2021-02-26 02:18:16
በምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሞ ወረዳ ነጭኖ ቀበሌ 10 አማራዎች በኦነግ ታጣቂዎችና በተባባሪዎቹ ዛሬ የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት እስከ 4 ሰዓት በስለት ተወግተው መገደላቸውን ነው ነዋሪዎች የገለፁት።
በነጭኖ ቀበሌ ደደቢ በተባለ ወንዝ አካባቢ በቆሎ እየወቁ ሳሉ ነው አማራዎች ከ30 በላይ በሚሆኑ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ተይዘው በስለት የታረዱት ይላሉ ነዋሪዎች።
አንድ ቦታ ላይ 6፣አጠገቡ 2፣ በመንገድ ላይ 2 በአጠቃላይ የ10 አማራዎችን አስከሬን ለማንሳት መቻሉን የደረሰን መረጃ አመልክቷል።
በግፍና በአሰቃቂ መልኩ በስለት ብቻ አንገታቸው ላይ ተወግተው የተገደሉትም ዕድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆኑ እነሱም ታደሰ ሙሉነህ፣ውብሸት፣እንዳላማው፣ቄስ አንተነህ፣ክንዴነህ፣ካሳሁን፣ተመስገን፣መልካሙ፣ሲሳይእና አንድ ስሙ ያልታወቀ የ7 ዓመት ህጻን መሆናቸው በነዋሪዎች ተረጋግጧል።
ከመካከላቸው ለወሬ ነጋሪ አንድ መልካሙ ተሾመ የተባለ የ24 ዓመት ወጣት ልጅ ሮጦ በማምለጥ የተረፈ ቢሆንም በሁኔታው በከፍተኛ መረበሽ ውስጥ በመግባቱ ለጊዜው በቂ መረጃ ሊሰጠን አልቻለም።
አሰቃቂ ግድያው ከተፈፀመ በኋላ ከ30 ያላነሱ የኦሮሚያ ልዩ ኃይልና የፖሊስ አባላት ቢመጡም አስከሬን ሳያነሱ "ደክሞናልና እርቦናል" በሚል ጥለውን ወደመጡበት ተመልሰዋል ብለዋል።
16 የመኖሪያ ቤቶች፣ የእህል ጎተራና ክምር ስለመቃጠላቸው ምንጮች ገልፀዋል።
Laink
@coronaethiopiaa @coronaethiopiaa
8.8K views23:18