የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች:
2.98K
የሰርጥ መግለጫ
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል
DW AMHARIC NEWS IS A GLOBAL NEWS AND INFORMATION CHANNEL FROM A GERMAN INTERNATIONAL BROADCASTER DEUTSCHE WELLE (DW)
Contact @DWCOMMENTBOT
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
2
4 stars
0
3 stars
0
2 stars
0
1 stars
1
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5
2021-01-30 16:32:54
#update
የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ ህገወጥ የመሬት ወረራ ፣ ባለቤት አልባ ህንፃዎች፤ የኮንደሚኒየም ቤቶች፤ የቀበሌ መኖርያና ንግድ ቤቶችን አስመልክቶ በጥናት የተገኘው ግኝትቶች ላይ ዛሬ የውሳኔ ሃሳብ አሳልፏል።
በጥናቱ የተገኙ 322 ባለቤት አልባ ህንጻዎች በግልፅ ጨረታ ተሸጠው ወደ መንግስት ካዝና ገቢ እንዲሆኑ ወስኗል።
በጥናቱ የተገኘው ህገ-ወጥ መንገድ የተያዙ፤ ባዶ ሆነው የተገኙ 21,695 የኮንዶሚኒየም ቤቶችን በማስለቀቅ ለተጠቃሚዎች እንዲታደል ተወስኗል።
ይህ በዋናነት በ1997 ተመዝጋቢ የሆኑና በቋሚነት እየቆጠቡ ላሉ ነዋሪዎች በእጣ እንዲተላለፍ፤ የቀበሌ ቤቶችን አስመልክቶ በህገ-ወጦች የተያዙ የመኖርያ ቤቶች ግልፅ የሆነ መስፈርት ወቶላቸው ለደሆች፤ ለአቅመ ደካሞችና ለተለያየ ችግር ለተጋለጡ ነዋሪዎች እንዲሰጥ፤ የቀበሌ የንግድ ቤቶች በህገ-ወጥነት ከያዙት ሰዎች ተነጥቆ ለስራ አጥ ወጣቶች በእጣ እንሰጥ ሲሉ ወስነዋል፡፡
ምንጭ ፦ የአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪ ዕ/ቤት
@dwamharic_news
@dwamharicnewsbot
768 viewsedited 13:32
2021-01-30 16:32:53
742 views13:32
2021-01-30 14:57:29
ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ቡናን ቆልቶ ፈጭቶ የሚያሽግ ዘመናዊ ፋብሪካ ተመረቀ።
የኦሮሚያ የቡና አምራች ገበሬዎች ሕብረት ስራ ዩኒዬን በገላን ከተማ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባዉን ዋን ኮ ኮፊ 'ONE-KOO COFFEE' ቡናን ቆልቶ ፈጭቶ የሚያሽግ ዘመናዊ ፋብሪካ አስመርቋል።
ፋብሪካውን የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ መርቀው ከፍተዋል። በተመሣሣይ መልኩ ወደ 50 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ በቡሌ ሆራ ከተማ የተገነባዉ ዘመናዊ መጋዘንም ተመርቋል።
የዩኒዬኑ ምክትል ሥራ አስጂያጅ አቶ ደጀኔ ሂርጳ በ800ሺህ ብር ካፒታል የተቋቋመዉ ዩኒዬኑ ከ600 ሚሊዮን ብር ካፒታል ማፍራቱን ተናግረዋል።
የተመረቀዉ ዘመናዊ ፋብሪካም በኦሮሚያ ክልል የሚመረተዉን ቡና በዘመናዊ መንገድ ለሃገር ዉስጥና ለዉጪ ሃገር ገበያ ለማቅረብ ያስችላል ብለዋል።
@dwamharic_news
@dwamharicnewsbot
842 viewsedited 11:57