Get Mystery Box with random crypto!

#ቤተ_ክርስቲያን_የመሳለም_ሥርዓት ጠዋትና ማታ ቤተ ክርስቲያን ለመሳለም መትጋት ያስፈልጋል። ( | ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች

#ቤተ_ክርስቲያን_የመሳለም_ሥርዓት

ጠዋትና ማታ ቤተ ክርስቲያን ለመሳለም መትጋት ያስፈልጋል። (ምሳ.8:34)
ወደ ቤተክርስቲያን ሲገባ ከቅፅረ ቤተክርስቲያን በር ላይ ሲደርሱ መሳለም ይገባል።
@eotcy
መዝ.28፥2፣ 95፥9፣ ኤር.26፥2፣ ሕዝ.46፥3፣ ፊልጵ 2፥9-10
ሁላችሁም አስተውሉ ስንሳለም እንደት ነው????

መጀመሪያ ቀኝ እጅን ላይ ዋ ጣታችንን ቀጥ እናደርጋለን
ከዛ እረጅም ወይም የመሀል ጣታችንን እጥፍ እናደርጋለን ከ ዋ ጣት ጋር ስናገናኘው መስቀል ይሰራል ከዋላ ያሉትን ሁለት ጣቶች እንዲመቸን አጠፍ አጠፍ እናደርጋቸዋለን።
@eotcy
#ምሳሌያቸው

በቀኝ እጅ መሳለማችን ገነትን በመሻት ወይም እግዚአብሔር በገነት ስለሆነ ያለው ገነትን ለማመልከት ነው።

መስቀል መስራችን ደግሞ መዳናችንን ለማመልከትና እንደተሰቀለ ለመመስከር ነው።
@eotcy
ስንሳለም በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ማለት አለብን።
ትርጉሙም፥ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ ነው ማለት ነው።

ስንሳለም፥ መጀመሪያ መስቀል እንደሰራን በቀኝ እጃችን ግንባራችን ላይ እናደርጋለን።

#ምሳሌው፥ እግዚአብሔር በሰማይ እንደሚኖር እንደማይመረመር ለመግለፅ ነው።
@eotcy
ከዛ፥ ወደ ታች እደረታችን እና ሆዳችን አካባቢ እናደርጋለን።

ምሳሌው፥ ጌታ ከሰማየ ሰማያት መውረዱን ከድንግል ማርያም መወለዱን ለመግለ ነው።

ከዛ፥ ወደ ግራ ጎንአችን ከጡታችን በላይ እናደርጋለን።
@eotcy
#ምሳሌው፥ አዳም አባታችን የሞትን ሞት እንደሞተ እና ሲኦል እንደ ገባ ለመግለፅ ነው።

በመጨረሻም፥ ወደ ቀኝ ጎናችን እናደርጋለን።

#ምሳሌው፥ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ከገነት ይዞ ጠላታችን ዲያቢሎስን አስፎ ወደ ገነት መግባቱን ለመግለፅ ነው።
@eotcy
ወደ ቤተክርስቲያን ሲገቡ ጫማን አውልቆ ወገብን ታጥቆ አደግድጎ መግባት ነው። ጫማ አድርጎ ቤተ ክርስቲያን መግባት ክልክል ነው።
ዘፀ 3፥5- ዮሐ.ሥ 7፥33
ኢያ 5፥ 15 ፍት፡መን፡12

ሃሳብን በመንፈሳዊ ነገር ወስኖ ወደ ውጪ ወደ አለማዊ ነገር እንዳይሄድ መግታትና መቆጣጠር ያስፈልጋል።
ከካህን ቀርቦ መስቀል መሳለምና በረከትም መቀበል ያሻል።
@eotcy
በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተስለው የሚገኙትን የሥላሴን ፣ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ፣ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ፣ የመላእክትን ፣
የነቢያትን ፣ የፃድቃንን ፣ የሰማዕታትን ፣ የደጋጎች ቅዱሳንን ሥዕሎች እጅ መንሳትና የአክብሮት ስግደት መስገድ ይገባል።

በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አስተውሉመሳቅ
ሥለ አለማዊ ሥራ መነጋገር ክልክል ነው።

ከገቡ በኋላ:ዝምታ:ፀጥታ
ፍርሃት የእግዚአብሔርን ምህረት በጥብዓተ ልብ መፈለግ አለብን።
@eotcy
ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያን የመዘምራንን ማሕሌት፣ የቅዱሳን መላእክትን ምስጋና ፣ የነቢያትን ትንቢት ፣ የሐዋርያትን ስብከት መስሚያና የልዑል እግዚአብሔርን ነገር መማሪያ ቦታ ስለሆነች ነው።

ከዚህም በላይ የሥጋ ወደሙ ምስጢር የሚፈፀምበት ቦታ ስለሆነች ነው።
ዘሌ. 26፥2
@eotcy
#አስተውሉ
አጭርና ያደፈ ልብስ ለብሶ ወደ ቤተክርስቲያን መሔድ ክልክል ነው። ረዘም ያለ እና ንፁህ ልብስ ለብሶ መሔድ ያስፈልጋል።
ዘፀ. 19፥10-11
@eotcy
በተለይ #ሴቶች እራሳችንን ተከናንበን እንዲንፀልይ ታዘናል።

በመጨረሻም ወደ ቤተክርስቲያን ባዶ እጅ መሔድ አይገባም ። መባዕ፣ ምፅዋት ይዞ መሔድ ይገባል። ዘጸ.34፥20
ወሰብሐት ለእግዚአብሔር
shear አርጉት!
Join @eotcy