Get Mystery Box with random crypto!

ዶይቸ ቬለን | DW AMHARIC NEWS🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ dwamharic_news — ዶይቸ ቬለን | DW AMHARIC NEWS🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ dwamharic_news — ዶይቸ ቬለን | DW AMHARIC NEWS🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @dwamharic_news
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 2.98K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል
DW AMHARIC NEWS IS A GLOBAL NEWS AND INFORMATION CHANNEL FROM A GERMAN INTERNATIONAL BROADCASTER DEUTSCHE WELLE (DW)
Contact @DWCOMMENTBOT

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-23 20:41:01 የሐምሌ 16 ቀን 1014 ዓ/ም የዓለም ዜና በድምጽ
ርዕሶቹ
አዲስ አበባ ውስጥ የሽብር ጥቃት ሊፈጽሙ ነበር ያላቸውን ከ450 በላይ ሰዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የፌደራል የጸጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ። ግብረ ኃይሉ ዛሬ ባወጣው መግለጫ መሠረት ተጠርጣሪዎቹ አል ሸባብ እና አይ ኤስ እና በሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የአራት ታጣቂ ቡድኖች አባላት ናቸው።

በምስራቅ አፍሪቃ በዚህ ዓመት ከ50 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፍተኛ የምግብ ዋስትና እጦት ሊጋለጡ እንደሚችሉ የምስራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግስታት ወይም በእንግሊዘኛ ምህጻሩ ኢጋድ አስጠነቀቀ። ኢጋድ ትናንት አርብ ባወጣው መግለጫው በሶማሊያ እና ሱዳን ከ300 ሺ በላይ ሰዎች በከፋ የረሃብ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ ገልጿል።

በማሊ በዋነኛው የመንግስት ወታደራዊ የጦር ሰፈር ላይ ለደረሰው ጥቃት ከአልቃኢዳ ጋር ግንኙነት እንዳለው የሚነገርለት እስላማዊ ቡድን ኃላፊነት ወሰደ። ቡድኑ ጥቃቱን የማሊ የመንግስት ኃይሎች ከሩሲያ ቅጥረኞች ጋር በማበራቸው የተሰጠ ምላሽ ነው ብሏል።

ሩሲያ በጥቁር ባህር ዳርቻ የምትገኘውን የዩክሬኗን የወደብ ከተማ ኦዴሳን በሚሳኤል መታች። የዛሬው የሩሲያ የሚሳኤል ጥቃት የተሰማው ሞስኮ ከኪዬቭ ጋር በወደብ ከተማዋ በኩል እህል ወደ ውጭ እንዲላክ ከስምምነት ከደረሱ ከሰዓታት በኋላ ነው።

የዓለም ጤና ድርጅት በርካታ ሀገራትን እያዳረሰ የሚገኘውን የጦጣ ፈንጣጣ በሽታ «ዓለም አቀፍ ስጋት» ሆኗል ሲል አወጀ።
https://p.dw.com/p/4EYZE?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
@dwcommentbot
1.7K viewsedited  17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 15:58:49
የአሜሪካ የረድኤት ድርጅት ኃላፊ ሳማንታ ፓወር የአፍሪቃ ቀንድ ጉብኝታቸውን ጀመሩ።
የአሜሪካ የረድኤት ድርጅት በእንግሊዥኛው ምህፃሩ USAID ኃላፊ ሳማንታ ፓወር በአፍሪካ ቀንድ በጎርጎሮሳዊው ከዛሬ ሀምሌ 22 ቀን 2022 ጀምሮ ለሶስት ቀናት ለሚያደርጉት ጉብኝት ትናንት ኬንያ ገብተዋል።
ሀላፊዋ ድርቅ ያስከተለውን ጉዳት ለመገምገም ሶማሊያን እንዲሁም ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጉብኝቱ ድርጅቱ በሶማሊያ፣ በኬንያ እና በኢትዮጵያ በሚሊዮን በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ የደረሰውን የድርቅ አደጋ ለመከላከል ተጨማሪ 1.2 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ እንደሚሰጥ ከገለፀ ከቀናት በኋላ ነው።
ከፍተኛ የረሃብ ስጋት ባለባቸው ሀገራት የሚደርሰውን ረሃብ እና ሞት ለመታደግ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሀብት እንዲያሰባስብ ፓወር በጉብኝቱ ወቅት ያሳስባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ሳማንታ ፓወር በጉብኝታቸው ከሰብአዊ አጋሮች፣ ከሲቪል ማህበረሰብ እና ከከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ስለ ድርጅቱ ድጋፍ እና ሩሲያ በዩክሬን ላይ የምታደርገው ጦርነት በምግብ ዋስትና ላይ ስላስከተለው ተጽእኖ ይወያያሉ ተብሏል።
1.3K views12:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 15:58:49
በግብፅ፣ በሱዳን እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን ትብብር ማስፋት የታላቁ ህዳሴ ጉዳይን ለመፍታት ያስችላል ሲሉ የግብፁ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ተናገሩ።
አልሲሲ ይህንን የተናገሩት ትናንት በሰርቢያ የቤልግሬድ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ከተሰጣቸው በኋላ ባደረጉት ንግግር ነው።
በየሄዱበት ሀገር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጉዳይ በማንሳት የሚታወቁት አልሲሲ በሳምንትቱ መጀመሪያ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በምስራቅ አውሮፓዊቷ ሀገር ሰርቢያ ባደረጉት ጉብኝትም ጉዳዩን አንስተዋል።
ኤል ሲሲ በትናንቱ ንግግራቸው በግብፅ፣ በሱዳን እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን ትብብር ማስፋት የታላቁ ህዳሴ ጉዳይን ለመፍታት ያስችላል ብለዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በሶስቱ ሀገራት መካከል ሚዛናዊ እና ፍትሃዊ የህግ ስምምነት መኖሩ የኢትዮጵያን የልማት እና የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ከማሳደግ ጎን ለጎን የግብፅን እና የሱዳንን የውሃ መብት ለማስጠበቅ ያስችላል ብለዋል።
ግብፅ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ ላይ የግብፅና የኢትዮጵያን ግንኙነት ለማሳደግ ያላትን እምነት መሰረት በማድረግ ለዓመታት የድርድር መንገድን ስትከተል መቆየቷን ገልፀው፤የውሃ አካላትን የጋራ አጠቃቀም የሚቆጣጠሩ ሁለንተናዊ መርሆች መከበር እንዳለባቸው ተናግረዋል። ይህም እንደ ፕሬዚዳንቱ የሀገሮችን ፍላጎት በሚዛናዊ በሆነ መንገድ ያሳካል።
ህጋዊ ስምምነት በሌለበት ሁኔታ ኢትዮጵያ የግድቡን የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ሙሌት በማጠናቀቅ በያዝነው አመት መጀመሪያ የግድቡን ተርባይን የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨት መጀመሯ እና ሦስተኛውን ሙሌትም በመጭው ነሀሴ እና መስከረም ወር ለመጀመር ዕቅድ መያዟ እንዳሳሰባቸው መግለፃቸውን አልሃራም የተባለው የግብፅ ጋዜጣ ዘግቧል።
1.1K views12:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 12:31:19
በኤርትራ የታሰሩ ጋዜጠኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቁ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት አቤቱታ ቀረበ።
የጋዜጠኞች መብት የሚከራከረው ፤ የጋዜጠኞች ጥበቃ ኮሚቴ በእንግሊዥኛው ምህፃሩ CPJ እና ሌሎች ሰባት የመብት ድርጅቶች እና የህግ ባለሙያዎች በጎርጎሪያኑ ሀምሌ 21 ቀን 2022 በጋራ ባወጡት መግለጫ በኤርትራ የታሰሩ ጋዜጠኞችን በተመለከተ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት አቤቱታ አቅርበዋል።
በኤርትራ በእስር ላይ በሚገኘው በጋዜጠኛ ዳዊት ይስሃቅ እና በሌሎች 15 ጋዜጠኞች በተፈፀመው የዘፈቀደ እስር ላይ ተጠያቂነት እንዲሰፍንም አሳስበዋል።
የመብት ተከራካሪ ቡድኖቹ ዳዊት እና ሌሎች ጋዜጠኞች ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ እና ከቤተሰቦቻቸው ወይም ከጠበቆቻቸቸው ጋር ሳይገናኙ መቆየታቸውን ገልፀው፤ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ ጠይቀዋል። .ይህ ጉዳይ በዓለም ዙሪያ ለረጅም ጊዜ ከታሰሩ ጋዜጠኞች መካከል ያደርጋቸዋልም ብለዋል።
የተባበሩት መንግስታት የኤርትራ የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ልዩ ዘጋቢ መሀመድ አብደልሰላም ባቢከር በበኩላቸው የዳዊት ጉዳይ ከ2000ዎቹ መጀመሪያ ጀምሮ በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ፤ በመንግስት ላይ ባደረጉት ትችት ያለ ህጋዊ ሂደት በኤርትራ እስር ቤት ውስጥ ታስረው የሚማቅቁ በመቶዎች የሚቆጠሩ እስረኞችን ጉዳይ ይጨምራል ብለዋል።
የጋዜጠኞች መብት ኮሚቴ የአፍሪካ ፕሮግራም አስተባባሪ አንጄላ ኩንታል ደግሞ በዳዊትና በባልደረቦቹ ጉዳይ ድርጅታቸው «የትኛውንም የፍትህ መንገድ መከተልን ይቀጥላል» ብለዋል።
874 views09:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 09:30:36 https://p.dw.com/p/4ETDE
772 views06:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 09:30:10 \https://p.dw.com/p/4ETFN
738 views06:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 16:19:01 ፕላስቲክን ወደ ነዳጅ የቀየሩት ወጣቶች
በአሁኑ ወቅት የፕላስቲክ ቆሻሻ በዓለማችን ትልቅ ችግር ነው።.ፕላስቲክ በባህሪው ቶሎ የማይበሰብስ በመሆኑ የአፈር ለምነትን እና በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ህይወት ያላቸው ነገሮችን እየጎዳ ነው።ይህንን ችግር በመገንዘብ ከወደ ጅማ ስድስት ወጣቶች የፕላስቲክ ቆሻሻን ወደ ነዳጅ መቀየር የሚያስችል ማሽን ሰርተዋል። https://p.dw.com/p/4EQOp
?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwcommentbot
791 viewsedited  13:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 18:37:02
ካርቱም-በጎሳዎች ግጭት 105 ተገደሉ
በሱዳን ደቡባዊ ግዛት ብሉናይል፣ በመሬት ይገባኛል ውዝግብ የዛሬ ዘጠኝ ቀን በተነሳ የጎሳ ግጭት 105 ሰዎች መገደላቸውንና 291 መቁሰላቸውን የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ሱዳንን ከኢትዮጵያና ከደቡብ ሱዳን ጋር በሚያዋስነው በዚሁ ግዛት ግጭቱ የተካሄደው በርታና ሀውሳ በተባሉ ጎሳዎች መካከል ነው። ከካርቱም 460 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘው ከግዛቲቱ ዋና ከተማ አል ደማዚን የጤና ሚኒስትሩ በስልክ እንደተናገሩት በአካባቢው ጦር ሠራዊት ከተሰማራበት ካለፈው ቅዳሜ አንስቶ ግጭቱ ቀንሷል።የተመድ እንደሚለው በግጭቱ ምክንያት ከ17 ሺህ በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል። ከመካከላቸው 14 ሺዉ አል ደማዚን ውስጥ በሚገኙ ሦስት ትምሕርት ቤቶች ተጠልለዋል።የብሉ ናይሉ ግጭት የተቀሰቀሰው ሃውሳዎች የመሬት አጠቃቀምን በበላይነት የሚቆጣጠር የሲቪል አስተዳደር እንዲሆን ያቀረቡትን ጥያቄ በርታዎች ከተቃወሙ በኋላ ነው።አንድ የበርታ ከፍተኛ መሪ እንዳሉት ግን ግጭቱ የተነሳው ሃውሳዎች የመሬት ይዞታን ደንብ በመጣሳቸው ነው።
809 views15:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 17:31:36
የአዲስ አበባ ከንቲባ ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቶ ለሕግ እንዲቀርቡ ሲል ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ዛሬ ጠየቀ። "የኢትዮጵያ ሕዝብ በገዥው ፓርቲ የሚፈጸሙበት የሰብዓዊ መብት ረገጣዎች፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ቀውሶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፉ በመሄድ ላይ ይገኛሉ" ሲል በመግለጫው የተናገረው ፓርቲው "የከንቲባ አዳነች አበቤ አስተዳደር ከተማዋንም ሆነ አገሪቷን ወደ ቀውስ በፍጥነት እና በጥልቀት እየገፋት ይገኛል" ብሏል።

ፓርቲው ሰሞኑን የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለባለ እድለኞች ለመስጠት በወጣው የተጭበረበረ ዕጣ የከተማዋ ከንቲባ "በድርጊቱ መሪ ተዋናይ እንደነበሩ በርካታ መረጃዎች ተገኝቶባቸዋል" ብሏል በመግለጫው፡፡ "በዚህ አውድ፣ ከንቲባዋን ትቶ ሌሎች የአዲስ አበባ አስተዳዳር ባለሥልጣናት እና ሙያተኞች ላይ እርምጃ መወሰዱ የፍትሕ ሥርዓቱን ባዶነት እና አድሎኝነት አጋልጧል" የሚለው ባልደራስ « የከንቲባዋ ያለመከሰስ መብት ተነስቶ ለተነሱባቸው ጥያቄዎች የከንቲባዋ ያለመከሰስ መብት ተነስቶ ለሕግ እንዲቀርቡ፣ የኦሮሚያ ክልል ሕገ መንግሥት በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ እንዳይሆን እና የኦሮሚያ ክልል ባንዲራና መዝሙር በአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች እንዳይሰቀል እና እንዳይዘመር" ሲል ጠይቋል።
የከተማው ምክር ቤት አባል የሆኑት ዶክተር ሲሳይ መንግሥቴ ሰሞኑን በተከናወነው የምክር ቤቱ ጉባኤ ላይ "ትምህርት ቤቶች ላይ የኦሮሚያ ባንዲራ ይውለብለብ አይውለብለብ በሚል ችግር ፈጥሯል፣ መዝሙሩ ይዘመር አይዘመር በሥርዓት ነው መወሰን ያለበት" በሚል ላቀረቡት ጥያቄ ከንቲባ አዳነች አቤቤ "የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ለአዲስ አበባ በሚሆን መንገድ የአዲስ አበባ ተማሪዎች ኦሮሚኛን መማር የሚገባቸው በምን መልኩ ነው ለሚለው ካሪኩለም ቀርጿል። ኦሮምኛ መዘመራቸው ይቀጥላል ብለዋል።
704 views14:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 16:46:02
ዋሽንግተን የዩናይትድ ስቴትስና የአፍሪቃ መሪዎች ጉባኤ

ዩናይትድ ስቴትስ በመጪው ዓመት ከአፍሪቃ ሀገራት መሪዎች ጋር ጉባኤ ለማካሄድ ማቀዷን አስታወቀች።የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በታህሳስ ወር ሊካሄድ የታቀደው ይኽው ጉባኤ፣ዩናይትድ ስቴትስ አፍሪቃን ለመደገፍ ያላት ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ብለዋል። ታህሳስ አጋማሽ ላይ ዋሽግተን ዉስጥ ይካሄዳል የተባለው ጉባኤ ጉባኤ ከምግብ ዋስትና አንስቶ እስከ የአየር ንብረት ለውጥ ድረስ ባሉት ፈታኝ ችግሮች ላይ እንደሚወያይ ባይደን ጠቁመዋል። የዩናይትድ ስቴትስና የአፍሪቃ ግንኙነት አስፈላጊነት፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚጋሯቸው፣ ቅድሚያ በሚሰጧቸው ጉዳዮች ላይ ትብብርን ማጠናከርም ጉባኤው አጽንኦት ከሚሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ መሆኑን ፕሬዝደንቱ አስታውቀዋል።የአሜሪካን ምክትል ፕሬዝዳንት ካማላ ሃሪስ ማራኬሽ ሞሮኮ ውስጥ በተካሄደው በዩናይትድ ስቴትስ እና አፍሪቃ የንግድ ጉባኤ ላይ ባሰሙት ንግግር ጉባኤው እንደሚካሄድ አንስተው ነበር። ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የዋሽንግተን አስተዳደር ከፍተኛ ባለሥልጣን እንዳሉት በእቅዱ መሠረት 50 የአፍሪቃ ሀገራት መሪዎች በጉባኤው ላይ ይካፈላሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ባይደን የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ከሆኑ ወዲህ አፍሪቃ አልጎበኙም።የአሁኑ ባይደን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት የምዕራቡን ዴሞክራሲ በማስተዋወቅ በአፍሪቃ ብዙ መዋዕለ ንዋይ ከወረተችው ከቻይና ጋር ለመስተካከል የሚደረግ ጥረት ተደርጎ ተወስዷል። ሆኖም ባለሥልጣኑ እንዳሉት የጉባኤው ትኩረት ይሄ አይደለም። «አፍሪቃውያን አጋሮቻችንን ከእኛና ከቻይና እንዲመርጡ አንጠይቃቸውም ሆኖም ዩናይትድ ስቴትስ የተሻለ ሞዴል ታቀርባለች» ብለዋል።
655 views13:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ