Get Mystery Box with random crypto!

ዶይቸ ቬለን | DW AMHARIC NEWS🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ dwamharic_news — ዶይቸ ቬለን | DW AMHARIC NEWS🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ dwamharic_news — ዶይቸ ቬለን | DW AMHARIC NEWS🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @dwamharic_news
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 2.98K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል
DW AMHARIC NEWS IS A GLOBAL NEWS AND INFORMATION CHANNEL FROM A GERMAN INTERNATIONAL BROADCASTER DEUTSCHE WELLE (DW)
Contact @DWCOMMENTBOT

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2021-02-02 11:22:46
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸዉ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ቤት ግንባታ አስጀመሩ።

ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸዉ ለገጣፎ አካባቢ በሚገኘው ዲቦራ ፋዉንዴሽን ማእከል የአእምሮ ዉስንነት ላለባቸዉ ህጻናት እና ወጣቶች አገልግሎት የሚዉል ትምህርት ቤት ለመገንባት ዛሬ የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።

የቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት በአይምሮ ጤና እንክብካቤ እና ደህንነት ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ያስታወቀ ሲሆን ለዚህ ግንባታም 19 ሚሊዩን ብር መመደቡን ገልጿል።

የግንባታ ወጪው የተሸፈነውም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ ለትምህርት ቤቶች ግንባታ ከሰጡት የመደመር መጽሀፍ ሽያጭ ላይ መሆኑን ጽ/ቤቱ ጠቅሷል፡፡

@dwamharic_news
@dwamharicnewsbot
86 viewsedited  08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-02 10:33:07
"...የአገሪቱ ጦር የሕዝቡን ፍላጎት ቀልብሶ ስልጣን መቆጣጠሩ አግባብ አይደለም" - ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን

ትላንት የማይናማር ጦር መፈንቅለ መንግሥት ማድረጉን ተከትሎ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶ ባይደን በማይናማር ላይ ማዕቀብ ሊጥሉ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።

ፕሬዝደንት ባይደን ባወጡት መግለጫ የአገሪቱ ጦር የሕዝቡን ፍላጎት ቀልብሶ ስልጣን መቆጣጠሩ አግባብ አይደለም ብለዋል።

ባይደን፤ “በየትኛውም ስፍራ በዲሞክራሲ ላይ ጥቃት ሲደርስ አሜሪካ ወደጎን አትልም” ሲሉ ገልፀዋል።

በቀድሞዋ በርማ በዛሬዋ ስሟ ማይናማር የነበረውን አምባገነናዊ ወታደራዊ መንግሥት ተከትሎ በአሜሪካ ለረዥም ጊዜ ማዕቀብ ተጥሎ ቆይቶ ነበር።

አሜሪካ ከ10 ዓመታት በላይ በበርማ ላይ ጥላ የነበረውን ማዕቀብ ያነሳችው አገሪቱ ወደ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት መሸጋገሯን ተከትሎ መሆኑን ባይደን አስታውሰዋል። (BBC)

@dwamharic_news
@dwamharicnewsbot
154 viewsedited  07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-02 10:32:47
የማይስ ኢትዮጵያ ዘርፍ መለያ ዓርማ ይፋ ይደረጋል።

በጉባዔዎቾ፣ ስብሰባዎችና ዐውደ ርዕዮች ሁነቶችን ያካተተው የማይስ ኢትዮጵያ ዘርፍ መለያ ዓርማ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ ከፍተኛውን የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ ይፋ ይደረጋል።

ማይስ ኢትዮጵያ ጉባዔዎች፣ የጉዞ ማበረታቻዎች፣ ኮንፈረንስና የኢግዚቢሽንን ሁነቶችን ያካተተ የቱሪዝም ዘርፍ ሲሆን ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ተቋማት መገኛና ሁነቶችን አስተናጋጅ በመሆኗ ከዘርፉ ተጠቃሚ ለመሆን አቅዳለች።

በዚህም እንግዶችን ለመቀበልና ሁነቶች እንዲከናወኑ አጋር አካላትን በማስተባበር ዘርፉን የሚመራ በቱሪዝም ኢትዮጵያ ስር የኢትዮጵያ ኮንቬንሽን ቢሮ የተሸኘ ተቋም ተመስርቷል። ተቋሙም "በምድረ ቀደምት እንገናኝ" የሚል መሪ ቃል እንደሚኖረው ተገልጿል። (ENA)
@dwamharic_news
@dwamharicnewsbot
141 viewsedited  07:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-01 20:41:03
ብርጋዴር ጄነራል መኣሾ ሀጎስ ስዩም የተመድ የደቡብ ሱዳን ሰላም ማስከበር ተልእኮ አዛዥ ሆኑ !

በኢትዮጵያ አየር ኃይል ውስጥ ለ25 ዓመታት ያገለገሉት ብ/ጄነራል መአሾ ሀጎስ ስዩም የተመድ የደቡብ ሱዳን ሰላም ማስከበር ተልእኮ አዛዥ ሆነው መሰየማቸውን የተመድን መረጃ ዋቢ አድርጎ ኢብኮ ገልጿል።

ብርጋዴየር ጄነራል መኣሾ ሃጎስ በተመድ የላይቤሪያ እንዲሁም ዳርፉር ሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ ማገልገላቸው ታውቋል።

አዲሱን ሹመት ከጥር 04 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ እንደተሰጣቸው ተመድ ገልጿል።

@dwamharic_news
@dwamharicnewsbot
552 viewsedited  17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-01 20:25:21
#Ethiopia

የባለፉት 24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት :

• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ - 6_216
• በበሽታው የተያዙ - 734
• ህይወታቸው ያለፈ - 10
• ከበሽታው ያገገሙ - 106

አጠቃላይ 138,384 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ የ2,103 ሰዎች ህይወት አልፏል፤ 122,978 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው አገግመዋል።

230 ሰዎች በፅኑ ታመው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።

@dwamharic_news
@dwamharicnewsbot
538 viewsedited  17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-01 19:37:56
አዲስ አበባ ቅዳሜ እና እሁድ ያስተናገደችው የእሳት አደጋ ፦

#1

በጉለሌ እጸዋት ማእከል የደረሰው የእሳት አደጋ 2 ሄክታር ቦታ የሸፈነ ነው። በአደጋው ከ200 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሟል፤ ምን ያህል ንብረት ከውድመት እንደተረፈ ለጊዜው አልታወቀም።

#2

በጉለሌ ክፍል ከተማ ወረዳ አምስት ጽዮን ሆቴል አካባቢ በአንድ ሼድ ላይ በደረሰው የእሳት አዳጋ ከ50 ሺህ ብር በላይ የሚጠጋ ንብረት ለውድመት ሲዳረግ ከ4 ሚሊየን ብር በላይ የሚጠጋ ንብረት ደግሞ ማዳን ተችሏል፡፡

#3

በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ አንድ ኮሎምብያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በመኖርያ ቤት ላይ በደረሰ አደጋ 20 ሺህ ብር በሚገመት ንብረት ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን ከ300 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ንብረት ማዳን ተችሏል፡፡

#4

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ገርጂ ማርያም አካባቢ በአንድ ህንጻ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ 100 ሺህ ብር በሚጠጋ ንብረት ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን ከ100 ሚሊየን ብር በላይ ከውድመት ማዳን እንደተቻለ ተችሏል።

#5

በጉለሌ ክፍለ ከተማ እንጦጦ ማርያም አካባቢ ላይ በሚገኝ የእንጨት ክምር ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ ሶስት መቶ ሺህ የሚጠጋ ንብረት ሲወድም ወደ አንድ ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ማዳን ተችሏል።

#6

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 "እፎይታ የገበያ ማዕከል" ላይ በሚገኙ ሱቆች ላይ በደረሰው የእሳት አደጋ የጉዳት መጠን በማጣራት ላይ ይገኛል።

* ዛሬ ሰኞ ቦሌ ዘሀብ ሆቴል ፊት ለፊት እና ኡራኤል አካባቢ በመኖሪያ ቤቶች ላይ የእሳት አደጋ አጋጥሞ ነበር (የጉዳት መጠን አልታወቀም)

(የእሳትና የአዳጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን)
Compiled By: ETHIO FM 107.8

@dwamharic_news
@dwamharicnewsbot
543 viewsedited  16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-01 19:36:29
#AddisAbaba

"ዛሬም በሁለት ተጨማሪ አካባቢዎች እሳት ለማስነሳት የተደረገው ሙከራ ከሽፏል" - የአ/አ ከተማ አስተዳደር

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዛሬ በሁለት ተጨማሪ አካባቢዎች እሳት ለማስነሳት የተደረገው ሙከራ ከሽፏል ሲል ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ገለፀ።

በከተማው ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎች እየታዩ ያሉት የእሳት ቃጠሎዎች በከተማው ህዝብ እና አመራሮች፣ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ሰራተኞች፣ የፀጥታ አካላትና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የጋራ ርብርብ የከፋ ጉዳት ሳያደርሱ መቆጣጠር ተችሏል ብሏል አስተዳደሩ።

አስተዳደሩ ፥ "የጥፋት አላማቸው ያልተሳካላቸው አካላት ሆን ብለው ህብረተሰቡን ለማሸበር እያደረጉት ያለው ተግባር እንደማይሳካ እናሳውቃለን" ብሏል በመግለጫው።

ህብረተሰቡ ሳይደናገጥ ተገቢውን ጥንቃቄ እያደረገ፣ ሳይዘናጋ ነቅቶ አካባቢውን በመከታተል እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መረጃ በመለዋወጥ ያለምንም ስጋት መደበኛ እንቅስቃሴውን ማስቀጠል ይኖርበታልም ብሏል።

@dwamharic_news
@dwamharicnewsbot
530 viewsedited  16:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-01 16:13:30
ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን እንዲያሳውቅ ተጠየቀ።

ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን 'ቁርጥ' ያለ ቀን እንዲያሳውቅ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሳስቧል።

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ ፥ "ፈተናው የሚሰጥበትን ቀን ለማሳወቅ ለፈተናው የሚያስፈልጉት 400 ሺህ ታብሌቶች ወደ አገር ውስጥ አልገቡም" ብለዋል።

ለዚህም ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር እንደሚሰራና 'ታብሌቶቹ' ወደ አገር ሲገቡ ፈተናው የሚሰጥበት ቀን እንደሚወሰን ተናግረዋል።

የፈተና አሰጣጥ ሂደቱን ለማቀላጠፍ በ1 ሺህ 500 የፈተና ጣቢያዎች አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም እንዳስረዱ ኢዜአ ዘግቧል።

@dwamharic_news
@dwamharicnewsbot
636 viewsedited  13:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-01 16:02:42
በዚህ ዓመት በርካታ ተማሪዎች ወደ ትምህርት እንዳልተመለሱ ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና፣ የአርብቶ አደርና አካባቢ ጥበቃ ቋሚ ኮሚቴ የትምህርት ሚኒስቴርን የሁለተኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል።

ሚኒስቴሩ ለቋሚ ኮሚቴው ያቀረበው ሪፖርት እንደሚያሳየው በአፋር፣ በሶማሌ፣ በጋምቤላ፣ በቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ በኦሮሚያና ደቡብ ክልሎች አርብቶ አደር አካባቢዎች የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከላከያ ግብዓቶች ተሟልተው ትምህርት ተጀምሯል ብሏል።

በክልሎቹ ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች የተገነቡ ሲሆን የመምህራን እጥረት ችግርን ለማቃለልም በጎ ፈቃደኛ መምህራን እየተሳተፉ ነው።

ይሁን እንጂ በአካባቢዎቹ ከቅድመ መደበኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት በአማካይ 30 በመቶ ያህሉ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው አልተመለሱም ነው የተባለው።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወይዘሮ አልማዝ መሰለ እንደሚሉት፤ በሕዝብ ንቅናቄ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ማድረግ ያስፈልጋል።

ከዚህ ጎን ለጎን ከክልሎችና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር መጀመር እንዳለበት ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት በአፋጣኝ ተገልጾ የ9ኛ ክፍል ትምህርት መጀመር እንዳለበት አሳስበዋል።

በኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ከመግባቱ በፊት ትምህርት ሚኒስቴር 26 ሚሊዮን ያህል ተማሪዎችን ሲያስተምር ቢቆይም ዘንድሮ በርካታ ተማሪዎች ወደ ትምህርታቸው እንዳልተመለሱ ተገልጿል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

@dwamharic_news
@dwamharicnewsbot
603 viewsedited  13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-01 16:02:27
ምርጫ ቦርድ የፓርቲዎችን የምርጫ ምልክት ዛሬ ይፋ ያደርጋል !

የኢትዮጽያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የፓለቲካ ፓርቲዎችን የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

የቦርዱ ኮሙኒኬሽን አማካሪ ወይዘሪት ሶሊያና ሽመልስ እንደገለጹት፤ እስካሁን መስፈርቱን አሟልተው ጠቅላላ የተመዘግቡት 53 የፖለቲካ ፓርቲዎች ሲሆኑ ከእነዚህም መካከል እስእካሁን የደረሷቸውን 48 የምርጫ ምልክቶች ናቸው።

እነዚህን ምልክቶችም አስቀድሞ በተያዘው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ቦርዱ ዛሬ ይፋ ያደርጋል ማለታቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አስነብቧል።

@dwamharic_news
@dwamharicnewsbot
611 viewsedited  13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ