Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ eotcy — ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
የቴሌግራም ቻናል አርማ eotcy — ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
የሰርጥ አድራሻ: @eotcy
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.36K
የሰርጥ መግለጫ

መንፈሳዊ ቻናል እንጋብዛቹ
@EOTCY
ምን አይነት ነገሮችን ነው የሚፈልጉት?
➢ የተለያዩ ትምህርቶችን
➢ መጣጥፎችን
➢ መንፈሳዊ ግጥሞችን
➢ ተከታታይ ትምህርቶችን
➢ ብሒለ አበው
➢ ወይስ ዜና ቤተክርስቲያን
አሁኑኑ ይቀላቀሉን የኦርቶዶክስ ተዋህዶን ቀጥተኛ አስተምህሮ ያገኙበታል👇👇👇
@EOTCY

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-07-05 11:41:14
ታላቅ የንግስ በዓል ጥሪ
ሰማዕታት የዚህችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ
ደማቸውንም ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ
ስለ መንግስተ ሰማያትም መራራ ሞትን ታገሱ
ውዳሴ ማርያም የሐሙስ

የሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስና የዓለም ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ሐምሌ 5 የእረፍት መታሰቢያ በዓልን ታስቦ ይውላል። ይህንን ታላቅ በዓል በስማቸው በተሰየመው በጥንታዊውና አንጋፋው ደብር በብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስወ ጳውሎስ እና ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ይከብራልእርሶም ከወዳጆቾ ጋር በመምጣት ከቃልኪዳናየው የሳተፉ ዘንድ በአምላከ ጴጥሮስወ ጻውሎስ ስም ተጋብቻችኃል።

አድራሻ ከፒያሳ ወደ አስኮ ሲመጡ ዊንጌት ዊንጌት ኮሌጅ አጠገብ
ከጦርኃይሎች መስመር ለሚመጡ እንዲሁ ከሁሉም አቅጣጫ ለሚመጡ ዊንጌት አደባባይ ገባ ብሎ
@eotcy
@eotcy
@eotcy
1.0K views𝔟𝔢𝔫𝔬𝔫 𝙗𝙚𝙣𝙖, edited  08:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 07:35:33 ንጉስ ሰሎሞን እና ጉንዳኗ

ንጉስ ሰሎሞን ለተፈጥሮ ባለው ፍቅር ይታወቃል እርሱ በየጊዜው በአትክልት ስፍራዎቹ በወንዝ ዳርቻዎችና በተራራዎች ላይ ይዘዋወር ነበር።

እርሱ እንስሳትን ወፎችን ዓሳዎችንና ነፍሳትን በፍላጎት በመመልከትና በደመ ነፍሳቸው ውስጥ የተገለጠውን የጥበባቸውን ጠባይ በማየት እግዚአብሔር ለእነርሱ ያለውን እንክብካቤ ያረጋግጥ ነበር።

ከዕለታት አንድ ቀን ታዲያ ትኩረቱ በአንዲት ትንሽ ጉንዳን ላይ ያርፋል። ጉንዳጊቱ ከእርሷ ክብደት ብዙ እጥፍ የሚበልጠውን የጥሬ ግማሽ ተሸክማ እየሄደች ነበር። ጉንዳኗ ይህን የጥሬ ስባሪ ተሸክማ የምትጓዘው በጉንድጓዷ ውስጥ ለማከማቸት ነበር።
@eotcy
በዚህ ጊዜ ንጉሡ እጅግ ስለተደነቀ ይህቺን ጉንዳን ለምንድን ነው የማላስደስታት ይላል። እርሱ ይህን ያለው ያላትን ጉልበት ሁሉ ከዚህ የጥሬ ድቃቂ ላይ ስታጠፋ ስለተመለከተ ነበር።
"እግዚአብሔር ይህን ያህል ታላቅ ሃብት ለእኔ የሰጠኝ ደስታን ለህዝቤ ብቻ እንድሰጥ ሳይሆን ለእንስሳትም ለወፎችም ለነፍሳት ጭምር እንድሰጥ ነው።
@eotcy
ንጉሡ ይህን ብሎ ጉንዳኒቱን ካነሳ በኋላ ውስጡ እጅግ ለስላሳ በሆነ ሐር የተነጠፈ የወርቅ ሳጥን ውስጥ ያስቀምጣታል። ከእርሷ ጋር በወርቅ ሳጥኑ ውስጥ አንድ የስንዴ ቅንጣት ካስቀመጠላት በኋላ ከፈገግታ ጋር በየዕለቱ ምንም ሳትደክሚ የምትበይውን የስንዴ ቅንጣት ስለምሰጥሽ ከእንግዲህ በኃላ አትደክሚም በጎተራዬ ውስጥ የተትረፈረፈው ጥሬ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን እንስሳትን ወፎችንና ነፍሳትን የሚመግብ ነው አላት።

ንጉሡ እንዲህ ያለውን መልካም እንክብካቤ ለእርሷ ስላደረገላት ጉንዳኒቱ ታመሰግለዋለች።
@eotcy
በሚቀጥለው ቀን ንጉሡ ወደ ጉንዳኒቱ ተመልሶ ሲመጣ የተመገበችውን የአንዱን ቅንጣት ስንዴ ግማሽ እንደሆነ ሲመለከት እጅግ ይደነቃል። ሌላ አንድ የስንዴ ቅንጣት አስቀምጦላት በሚቀጥለው ቀን ተመልሶ ሲመጣ ጉንዳኗ ግማሹን ቅንጣት ተመግባ ግማሹን እንዳስቀመጠች ይመለከታል።

ይህ ሁኔታ እየተደጋገመ መሄዱን የተመለከተው ንጉሥ ሰሎሞን ጉንዳኗን ለምንድን ነው ሁል ጊዜ የአንዱን ቅንጣት ስንዴ ግማሽ የምታስቀልጭው? በማለት ይጠይቃታል።
@eotcy
ጉንዳኒቱም እንዲህ በማለት መለሰችለት እኔ በየዕለቱ የስንዴውን ግማሽ የማስቀምጠው ለመጠባበቂያ ነው አንተ ለእኔ ምን ያህል እንክብካቤ እንዳደረክልኝና በጎተራዎችህ ውስጥ ምን ያህል የበዛ ጥሬ እንዳለህ አውቃለሁ ይሁን እንጂ አንተ ሰው ስለሆንክ በየዕለቱ የምትከውነው የስራህ ብዛት እኔን እንድትረሳኝ ያደርገሃል ይሄ በሚሆንበት ጊዜ ያስቀመጥኳትን የስንደ ቅንጣት ከረሃብ ትታደግልኛለች ምግቤን በድካሜ እንዳገኝ የተወኝ እግዚአብሔር አይረሳኝም አንተ ግን ልትረሳኝ ትችላለህ።

በዚህ ጊዜ ንጉሡ ጉንዳኗን ወደ ቀደመ ሕይወቷ ተመልሳ ኑሮዋን እንዴትቀጥል ይለቃታል
እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያስቀመጠውን ነገር ለእርሷ እንደሰጣት ተገንዝቧልና።

ፈጥሮ የማይጥል ወዶ የማይጠላ እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ክርስቲያኖች ሰው እንደተሰባሪ ብርጭቆ ነው።
እግዚአብሔርን የተመረኮዘ አይወድቅም።

.......የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ የመዳን ቀን አሁን ነው
-2ኛ ቆሮ6÷2

@eotcy
@eotcy
@eotcy
513 views𝔟𝔢𝔫𝔬𝔫 𝙗𝙚𝙣𝙖, edited  04:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 12:24:17 ዛሬ ይህቺን ልበላችሁ


እጅህ ላይ ከታመንህ እግዚአብሔር አምላክ በእጁ ውስጥ ያለውን ነገር ይሰጥሃል።


በውስጥህ ያለውን አቅም መጠቀም ከቻልህ እግዚአብሔር የአንተ ያልሆነ ተጨማሪ አቅም ይሰጥሃል።


ከእግረኞች ጋር ሳትደክም እኩል መራመድና መቅደም ከቻልህ እግዚአብሔር ፈረስን ለውድድር ይሰጥሃል። ኤር. 12፥5


የሚታዩ ኃጢአቶችን ለመዋጋት ታምነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር የተሸሸጉና የማይታዩ ኃጢአቶችን ድል እንድትነሣ ይሾምሃል።


በሕፃንነትህ በልጅነትህ ለእግዚአብሔር የታመንህ ሆነህ ከተገኘህ እርሱ በወጣትነትህ በምታደርገው ውጊያ ውስጥ ታማኝነትን ያድልሃል።


ልያን ለመቀበል ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር ራሔልን ሚስት አድርገህ ታገባት ዘንድ ይሰጥሃል። ዘፍ. 29፥27

በሲና ምድረ በዳ ለመቀመጥ ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር አምላክ የተስፋይቱን ምድር ከንዓንን ያወርስሃል።


በዚህ በተወሰነና አጭር ሕይወት ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር መጨረሻ የሌለውን ዘላለማዊ ሕይወት ያድልሃል።

#ልብ_በሉ

ትልቁ ቁም ነገር በእጅህ ውስጥ የገባው ነገር ትንሽም ይሁን ጥቂት በእርሱ መታመን መቻልህ ነው።

ስለሆነም ባለህ አንድ መክሊት ታምነህ ስትገኝ እግዚአብሔር አምስት መክሊቶችን በአደራ ይሰጥሃል።

አንተ በሚታዩት ነገሮች ላይ ታማኝ ሆነህ ስትገኝ እርሱ በማይታዩት ነገሮች ላይ ይሾምሃል።

በመሆኑም ዓይን ያላየችውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልብ ያልታሰበውን መንግሥቱን ያወርስሃል። 1ኛ ቆሮ 2፥9

(አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ - መንፈሳዊው መንገድ መጽሐፍ አያሌው ዘኢየሱስ እንደተረጎመው።)

የሕይወት ፡ እናቱ ፡ ሆይ፤ ተቀዳሚ ፡ ተከታይ ፡ በሌለው ፡ በአንድ ፡ ልጅሽና ፡ በእኛ ፡ መካከል ፡ አስታርቂን።

እነሆ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው
-1ኛቆሮ 6÷2

Join @eotcy
663 views𝔟𝔢𝔫𝔬𝔫 𝙗𝙚𝙣𝙖, 09:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 18:15:31 " #ከምታማኝ_ስመለስ_ምከረኝ "
.......................................

ይህንን ጥቅስ ዛሬ በታክሲ ተሳፍሬ ወደ ቤቴ ስጓዝ ተለጥፎ ተመለከትኩ። ሀሳቡ ስለገዛኝ ደጋግሜ አብሰለሰልኩት። ትልቅ መልእክት ነው።

ሐሜት ማለት በቁሙ ዐሚታ ፣ነቀፋ ፣ስድብ ፣ክፉ ነገር፣ ገመና ፣ነውር ፣ስም የሚያጠፋ ፣የሚሰብር በእውነት ወይም በሐሰት የሚነገር ማለት ነው፡፡
ሐሜት ሰውን ያለመሳሪያ የሚገድል መሳሪያ ነው።

ሐሜት በራሳቸው የማይተማመኑ ስለሚያወሩት ነገር እንኳን እርግጠኛ ያልሆኑ ማስረጃቸውን እንኳን "በአሉ" የሚያቀርቡ የራሳቸው ሀሳብ የሌላቸው የዝቅተኛ አስተሳሰብ ባለቤት የሆኑ ሰዎች የስራ ዘርፍ ነው።

<< ለሐሜት የሚሄድ ሚስጢሩን ይገልጣል ፣ በመንፈስ የታመነ ግን ነገሩን ይሰውራል " ምሳ 11÷13
እንደሚል ቅዱስ ቃሉ ሐሜተኛ ሰው #በእግዚአብሔር በሰውም ዘንድ የተጠላ ነው። ስለዚህ ሰውን ከምናማው ይልቅ ጥፋቱን እንገረው ምን አልባት ጥፋታቸው
ሲነገራቸው የማይቀበሉ፣ የማይሰሙ፣ የሚያኮርፉ፣ የሚናደዱ እና
የሚጠሉንም ጭምር ይኖራሉ እኛ ግን ይህን ሁሉ ቢያስቡም ከምናማቸው
መንገር ብቻ ነው ትክክለኛ መፍትሔው መምከርም ጭምር ያስፈልጋል ሐሜት በጥቅሉ አላስፈላጊ ነገር ነው
#ሐዋርያው_ቅዱስ_ጴጥሮስ እንደተናገረ
"እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኮልንም ሁሉ ግብዝነትም ቅንዓትም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደሆነ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደተወለዱ ህጻናት ተንኮል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ"
1ኛ ጴጥ 2÷1-3

እንደተባለ #ከእግዚአብሔር ለመገናኘት ህጉንና ትዕዛዛቱን በመፈጸም እንደ ህጻናት ልንሆን ያስፈልጋል
" እንደ ሕፃናት ካልሆናችሁ ከቶ የእግዚአብሔርን መንግሥት አትወርሱም " ማቴ 18÷3 ከሐሜት መራቅ ያስፈልጋል።

ሌሎች ሰዎችም ሐሜት ሲጀምሩልን እንደ ሶቅራጥስ ይህንን እንጠይቃቸው...

በአንድ ወቅት ወደ ታላቁ ፈላስፋ ወደ ሶቅራጥስ አንድ ሰው መጥቶ እንዲህ አለው ፡-

‹‹እገሌ ስለተባለው ወዳጅህ የሠማሁት ደስ አይልም›› አለው፡፡ ሶቅራጦስ ግን ዝም አለ፡፡ ሠውየውም እንደገና፡- ‹‹ይገርማል ከእርሱ አይጠበቅም፤ በጣም ገርሞኛል›› አለው፡፡

ሶቅራጠስም እንደማይለቀው ስለተረዳ፡-
‹‹ ስለ ወዳጄ ልትነግረኝ የፈለግከውን ልሠማው የምችለው ሶስት ጥያቄዎች አሉኝ፤ እነርሱን ስትመልስልኝ ብቻ ነው›› አለው፡፡ ሠውየውም ተስማማ፡፡

1,‹‹የመጀመሪያው ጥያቄዬ የእውነት ጥያቄ ነው፡፡

" ስለወዳጄ የሠማኸው መቶ በመቶ እውነት ነው ወይ?›› አለ፡፡

ሠውየውም፡- ‹‹መቶ በመቶ እርግጠኛ መሆን አልችልም››አለው፡፡ ያው እንግዲህ " አሉ " እያለ ሊያወራ ነበር።

ሶቅራጦስም ቀጠለ፡-

2,‹‹ልትነግረኝ የፈለግከው እርግጠኛ ያልሆነነገር ነው ማለት ነው፤ ሁለተኛው ጥያቄዬ የመልካምነት ነው፡፡ " የምትነግረኝ መልካም ነገር ነው ወይ?›› አለው፡፡

ሰውየውም፡- ‹‹እርሱማ መልካም አይደለም›› አለው፡፡

ሶቅራጦስም፡-

3,‹‹አንደኛ እውነትነቱ ያልተረጋገጠ፤ ሁለተኛ መልካም ያልሆነ ነገር ልትነግረኝ ፈልገሃል፡፡ ሶስተኛ ጥያቄ አለኝ?›› አለው፡፡
ሠውየውም፡- ‹‹እሺ›› አለ፡፡

ሶቅራጦስም፡-

4,‹‹ለእኔ የሚጠቅመኝ ነገር አለው ወይ?››አለው፡፡

ሠውየውም፡- ‹‹የለም›› ብሎ መለሠ፡፡ሶቅራጦስም በመጨረሻ፡-

5,‹‹እውነትነቱ ያልተረጋገጠ፤ መልካም ያልሆነ፤ ለእኔ የማይጠቅም ነገር አልሠማም››አለው ይባላል፡፡

ወዳጆቼ እውነትነቱ ያልተረጋገጠ፣ መልካም ያልሆነ እና በሕይወታችን ላይ ጉልህ ሚና የሌለው ነገር ላይ ጊዜን ማጥፋት ትልቅ ብክነት ነው፡፡አንዳንድ ሠዎች በማይመለከታቸው ነገር እድሜአቸውን ይገፋሉ፡፡ በዚህም መልሠው ማግኘት የማይችሉትን ውዱን ጊዜአቸውን የሰውን ሥጋ በመብላት ያባክናሉ።

ሐሜት የሰውን ስጋ እንደመብላት ስለሆነ ሁላችንም ከሐሜት እራሳችንን ልናርቅ ይገባል !!

መልካም ምሽት ይሁንላችሁ




@eotcy
@eotcy
@eotcy
494 views𝔟𝔢𝔫𝔬𝔫 𝙗𝙚𝙣𝙖, edited  15:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 04:17:52 #ሦስት_ስገድ
___
አንድ ሰው በጣም ይጸጸት እና ንስሐ ገብቶ ተገቢውን ቀኖና (ቅጣት) ተቀብሎ ፈጣሪውን እያስደሰተ ለመኖር ወስኖ ወደ አንድ ካህን ይመጣል።
ካህኑም ተገቢውን የአባትነት አቀባበል አድርገውለት ሲያበቁ የመጣበትን ጉዳይ ማስረዳት ቀጠለ ። ከዚያም ልቦናውን ታዛቢ ፣ አንደበቱን ከሳሽ ፣እግዚአብሔርን ዳኛ አድርጎ የሠራውን ልዩ ልዩ ዘግናኝና ከባባድ ኃጥያት አንድ በአንድ በዝርዝር ተናገረ ። እኒያ አባት ሁሉን በትእግስት ካዳመጡ ቡኃላ ተገቢውን ምክርና ተግሳጽ ሰጥተው ሲጨርሱ
"በል ሦስት ስገድ " ይሉታል ። ሰውዬውም
" በየቀኑ ሦስት ሦስት ማለትዎ ነው አባቴ ?" ይላቸዋል ። ካህኑም "የለም የለም ሦስት ብቻ ስገድ " አሉት ።
በዚህ ጊዜ ሰውዬው በጣም ተገርሞ " እንዴ አባቴ ሦስት ነው ወይስ ሶስት መቶ ነው ? " ሲል አስረግጦ ይጠይቃቸዋል ። ካህኑም " ኧረ ሦስት ነው ያልኩህ ልጄ የምን ሶስት መቶ አመጣህብኝ እንዴ ያላልኩትን? #ብቻ_ስትሰግድ_በደልህን እያሰብክ የፈጣሪህን ምህረት እና ይቅርታ ከልብህ እየተማጸንክ በልብህ ጉልበት ጭምር ስገድ " ይሉታል ። ሰውዬውም በጣም እየተገረመ እና እየተደነቀ የካህን ትዕዛዝ ነው እና አመስግኖ ተነስቶ ይሔዳል። ከዚያም እግዚአብሔር ለካህኑጨ(ለንስሐ አባቱ) ይገለጥለት እና
" እንዴት እንዴት ነው ያን ሁሉ ኃጥያት ነግሮህ ሲያበቃ ሦስት ብቻ ስገድ የምትለው ? " ሲል ይጠይቃቸዋል ። እኒያ አባትም ፈገግ እያሉ
" አይ ፈጣሪዬ ይሄንንም እኔ ሁኜ ነው እንጂ አንተ ብትሆን እኮ በነጻ ነበር የምታሰናብተው " አሉት ይባላል ።
.........................

ይኼ የእግዚአብሔርን ከባቴ አበሳነት በሚገባ የሚያስረዳ ምናባዊ ታሪክ ነው ።
እንዲህ ሲባል ንስሐ አያስፈልግም ማለት ሳይሆን ያለ እግዚአብሔር ቸርነት ሦስትም ሦስት መቶም ብንሰግድ ጥቅም እደሌለን እድናውቅ ነው።
ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የእግዚአብሔርን መሐሪነት እዲህ ይገልጠዋል። " የራበው ሰው ለምግብ፤ የጠማው ሰው ለመጠጥ እደሚቸኩል እግዚአብሔርም እኛን ለመማር / ምህረት ለመስጠት / ይቸኩላል" አባቶቻችንም የእግዚአብሔርን የምሕረቱን ጥግ ስለሚያውቁ ርህሩህ ናቸው።
እንደ ኃጥያታችን ክፋት አይቶ ምህረቱን ከኛ ያላራቀ የቅዱሳን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው ። " ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምህረት የተነሳ ነው፤ ርኀራኄው አያልቅምና" ኤር 3፥23

.....እነሆ የተወደደወ ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው
-1ኛ ቆሮ6÷2


ይህን በመንካት ይቀላቀሉን
ይህን በመንካት ይቀላቀሉን
ይህን በመንካት ይቀላቀሉን
1.5K views𝔟𝔢𝔫𝔬𝔫 𝙗𝙚𝙣𝙖, edited  01:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 04:14:57
383 views𝔟𝔢𝔫𝔬𝔫 𝙗𝙚𝙣𝙖, 01:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 13:12:26 ወንድሞቼ አና እህቶቼ የማክበር ሰላምታዬን እያቀረብኩ መልእክቴን አደርሳለሁ ይህንን መልእክት ለውድ ኦርቶዳክሳውያን ሼር በማድረግ ተባበሩን። በመጀመሪያ ከላይ የላኩትን የሀሰት ድምጽ ይስሙት
@eotcy
የውሸት አስተምሮ ነው አትመኑ እየተበተነ ነው ይህም አስተምሮ አጠር አርጌ እገልጽላቾኋለሁ
@eotcy

ውሸቱም

የተወደድክ እባክህ ለማንበብና ለማስተላለፍ ሞክር፡ እውነተኛ ታሪክ ነውና።
አንድ የታመመች ሴት ነበረች በህልሟም የድንግል ልጅ ጌታችን መደኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንድትጠጣ ውሀ ሲሰጣት አየች፡ ..................

የሚል ነበር ሙሉዉን ከላይ ለቅቄላች ኋለሁ

እባክህን ይሄን መልዕክት ለ 13 እና ከዛ በላይ ለሆኑ ለምታውቃቸው ሰዎች ላክ እና እመነኝ የሆነ ነገር በህይወትህ ይክሰታል።
ይቅርታ ስለረበሽኩህ ፡ እኔ አምላክህ ነኝ፡

የገረመኝ አምላክ ከመቼ ጀምሮ ነው ጹሁፍ መጻፍ የጀመረው
@eotcy
ጸልይ አልልህም ብቻ አወድሰኝ(አሞግሰኝ) እና እባክህ እስከ ሌሊት በቻልከው መጠን ለአለም ሁሉ ይሄን መልእክት ላክ።
@eotcy
የሰው ልጅ ካልጸለየ አምላኩ ጋር በምን ይገናኛል አስተውሉ ወገኖቼ

በእግዚአብሔር የምትተማመን ከሆን መልእክቱን ላክ ነገህ ደሰ የሚያሰኝ ይሆንልሀል።
እኛ ኦረቶዶክሳዊያን ሁሌም በእግዚአብሔር እንተማመናለን
@eotcy
ግን በህይወትህ ለእግዚአብሔር ቅድሚያ ትሰጣለ? አዎ ከሆነ መልስህ አሁን የምትሰራውን ነገር ሁሉ ትተህ ይሄን መልእክት ለ12 ሰዎች አሁኑኑ ላክ

ለእግዚአብሔር ቅድሚያ የሚሰጠው ጹሁፍ ባሰራጨ ሳይሆን ለስሙበመዘመር
ጾም በመጾም ጸሎት በማድረግ እና
ኦርቶዳክሳዊ ሰነምግባር በመላበስ ነው
@eotcy
መልእክት ለ12 ሰዎች አሁኑኑ ላክ ከዛ ጌታ ነገ ምን እንደሚያደርግልህ ታያለህ እግዚአብሔር ይወድሀል። እመነኝ ከ 7 ቀን በኋላ ህልምህ እውን ይሆናል።

እዩት በጣም ውሸት መሆኑን ከዚ እንረዳለን ለ 12 ሰዎች ስለተላከ ምንም አይነት ህልም እውን እንደማይሆን አጥብቄ እነግራችኋለሁ
@eotcy
ይህን የውሸት ጹሁፍ መንፈሳዊ አስመስለው የእናታችንን ድንግል ማርያምን ስም ከተው ኦርቶዳክሳዊያን እህት ወንድሞቻችንን ሲያታሉ አመታት ተቆጥረዋል አሁን ግን ከዚህ ተረድታቹ የሚላክላችሁን ጹሁፍ ትክክል መሆኑን አባቶችን በመጠየቅ ተረድታቹ ነው ለሰው ሼር ማረግ ያለባቹ
ባላቹሁበት በሰላም ቆዩልኝ

ህይወት የሚሰጠንን ቅዱስ ቃሉን ብቻ ሼር እናድርግ

@eotcy
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
562 viewsቤንኦኒ, 10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 13:12:26 እባካችሁ የተሳሳተ voice ነው ሼር በማድረግ አትተባበሩ ሙሉውን ከታች ይነበብ
Https://t.me/eotcy
453 viewsቤንኦኒ, edited  10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 20:44:17 *********************

#የወር_አበባ በድጋሚ የተለቀቀ

በውስጥ መስመር በተደጋጋሚ የመጡ ጥያቄዎች
ለህቶቻቻችን ይዳረስ ዘንድ ያጋሩልን
#በወር_አበባ_ጊዜ_መስቀል_መሳለም_መጽሐ_ቅዱስ_እና_ሌሎች_ጸሎት_መጽሀፍትን_ማንበብ_ይቻላል

እንዲሁም ወደ ቤተክርስትያን መሄድ ይቻላል
የወር አበባ በሴቶች ላይ በየወሩ የሚታይ የደም መፍሰስ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን
አስተምህሮ “ደመ ጽጌ፣ አበባ ደም” በመባል ይጠራል፡፡አሰያየሙም የወንድ ዘር
ካላገኘ ከማህጸን ግድግዳ ፍራሽ ጋር በደም መልክ ስለሚፈስና የኋለኛው
ማንነቱ ደምነት ስለሆነ ነው፡፡ ይህም ማለት አገልግሎቱን የጨረሰ፣ ያረጀ፣ ቆሻሻ
ማለት ነው፡፡ ይህ በየወሩ ዑደትን ተከትሎ የሚሄደው የዘር ፍሳሽ በስነ ህይወት
ትምህርት ኦቫሪ (ከዘር ከረጢት) የሚለቀቅ የወንድ ዘር ካላገኘ ኦቫ (ሴቴ ዘር)
ጋር እየተቀላቀለ የሚወርድ ነው፡፡

የወር አበባ #በቤተክርስቲያን አስተምህሮ በሁለት ከፍለን ነው መመልከት ያለብን፤ በዘመነ ኦሪትና ዘመነ ሐዲስ ኪዳን በማለት፡፡
በርግጥ በዘመነ ኦሪት የወር አበባ የርኩሰትና የመርገም ምልክት ነበር፡፡ ለዚህም
ማስረጃነት በመጽሃፍ ቅዱስ ዘሌ 18÷19፣ 20÷18 ያሉ ጥቅሶች “በመርገምዋ
ርኩሰት ሳለች” እና “#ባለ_መርገም_ሴት” በማለት ሲገልጸው፤ ባንጻሩ ደግሞ
ከወር አበባዋ ነጻ የሆነችውን ሴት “#ከርኩሰትዋ_ነጽታ” በማለት የወር አበባ
የርኩሰትና የመርገም ምልክት መሆኑን ይጠቁማል፡፡
በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የወር አበባ የርኩሰትና የመርገም ምልክት መሆኑ ቀርቷል፡፡
ርኩሰት አይደለም፤ ርኩስም አያሰኝም፡፡ በብሉይ ኪዳን አዳምና ሄዋን በገነት
በነበሩ ጊዜ ዕጸ በለስን በልተው #እግዚአብሔርን በደሉ፤ እግዚአብሔርም ሄዋንን
ደመ ዕጸ በለስን አፍስሰሻልና “ወበከመ አድመውኪያ ለእንትኩ ዕጽ ከማሁ
ድምዊ ለለወርኁ፡፡” በማለት ደሟ በየወሩ እንዲፈስ ፈጣሪ ፈረደባት፡፡ ስለዚህ
የሄዋን ደም መፍሰስ መነሻው መርገም ነው፡፡ በሐዲስ ኪዳን #ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በፈጸመው #ቤዛነት መርገምነቱና ርኩስነቱ
ተወግዷል፡፡
የወር አበባ በዚህ ዘመን ርኩሰት ወይም መርገም ባይሆንም እድፍ (ቆሻሻ) ነው፡፡

እድፍና ርኩሰት ልዩነት አላቸው፡፡
ርኩሰት ውስጣዊ ነው፤ በንስሃ እንጂ በውሃ አይጠራም፡፡ እድፍ ደግሞ ግዘፍ
አካል ያለው፣ የሚታይና ውሃ የሚያነጻው ነው፡፡ የወር አበባ በሴቶች ባህሪ ሳለ
እንደ ቆሻሻ አይቆጠርም፣ ከሰውነት ሲወገድ ግን ይቆጠራል፡፡ ይህንን
ለማስረዳት ምሳሌ መሆን ከሚችሉት ውስጥ ዛህል (ንፍጥ)፣ ሽንት፣ ምራቅ፣
ዓይነምድርና ሌሎችንም መጥቀስ ይቻላል፡፡

#ያስተውሉ

ወር አበባ ርኩሰት ባለመሆኑ መስቀል ከመሳም፣ ቤተክርስቲያን ከመሔድ፣ ከመጸለይ፣ ቅዱሳት መጻህፍትን
ከማንበብና ከመድገም አያግድም፡፡
ነገር ግን ከሩካቤ፣ ከመጠመቅ፣ ከመቁረብና ቤተ መቅደስ ከመግባት ይከለክላል፡፡

#ከሩካቤ :-

ሩካቤ በወር አበባ ጊዜ ከሚከለከሉ ነገሮች አንዱ ነው፡፡ በወር አበባ ጊዜ
የሚደረግ ግንኙነት የህክምና ባለሙያዎች ሳይቀር ለአባላዘር፣ ለልዩ ልዩ
በሽታዎችና ለኢንፌክሽን ሊያጋልጥ እንደሚችል በመናገር እንዳይፈጸም
ይመክራሉ፡፡
በመንፈሳዊው አስተምህሮ ስንመለከተው ደግሞ የሰው ልጅ ዘር #ቅዱስ በሆነው #በእግዚአብሔር አምሳል በመፈጠሩ፣ ይህንን የተከበረ ዘር፣ እዳሪ
ወይም ቆሻሻ ከሆነ ደም ጋር ማዋሃድ ኃጢያት እንደሆነ ይቆጠራል፡፡
#በመጽሐፍ_ቅዱስ ሴት ልጅ በወር አበባዋ ጊዜ እንዳለች የሚፈጸምን ሩካቤ

እርሷም በመርገምዋ ርኩሰት ሳለች ኃፍረተ ሥጋዋን ትገልጥ ዘንድ ወደ እርሷ
አትቅረብ” ዘሌ 18÷19፣ ዘሌ 20÷18።

በዚህም ምክንያት በወር አበባ ጊዜ የሚፈጸም ሩካቤ በኦሪትም ይሁን በአዲስ
ኪዳን ክልክል ነው፡፡

#ከመጠመቅ:-

#ሐዋርያው_ቅዱስ_ጴጥሮስ “ይህም ውኃ ደግሞ ማለት ጥምቀት ምሳሌ ሆኖ
አሁን ያድነናል፤ የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አይደለም፡፡ ለእግዚአብሔር በጎ
ህሊና ልመና ነው እንጂ” 1ኛ ጴጥ 3÷21
በማለት ተናግሯል፡፡ ስለዚህ ጥምቀት
ሥጋዊ እድፍን ማስወገጃ ስላልሆነ፣ ከመጠመቅ በፊት ተጣጥበው እንጂ ከእድፍ
ጋር ለመጠመቅ መቅረብ ተገቢ አይደለም፡፡ የወር አበባም ከላይ
እንደተመለከተው ከሰውነት ሲወጣ እድፍ (ቆሻሻ) በመሆኑ፣ ከዚህ #የቤተክርስቲያን ስርዓት ውጪ እንዲሆን ተደርጓል፡፡

#ቤተመቅደስ_መግባት ፡-

ሴት በወር አበባዋ ጊዜ የምትከለከለው ነገር #ቤተመቅደስ መግባትን ነው፡፡ይህም
የሆነው በርኩሰት ምክንያት ወይም በኦሪት ሕግ ምክንያት ሳይሆን #በቤተመቅደስ_መፍሰስ ያለበት_ደም_አማናዊ_የሆነውየክርስቶስ_ደም_ብቻ_በመሆኑነው
ይህ ስርዓት #ለሴቶች #ብቻ ሳይሆን #ለወንዶችም ነው፡፡
#አንድ_ወንድ_እየነሰረው_ወይም_የሆነ_ነገር_አካሉን_ቆርጦት_ደም_እየፈሰሰው_ከሆነ_ወደ_ቤተ_መቅደስ_መግባት_የለበትም
ዝንየት (ህልመ ለሊት) ቢያጋጥመው ከ፩ቀን ከቤተ መቅደስ መራቅ
#ምክንያቱም በቤተ መቅደስ ከ #ክርስቶስ ደም ውጪ ሌላ ነገር መፍሰስ ስለሌለበት ነው፡፡

አስተውሉ
**በወር አበባ ላይ ሳለች ሴት #ወደ_ቤተመቅደስ_አትግባ_ማለትቤተ_ክርስቲያን_አትሂድ_ማለት_ሳይሆን_ወደ_ቤተክርስቲያን_ሄዳ_የመጀመሪያውን_ቅጽር ( #አጥር ) #ከገባች_በኋላ_በመጠለያ_ውስጥ_በመሆን_ትጸልይ_ትማር ወይም ማንኛውንም
አይነት መንፈሳዊ ስራዎችን ሰርታ ትመለስ ማለት ነው፡፡
#ከመቁረብ፡-
ሴቶች ከወር አበባ ሳይነጹ #ሥጋ_ወደሙ መቀበል አይችሉም፡፡ ይህንን ስርዓት ተላልፈው ወደ ሥጋ ወደሙ እንዲቀርቡ ያደረገ ዲያቆንም ይሁን ቄስ ከክህነቱ
እንዲሻር #ፍትሕ_ነገስት ይደነግጋል፡፡ “ከግዳጅዋ ያልነጻችውን ሴት በደሟ ወራት
#ከቤተ_ክርስቲያን_አግብቶ_ሥጋውን_ደሙን_ያቀበለ_ከክህነቱይሻር፡፡” ፍትነገ 6፣
ዘሌ 7፡19
#ይህ_ሥርዓት_በሴቶች_ላይ_ብቻ_ሳይሆን_ወንዶችም_ህልመ_ለሊት
በሚያጋጥማቸው ሰዓት እንዳይገቡ ይከለከላል፡፡


ቤተ ክርስቲያን የገነት ምሳሌ ናት፡፡ ሔዋን ከአዳም ጋር በገነት ለሰባት ዓመታት
ስትኖር የወር አበባ አታይም ነበር፡፡ ቤተ መቅደስ የገነት ምሳሌ መሆኗ የተሟላ
እንዲሆን የወር አበባ የምታይ ሴት ወደ ቤተ መቅደስ አትገባም፡፡

........የተወደደችው ሰዓት አሁን ነው ፤ የሐዳን ቀን አሁን ነው
1ኛ ቆሮ 6÷2

ይህን የእናት ቤተክርስቲያን ትምህርት ለሌሎቹም እህቶቻችን ሼር በማድረግ
እናካፍላቸው፡፡
@eotcy
@eotcy
@eotcy
531 views𝔟𝔢𝔫𝔬𝔫 𝙗𝙚𝙣𝙖, edited  17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 06:14:36
የተከበራቹ የቴሌግራም ቻናላችን ቤተሰቦቻችን ለ2 ዓመታት የኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች በሚል ቻናል የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አስተምሮ የሆኑትን ነገሮች እያቀረብንላቹ ቆይተናል፤ ነገር ግን በታቀደለት ልክ እያደገ አይደለም ፤ የኦርቶዶክስ አስተምሮቶች ለሁሉም ይስፋፋ ዘንድ ቻናላችንን ይጋብዙልን ።
ሀሳብ አስተያታችሁ ይጠቅመናልና https://t.me/eotcy_comment ላይ ይቀላቀላሉ

ቻናሉ https://t.me/eotcy
https://t.me/eotcy
https://t.me/eotcy

ሼር ሼር ሼር

ለወዳጆ ያጋሩልን ዘንድ በአምላከ ቅዱስን ስም እንጠይቃለን

.......እነሆ የተወደደችው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው
1ኛ ቆሮ6÷2
576 views𝔟𝔢𝔫𝔬𝔫 𝙗𝙚𝙣𝙖, edited  03:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ