዲስ አማንያን አገልግሎት መስጠት የሚችሉ 19 አብያተ ክርስቲያናት ተገንብተው አገልግሎት እንዲጀምሩ ተደርጓል ፡፡

አራት አብያተ ክርስቲያናት ግንባታቸው ተጠናቆ በቅርብ የሚመረቁ እና አገልግሎት የሚጀምሩ ይሆናል፡፡
@eotcy
ሐዋርያዊ ተልእኮ በሚፈጸምባቸው አካባቢዎች በካህናት እጥረት ተዘግተው የነበሩ 55 አብያተ ክርስቲያናት በመቅጠር እንዲከፈቱና ለምእመናን አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል ፡፡

ከአዳዲስ አማንያን ጥምቀትና ድኅረ ጥምቀት አገልግሎት መስጠት የሚችሉ 9 የስብከት ኬላ አዳራሾች 1,200, 000 ብር ወጪ ተደርጓል ፡፡
2 የሲዳምኛ አልበም ፣ 2 የክስታንኛ መዝሙራት እና 2 እንግሊዝኛ የዝማሬ አልበም ተዘጋጅተዋል ፡፡

እንዲሁም የነገረ ሃይማኖት ትምህርት በከንባትኛ፣ በቤችኛ ፣ በጋምኛ ፣ በኮንሶኛና በማሌኛ ቋንቋዎች መዘጋጀታቸውን በሪፖርቱ አስታውቋል፡፡"

@eotcy
267 viewsᵇᵉⁿᵒⁿ 🅸🅽 , 04:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:31:48 #የምንለወጠው_ምን_ስናደርግ_ነው?

በታመምህ ጊዜ ድካም ይሰማሃል፤ ብርታት ያንስሃል፤ ፊትህም ይገረጣል፡፡ የዕለት ተዕለት ሥራዎችህን በአግባቡ ማከናወን ይሳንሃል፡፡ በዚህ ጊዜም ሕመምህ ምን ያህል እንደ በረታ ሰዎች ያስተውላሉ፤ መታከም እንደሚገባህም ይነግሩሃል፡፡ ስለዚህ ወደ ሐኪም ትኼዳለህ፡፡ ወደ ሐኪም የምትኼደው ግን ሐኪሙ ምን እንዲያደርግልህ ነው? አሁን ለሚሰሙህ ስሜቶች የሚሽሩ መድኃኒቶችን እንዲሰጥህ ነው፡፡ ኾኖም ይሰ'ሙህ የነበሩ ስሜቶች ቢሻሉህም ሰውነትህ አሁንም እንደ ደከመ፣ ፊትህ እንደ ገረጣ ከቀረ፣ የዕለት ተዕለት ሥራዎችህንም በአግባቡ ማከናወን ከተሳነህ በተሰጠህ ሕክምና ደስተኛ ትኾናለህን? አትኾንም !

“እውነታው ምንድን ነው?” ስንል ወደ ሐኪሙ የኼድከው የበሽታህን ምንጭ ለመታከም ሳይኾን የበሽታህን ምልክቶች ለማስታገሥ ስለኾነ ነው፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ የበሽታህ መንሥኤ እስካልታከመ ድረስ የበሽታህ ምልክቶች ለጊዜው ቢታገሡም ቅሉ ፈጽመው ሊወገዱ እንደ ማይችሉ ሐኪሙ በደንብ ያውቃል፡፡

በክርስቶስ ክርስቲያን፣ በወልድ ውሉድ፣ በመንፈስ ቅዱስም መንፈሳውያን የተባልን እኛም እግዚአብሔር መንፈሳዊ በሽታችንን እንዲያስወግድልን እንሻለን፡፡ እንደ እውነታው ግን ብዙዎቻችን ወደ እግዚአብሔር ቀርበን እንዲያስወግድልን የምንሻው ምልክቶቹን ነው፡፡ ለምሳሌ ችግርን፣ ኀዘንን፣ ቀቢጸ ተስፋንና የመሳሰሉትን እንዲያርቅልን እንፈልጋለን፡፡

እግዚአብሔር ደግሞ ከዚህ በተቃራኒ የእነዚህ ምክንያት የኾነውንና ሥር የሰደደውን፣ ዋና ምክንያትም የኾነውን መንፈሳዊ በሽታችንን ሳይሽር እነዚህን ምልክቶች ሊያርቅልን አይፈልግም፡፡ ችግር የሚኾነውም ይህን ጊዜ ነው፡፡ ምልክቶቹን እንዲያርቅልን ስንደክም ወደ ውሳጤያችን ገብቶ የችግሩን ምንጭ ሊያርቅልን የሚችለውን የእግዚአብሔርን ጸጋ (ኃይልን) አጥብቀን እንቃወማለንና፡፡ በውሳጤያችን የተሸሸገውን በሽታ ማስወገድ አንፈልግም፡፡ አመለካከታችን እንዲለወጥ አንፈቅድም፡፡ እውነተኛ ለውጥ የሚመጣውና አማን በአማን የምንታከመው ግን የልባችንን ውሳጤ ለእግዚአብሔር ስንከፍትለትና እርሱም በዚያ በመረቀዘው ቁስላችን ላይ ጽኑ መድኃኒት ሲያስርልን ነው፡፡ እንዲለወጡ የምንፈልጋቸው ምልክቶች በእርግጥም የሚለወጡት ይህ በልባችን ውስጥ የተደበቀው መንፈሳዊ በሽታችን ሲጠፋ ነው፡፡

➛ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
➛ አምስቱ የንስሐ መንገዶች - ገጽ 69-70
➛ ትርጉም በገብረ እግዚአብሔር ኪደ

@eotcy
127 viewsᵇᵉⁿᵒⁿ 🅸🅽 , 18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 11:34:44
ከመላእክት ማኅበር የገባ ዜግነት ኢትዮጵያዊነት ብቻ ነው። በምድር በቅሎ ከሰማያዊያኑ ሱራፌል ገብቶ የተቆጠረ ድንቅ ተክል አለን። አባ ተክለ ሃይማኖት የሚባል።

ለሚያምን ሁሉ ይቻላል ብሎ የለ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ።

እንኳን ለጻድቁ በዓለ ዕረፍት አደረሳችሁ!!!
@eotcy
361 viewsᵇᵉⁿᵒⁿ 🅸🅽 , 08:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 21:20:14
የማህተብ ትርጉም
1. ቀይ ክር ======የጌታችን ደም ምሳሌ ለማስታወስ እናስራለን
2. ጥቁር ክር======የሀዘናችን ምሳሌ ለማስታወስ እናስራለን
3. ነጭ ክር=======የሰላምና የፍቅሩን የትንሣኤ ሙታን የመላእክት ምሳሌ ለማስታወስ እናስራለን
4. የእንጨት መስቀል====ስለ እኛ ኃጢያትና እርግማን በመስቀል ላይ ጌታችን መሰቀሉን ነው
5. የነሀስ መስቀል=====ስለ እኛ ምራቅ መተፍቱ መረገጡ መገረፉ ስለ እኛ ጌታችን መቁሰሉ ነው
6. የብር መስቀል======= ስለ እኛ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በ30 ብር መሸጡ ነው
7. የወርቅ መስቀል====== የጌታ ክብሩን ንውስነቱን የሁሉ ገዥ አምላክ መሆኑን
በክርስቶስ ክርስቲያን በወልድ በመንፈስ ቅዱስ መንፈሳውያን ለመሆናችን ለመመስከር እናስራለን
ማህተቤን አልበጥስም
@eotcy
@eotcy
@eotcy
459 viewsᵇᵉⁿᵒⁿ 🅸🅽 , 18:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 21:15:22 + ብናምንስ + ፃድቁ ኢዮብን በመሰልነው +
@eotcy

ሰባት ወንዶች እንዲሁም ሦስት ሴቶች ልጆቹን በቅጽበት ሲያጣ ፈጣሪውን ያላማረረ ጻድቁ ኢዮብን እስኪ ለአፍታ እናስበው፡፡ ልጆቻቸውን ያጡ ወይም የሚያጡ ብዙ ወላጆች ልጆቹ ከመሞታቸው በፊት የመጨረሻ ቃላቸውን የመስማት፣ እጆቻቸውን የማሻሸትና ጥልቅ በሆነ ቤተሰባዊ ፍቅር የመሳም፣ ከሞቱም በኋላ እንደ ሥርዓቱ ዓይኖቻቸውን የመክደን እና አስከሬናቸውን አጥቦ የመገነዝ እድል አላቸው። ጻድቁ ኢዮብ ግን ከእነዚህ ውስጥ አንዱን እንኳን አላገኘም። ልጆቹ በታላቅ ወንድማቸው ቤት ሲበሉና ሲጠጡ ድንገት ዐውሎ ነፋስ ተነሥቶ ቤቱን ደርምሶ ስለ ገደላቸው እነርሱን ተንከባክቦ የማስታመም እድል አላገኘም። ነፍሳቸውም በወጣችበት ደቂቃ ዓይኖቻቸውን አልከደነም፡፡
@eotcy
የሞቱት ድንጋይ ተጭኗቸው ስለሆነና አስከሬናቸውን ለማውጣት በሚደረገው ቁፋሮ ወቅት አንዳንዶቹ ሕዋሳቶቻቸው በጣም ስለሚጎዱ ሙሉ አካላቸውን የመቅበሩ ነገር ያጠራጥራል፡፡ ታዲያ እነዚህ ሁሉ መከራዎች በአንድ ጊዜ ቢደራረቡበትም ጻድቁ ኢዮብ ግን ‹‹እግዚአብሔርን አልሰደበም፣ መላእክትን አልረገመም››። ይልቅ ወደ ምድር #ሰግዶ ‹‹እግዚአብሔር ሰጠ፣ እግዚአብሔርም ነሣ፤ የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን›› ብሎ አምላኩን አመሰገነ።

ትንሣኤ ባልተሰበከበት፣ የሰው ተስፋ በቀጨጨበት፣ ሞት ጥላውን ባጠላበት በኦሪት ዘመን የነበረ ኢዮብ እነዚያን ሁሉ ልጆች በአንድ ጊዜ አጥቶ እንዲህ ካመሰገነ፣ ስለ ትንሣኤው የተማርንና "የሙታንን መነሣት ተስፉ እናደርጋለን" ብለን የምንጸልይ፣ የኢዮብን ሩብ ያህል እንኳን መከራ ያልደረሰብን እኛ የሐዲስ ኪዳን ምእመናን ምን ያህል አመስጋኞች ልንሆን በተገባን?

@eotcy
501 viewsᵇᵉⁿᵒⁿ 🅸🅽 , 18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 07:31:01 ልብ ብለው ያንቡት በኛ ምክንያት ብዙዎቸ በተለያየ ምክንያት ተሰናክለዋል

+ የአንድ ሰው ውሎና አመሻሽ +

ይህ እስካሁን ምንጩን ያላገኘሁት አንድ ወንድሜ የላከልኝ በፈረንጅ አፍ የተጻፈ የቆየ የአንድ ሰው ገጠመኝ ነው :-

አንድ ወንድም ስልኩን ድምፅ አልባ ማድረግ ረስቶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ስብከት ይማራል:: በዚህ መካከል ስልኩ ይጮኃል::

ሰባኪው ስብከቱን አቁሞ በዓይኖቹ ተቆጣው:: ከስብከቱ በኋላ ምእመናን ስብከቱን በመረበሹ ወቀሱት:: አንዳንዶቹም እያዩት ራሳቸውን በትዝብት ነቀነቁ:: ከሚስቱ ጋር ወደ ቤታቸው ሲሔዱም ሚስቱ ስለ ቸልተኝነቱ ምክር መሥጠትዋን ቀጠለች::
እፍረት መሸማቀቅና ውርደት ዘልቆ እንደተሰማው በፊቱ ላይ ይታይ ነበር:: ከዚያች ሰንበት በኋላ እግሩን ወደ ቤተ ክርስቲያን አንሥቶ አያውቅም::

ውስጡ የተረበሸው ይህ ሰው ያንኑ ምሽት ወደ መጠጥ ቤት አመራ:: አእምሮው እንደታወከ ነበር::

ቁጭ ባለበት ድንገት የሚጠጣበት ጠርሙስ ወድቆ ተሰበረና መጠጡም በዙሪያ ተረጨ:: ፍንጣሪው የነካቸው ሰዎች ወደ እሱ መጠጋት ጀመሩ:: ሊጮኹበትና በጥፊ ሊሉት እንደሆነ ታውቆት ቀድሞ ዓይኖቹን ጨፈነ::

ሰዎቹ ግን በተሰበረው ጠርሙስ ስብርባሪ ተጎድቶ እንደሆነ ተጨንቀው ጠየቁት::

አስተናጋጁ መጥቶ የፈሰሰበትን እንዲያደርቅ ማበሻ ሰጠው:: የጽዳት ሠራተኛዋ መሬቱን ወለወለች::

የቤቱ ባለቤት "አይዞህ ያጋጥማል? ዕቃ የማይሰብር ማን አለና?" አለችውና ሌላ መጠጥ አስመጣችለት::
ከዚያች ቀን ጀምሮ ከዚያ መጠጥ ቤት ቀርቶ አያውቅም::

በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስልክን ክፍት ማድረግና ሥርዓተ አምልኮ መረበሽ መቅደስ ውስጥ ጫማ አድርጎ የመግባት ያህል ስኅተት ነው:: እንኩዋን ቤተ ክርስቲያን ኤምባሲ እንኩዋን ስልክህን ውጪ አስቀምጠህ ትገባለህ:: ሰውዬው ላጠፋው ጥፋት ግን በፍቅር የሚያናግረው ሰው በማጣቱ ከነ ስልኩ ሊጠፋ ወሰነ::

ቤተ ክርስቲያን የድኅነት ሥፍራ ናት:: መጠጥ ቤት ደግሞ የጥፋት ጎዳና ነው:: በዚህ ሰው ታሪክ ውስጥ ግን በድኅነት ሥፍራ ካሉ ሰዎች ይልቅ በጥፋት ሥፍራ ያሉ ሰዎች ለሰውዬው ስኅተት የተሻለ ፍቅር አሳዩ:: አንዳንዴ የአንዳንድ ምእመናን ጠባይ ነፍሳትን ወደ ሲኦል ይሰድዳል::

አንዳችን የአንዳችን ጠባቂ መሆን እንችላለን ዓለምን ለመፈወስ የሚቻለንን እናድርግ:: ነፍሳትን ከማዳን ነፍሳትን ማጥፋት በጣም ቀላል ነው::

መድኃኔዓለም ክርስቶስ የኃጢአተኞች ወዳጅ ነበረ:: እሱ የማንንም ቅስም በክፉ ቃል አልሰበረም:: እኛ ግን ሰው ላይ ስንጨክን መጠን የለንም:: በዚህ ምክንያት እንደ ኒቼ ያሉ ሰዎች "ብቸኛው ክርስቲያን መስቀል ላይ የሞተው ነው" ብለው እስኪዘብቱብን ደርሰዋል::

መጽሐፍ ግን ሰው ሲሳሳት ስናይ ምን ማድረግ እንዳለብን እንዲህ ሲል ይናገራል :-

"ወንድሞች ሆይ፥ ሰው በማናቸውም በደል ስንኳ ቢገኝ፥ መንፈሳውያን የሆናችሁ እናንተ እንደዚህ ያለውን ሰው በየውሃት መንፈስ አቅኑት" ገላ. 6:1

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

የፌስቡክ ገጽ :- https://t.me/eotcy
763 viewsᵇᵉⁿᵒⁿ 🅸🅽 , 04:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 06:46:13
አበው ስለ እመቤታችን እንዲህ አሉ

"አምላክ ከንጉሥ ሔሮድስ ሴት ልጅ ቢወለድ ኖሮ አልጋ ወራሽ በሆነና ባልተሰደደ ነበር። እርሱ ግን የድሆች ልጅ የሆነችውን ድንግል መረጠ"
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

"ታላቁ ተራራ ሆይ ታናሽዋ ብላቴና የተሸከመችህ ራስህን በሚቻላት መጠን አድርገህላት ነው ፣ ታላቁ እሳት ሆይ ታናሽዋ ብላቴና ተሸክማህ ያልተቃጠለችው ኃይልን ትችል ዘንድ አጽንተሃት ነው "
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ

"ይህ ዓለም የእግዚአብሔርን ልጅ በቀጥታ ከእግዚአብሔር አብ እጅ ለመቀበል የተገባ ሆኖ ስላልተገኘ ፣ ዓለም ከእርስዋ ይቀበል ዘንድ አንድያ ልጁን ለድንግል ማርያም እናት ትሆነው ዘንድ ሠጣት"
ቅዱስ አውግስጢኖስ

"ሔሮድስ የማይያዘውን ይይዝ ዘንድ ተነሣ ፣ ዓውሎ ነፋስንም በቤቱ አስገብቶ ሊዘጋ ታገለ"
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

"ጌታ ሆይ እናትህን ማን ብለን እንጥራት? እናት ብቻ እንዳንላት ድንግል ሆና አገኘናት ፣ ድንግል እንዳንላት ልጅ ታቅፋ አየናት። ጌታ ሆይ እናትህን ለመጥራት እንዲህ የሚያስቸግር ከሆነ አንተን ከቶ ምን ብለን እንጠራሃለን??"
ቅዱስ ኤፍሬም

ጽሑፉን ይጫኑት

@eotcy
@eotcy
@eotcy
936 viewsᵇᵉⁿᵒⁿ 🅸🅽 , edited  03:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 19:58:05 #ቤተ_ክርስቲያን_የመሳለም_ሥርዓት

ጠዋትና ማታ ቤተ ክርስቲያን ለመሳለም መትጋት ያስፈልጋል። (ምሳ.8:34)
ወደ ቤተክርስቲያን ሲገባ ከቅፅረ ቤተክርስቲያን በር ላይ ሲደርሱ መሳለም ይገባል።
@eotcy
መዝ.28፥2፣ 95፥9፣ ኤር.26፥2፣ ሕዝ.46፥3፣ ፊልጵ 2፥9-10
ሁላችሁም አስተውሉ ስንሳለም እንደት ነው????

መጀመሪያ ቀኝ እጅን ላይ ዋ ጣታችንን ቀጥ እናደርጋለን
ከዛ እረጅም ወይም የመሀል ጣታችንን እጥፍ እናደርጋለን ከ ዋ ጣት ጋር ስናገናኘው መስቀል ይሰራል ከዋላ ያሉትን ሁለት ጣቶች እንዲመቸን አጠፍ አጠፍ እናደርጋቸዋለን።
@eotcy
#ምሳሌያቸው

በቀኝ እጅ መሳለማችን ገነትን በመሻት ወይም እግዚአብሔር በገነት ስለሆነ ያለው ገነትን ለማመልከት ነው።

መስቀል መስራችን ደግሞ መዳናችንን ለማመልከትና እንደተሰቀለ ለመመስከር ነው።
@eotcy
ስንሳለም በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ማለት አለብን።
ትርጉሙም፥ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ ነው ማለት ነው።

ስንሳለም፥ መጀመሪያ መስቀል እንደሰራን በቀኝ እጃችን ግንባራችን ላይ እናደርጋለን።

#ምሳሌው፥ እግዚአብሔር በሰማይ እንደሚኖር እንደማይመረመር ለመግለፅ ነው።
@eotcy
ከዛ፥ ወደ ታች እደረታችን እና ሆዳችን አካባቢ እናደርጋለን።

ምሳሌው፥ ጌታ ከሰማየ ሰማያት መውረዱን ከድንግል ማርያም መወለዱን ለመግለ ነው።

ከዛ፥ ወደ ግራ ጎንአችን ከጡታችን በላይ እናደርጋለን።
@eotcy
#ምሳሌው፥ አዳም አባታችን የሞትን ሞት እንደሞተ እና ሲኦል እንደ ገባ ለመግለፅ ነው።

በመጨረሻም፥ ወደ ቀኝ ጎናችን እናደርጋለን።

#ምሳሌው፥ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ከገነት ይዞ ጠላታችን ዲያቢሎስን አስፎ ወደ ገነት መግባቱን ለመግለፅ ነው።
@eotcy
ወደ ቤተክርስቲያን ሲገቡ ጫማን አውልቆ ወገብን ታጥቆ አደግድጎ መግባት ነው። ጫማ አድርጎ ቤተ ክርስቲያን መግባት ክልክል ነው።
ዘፀ 3፥5- ዮሐ.ሥ 7፥33
ኢያ 5፥ 15 ፍት፡መን፡12

ሃሳብን በመንፈሳዊ ነገር ወስኖ ወደ ውጪ ወደ አለማዊ ነገር እንዳይሄድ መግታትና መቆጣጠር ያስፈልጋል።
ከካህን ቀርቦ መስቀል መሳለምና በረከትም መቀበል ያሻል።
@eotcy
በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተስለው የሚገኙትን የሥላሴን ፣ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ፣ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ፣ የመላእክትን ፣
የነቢያትን ፣ የፃድቃንን ፣ የሰማዕታትን ፣ የደጋጎች ቅዱሳንን ሥዕሎች እጅ መንሳትና የአክብሮት ስግደት መስገድ ይገባል።

በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አስተውሉመሳቅ
ሥለ አለማዊ ሥራ መነጋገር ክልክል ነው።

ከገቡ በኋላ:ዝምታ:ፀጥታ
ፍርሃት የእግዚአብሔርን ምህረት በጥብዓተ ልብ መፈለግ አለብን።
@eotcy
ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያን የመዘምራንን ማሕሌት፣ የቅዱሳን መላእክትን ምስጋና ፣ የነቢያትን ትንቢት ፣ የሐዋርያትን ስብከት መስሚያና የልዑል እግዚአብሔርን ነገር መማሪያ ቦታ ስለሆነች ነው።

ከዚህም በላይ የሥጋ ወደሙ ምስጢር የሚፈፀምበት ቦታ ስለሆነች ነው።
ዘሌ. 26፥2
@eotcy
#አስተውሉ
አጭርና ያደፈ ልብስ ለብሶ ወደ ቤተክርስቲያን መሔድ ክልክል ነው። ረዘም ያለ እና ንፁህ ልብስ ለብሶ መሔድ ያስፈልጋል።
ዘፀ. 19፥10-11
@eotcy
በተለይ #ሴቶች እራሳችንን ተከናንበን እንዲንፀልይ ታዘናል።

በመጨረሻም ወደ ቤተክርስቲያን ባዶ እጅ መሔድ አይገባም ። መባዕ፣ ምፅዋት ይዞ መሔድ ይገባል። ዘጸ.34፥20
ወሰብሐት ለእግዚአብሔር
shear አርጉት!
Join @eotcy
637 viewsᵇᵉⁿᵒⁿ 🅸🅽 , 16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ