#ቤተ_ክርስቲያን_የመሳለም_ሥርዓት ጠዋትና ማታ ቤተ ክርስቲያን ለመሳለም መትጋት ያስፈልጋል። (ምሳ.8:34) ወደ ቤተክርስቲያን ሲገባ ከቅፅረ ቤተክርስቲያን በር ላይ ሲደርሱ መሳለም ይገባል። @eotcy መዝ.28፥2፣ 95፥9፣ ኤር.26፥2፣ ሕዝ.46፥3፣ ፊልጵ 2፥9-10 ሁላችሁም አስተውሉ ስንሳለም እንደት ነው???? መጀመሪያ ቀኝ እጅን ላይ ዋ ጣታችንን ቀጥ እናደርጋለን ከዛ እረጅም ወይም የመሀል ጣታችንን እጥፍ እናደርጋለን ከ ዋ ጣት ጋር ስናገናኘው መስቀል ይሰራል ከዋላ ያሉትን ሁለት ጣቶች እንዲመቸን አጠፍ አጠፍ እናደርጋቸዋለን። @eotcy #ምሳሌያቸው በቀኝ እጅ መሳለማችን ገነትን በመሻት ወይም እግዚአብሔር በገነት ስለሆነ ያለው ገነትን ለማመልከት ነው። መስቀል መስራችን ደግሞ መዳናችንን ለማመልከትና እንደተሰቀለ ለመመስከር ነው። @eotcy ስንሳለም በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ማለት አለብን። ትርጉሙም፥ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ ነው ማለት ነው። ስንሳለም፥ መጀመሪያ መስቀል እንደሰራን በቀኝ እጃችን ግንባራችን ላይ እናደርጋለን። #ምሳሌው፥ እግዚአብሔር በሰማይ እንደሚኖር እንደማይመረመር ለመግለፅ ነው። @eotcy ከዛ፥ ወደ ታች እደረታችን እና ሆዳችን አካባቢ እናደርጋለን። ምሳሌው፥ ጌታ ከሰማየ ሰማያት መውረዱን ከድንግል ማርያም መወለዱን ለመግለ ነው። ከዛ፥ ወደ ግራ ጎንአችን ከጡታችን በላይ እናደርጋለን። @eotcy #ምሳሌው፥ አዳም አባታችን የሞትን ሞት እንደሞተ እና ሲኦል እንደ ገባ ለመግለፅ ነው። በመጨረሻም፥ ወደ ቀኝ ጎናችን እናደርጋለን። #ምሳሌው፥ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ከገነት ይዞ ጠላታችን ዲያቢሎስን አስፎ ወደ ገነት መግባቱን ለመግለፅ ነው። @eotcy ወደ ቤተክርስቲያን ሲገቡ ጫማን አውልቆ ወገብን ታጥቆ አደግድጎ መግባት ነው። ጫማ አድርጎ ቤተ ክርስቲያን መግባት ክልክል ነው። ዘፀ 3፥5- ዮሐ.ሥ 7፥33 ኢያ 5፥ 15 ፍት፡መን፡12 ሃሳብን በመንፈሳዊ ነገር ወስኖ ወደ ውጪ ወደ አለማዊ ነገር እንዳይሄድ መግታትና መቆጣጠር ያስፈልጋል። ከካህን ቀርቦ መስቀል መሳለምና በረከትም መቀበል ያሻል። @eotcy በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተስለው የሚገኙትን የሥላሴን ፣ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ፣ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ፣ የመላእክትን ፣ የነቢያትን ፣ የፃድቃንን ፣ የሰማዕታትን ፣ የደጋጎች ቅዱሳንን ሥዕሎች እጅ መንሳትና የአክብሮት ስግደት መስገድ ይገባል። በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አስተውሉመሳቅ ሥለ አለማዊ ሥራ መነጋገር ክልክል ነው። ከገቡ በኋላ:ዝምታ:ፀጥታ ፍርሃት የእግዚአብሔርን ምህረት በጥብዓተ ልብ መፈለግ አለብን። @eotcy ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያን የመዘምራንን ማሕሌት፣ የቅዱሳን መላእክትን ምስጋና ፣ የነቢያትን ትንቢት ፣ የሐዋርያትን ስብከት መስሚያና የልዑል እግዚአብሔርን ነገር መማሪያ ቦታ ስለሆነች ነው። ከዚህም በላይ የሥጋ ወደሙ ምስጢር የሚፈፀምበት ቦታ ስለሆነች ነው። ዘሌ. 26፥2 @eotcy #አስተውሉ አጭርና ያደፈ ልብስ ለብሶ ወደ ቤተክርስቲያን መሔድ ክልክል ነው። ረዘም ያለ እና ንፁህ ልብስ ለብሶ መሔድ ያስፈልጋል። ዘፀ. 19፥10-11 @eotcy በተለይ #ሴቶች እራሳችንን ተከናንበን እንዲንፀልይ ታዘናል። በመጨረሻም ወደ ቤተክርስቲያን ባዶ እጅ መሔድ አይገባም ። መባዕ፣ ምፅዋት ይዞ መሔድ ይገባል። ዘጸ.34፥20 ወሰብሐት ለእግዚአብሔር shear አርጉት! Join @eotcy 637 viewsᵇᵉⁿᵒⁿ 🅸🅽 , 16:58