Get Mystery Box with random crypto!

Ethio 19

የቴሌግራም ቻናል አርማ coronaethiopiaa — Ethio 19 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ coronaethiopiaa — Ethio 19
የሰርጥ አድራሻ: @coronaethiopiaa
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 1
የሰርጥ መግለጫ

Y

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2021-03-04 18:12:02
ትግራይ፡ የኤርትራ ወታደሮች እንዲወጡ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አቋም መያዙ ተገለጸ

የኤርትራ ሠራዊት ከትግራይ ክልል እንዲወጣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አንድ አይነት አቋም መያዙን የአስተዳደሩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ለቢቢሲ ተናገሩ።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የጽፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረ መስቀል ካሳ እንዳሉት የኤርትራ ሠራዊት በክልላቸው ውስጥ እንዳለ ከመግለጻቸው በተጫማሪ "በክልሉ ውስጥ ያሉ አካባቢዎችን ተቆጣጥረዋል። ወንጀሎችንም ፈጽመዋል" ሲሉ ከስሰዋል።
የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት በትግራይ ክልል የተከሰተውን ወታደራዊ ግጭት ተከትሎ የኤርትራ ሠራዊት በክልሉ ውስጥ እንደሚገኝ ቢገልጹም የኢትዮጵያም ሆነ የኤርትራ መንግሥታት ጉዳዩን ሲያስተባብሉ መቆየታቸው ይታወሳል።

የኤርትራ ወታደሮች ትግራይ ውስጥ መኖራቸውን በተመለከተ "ሕዝቡ በዓይኑ ያየው እውነታ ነው" ያሉት አቶ ገብረ መስቀል፤ "ስለዚህም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ወታደሮቹ ከክልሉ መውጣት አለባቸው ሲል አቋም ይዟል" በማለት በአንድ ድምጽ መወሰናቸውን ተናግረዋል።

Link
@coronaethiopiaa @coronaethiopiaa
296 viewsedited  15:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-03 16:56:02
ኢትዮጵያ ዜጎቿን ከሳዐዲ አረቢያ ማስወጣቷን ቀጥላለች።

ኢትዮጵያ ሳዐዲ አረቢያ በችግር ላይ የሚገኙ ዜጎቿን በተከታታይ በማስወጣት ላይ መሆኗ ይታወቃል።

ዛሬ የካቲት 24/2013 ዓ.ም 338 ኢትዮጵያዊያን ከሳኡዲ አረብያ ሪያድ ከተማ ወደ አገራቸው ተመልሰዋል።

ኢትዮጵያ ዜጎቿን ከሳዐዲ አረቢያ ማስወጣቷን ቀጥላለች።

ኢትዮጵያ ሳዐዲ አረቢያ በችግር ላይ የሚገኙ ዜጎቿን በተከታታይ በማስወጣት ላይ መሆኗ ይታወቃል።

ዛሬ የካቲት 24/2013 ዓ.ም 338 ኢትዮጵያዊያን ከሳኡዲ አረብያ ሪያድ ከተማ ወደ አገራቸው ተመልሰዋል።

Link
@coronaethiopiaa @coronaethiopiaa
472 viewsedited  13:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-03 02:59:28
የሚያሳዝነው ምስኪኑ የትግራይ ሕዝብ ነው...
71 views23:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 21:02:45
መልካም የአደዋ በአል።
903 views18:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 20:32:23
Pm. D.r Abiy Ahmed Ali.

ጉዟችን ኢትዮጵያን ወደ ቀጣዩ ከፍታ ማሻገር ነው። የዐድዋን ሪከርድ መስበር ነው። እንደምንችል አረጋግጠናል፤ እንደምንችል ማሳየት ግን ይቀረናል። ሰንኮፎቻችን ሁሉ ቀስ በቀስ እየተነቀሉና መንሳፈፊያ ክንፎቻችን እየተዘረጉ ሲመጡ ያለ ጥርጥር ዘመናችን ብሩኅ ይሆናል፤ ጉዞውን ጀምረናል። ወደ ዐድዋ መድረሻው መንገድ ፈታኝ ነበር፤ የዐድዋ ድል ግን ጣፋጭ ነው። ወደ ብልጽግና መድረሻ መንገዳችን ፈታኝ ይሆን ይሆናል። ብልጽግናችን ግን እንደ ዐድዋ ሁሉ አይቀሬ ድል ነው። ኢትዮጵያ ከዐድዋ በታች አትወርድም። ከዐድዋ በላይ ወዳለው ከፍታ ደግሞ አንድ ሆነን እኛ እናወጣታለን።

መልካም የድል በዓል ለሁላችንም ይሁን።

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትሩር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
የካቲት 22፣ 2013 ዓ.ም

Link
@coronaethiopiaa @coronaethiopiaa
803 viewsedited  17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 16:31:14

ልበለው እሰኪ እንተ ፍረዱ??
135 views13:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 15:48:15
እነ አቶጃዋር መሃመድ ላንድ ማርክ ሆስፒታል ተወሰዱ !

እነ አቶ ጃዋር መሃመድ ፣ አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ አቶ ሃምዛ ቦረና ዛሬ ጥዋት ላንድ ማርክ ሆስፒታል መወሰዳቸውን የኦሮሞ የፖለቲካ እስረኞች ጠበቆች ቡድን አሳውቋል።

ትላንት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በአቶ ጃዋር ፣ አቶ በቀለ ፣ በአቶ ሀምዛ እና አቶ ደጀኔ የህክምና ጉዳይ ላይ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የሰጠውን ውሳኔ በመሻር ቀደም ሲል የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ባዘዘው መሰረት ወደ ላንድማርክ ሆስፒታል እንዲወስዱ ትዕዛዝ መስጠቱን ይታወሳል።

በረሃብ አድማ ከ30 ቀናት በላይ የሆናቸው እነ አቶ ጃዋር መሃመድ ዛሬ ጥዋት በገቡበት በላንድ ማርክ ሆስፒታል አከባቢ ከፍተኛ የሆነ የጸጥታ ሀይል እነደተሰማራ ተዘግቧል።

PHOTO : Addis Standard

Join our channel
@coronaethiopiaa @coronaethiopiaa
379 views12:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-01 22:23:57

ጌቾን እንዴት አያችሁት ?
740 views19:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-01 21:49:14
ጋዜጠኛ ግርማይ ገብሩ በቁጥጥር ስር ዋለ።

የቢቢሲ የትግርኛ ቋንቋ አገልግሎት ጋዜጠኛው ግርማይ ገብሩ ዛሬ በመቐለ ከተማ በወታደሮች ቁጥጥር ስር መዋሉን ቢቢሲ አሳወቀ።

የዓይን እማኞች ጋዜጠኛ ግርማይ ገብሩን ወታደሮች ከነበረበት ካፌ ይዘውት ሲሄዱ መመልከታቸውን ተናግረዋል።

ጋዜጠኛው በምን ምክንያት በቁጥጥር ስር እንደዋለ እስካሁን የማውቀው ነገር የለም ብሏል ቢቢሲ።

ነገር ግን ጋዜጠኛ ግርማይ እዛው መቐለ ከተማ ውስጥ ወደሚገኝ ወታደራዊ ካምፕ መወሰዱን ሪፖርት እንደደረሰው ቢቢሲ ገልጿል።

* ከጋዜጠኛ ግርማይ ገብሩ በተጨማሪ ሌሎች 4 ሰዎች አብረውት ወታደራዊ ልብስ በለበሱ ወታደሮች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

Link
@coronaethiopiaa @coronaethiopiaa
855 views18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-01 17:04:05
ከ3 ሳምንታት በኃላ እነአቶ ጃዋር መሃመድ በአካል ፍርድ ቤት ቀረቡ :

በረሃብ አድማ ላይ እንደሚገኙ የሚነገረው እነ አቶ ጃዋር መሐመድ ዛሬ ረፋድ ላይ ፍርድ ቤት ለነበራቸው ቀጠሮ ሲቀርቡ አካላቸው ደክሞ እና ከስተው መታየታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ አቶ ጃዋር የክስ መዝገብ የተከሰሱ የ24 ሰዎችን የእምነት ክህደት ቃል ለመቀበል ዛሬ ጠዋት ላይ ቀጠሮ ይዞ ነበር። ከእነዚህ መካከል እነ አቶ ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባን ጨምሮ 22 ሰዎች በፍርድ ቤት ተገኝተው ነበር።

ጠበቆች ደንበኞቻቸው እነ አቶ ጃዋር መሐመድ፣ በቀለ ገርባ፣ ሐምዛ አዳነ እና ደጀኔ ጣፋ የረሃብ አድማ ከጀመሩ 33 ቀናት እንዳለፋቸው ለፍርድ ቤት ተናግረው፤ ደንበኞቻቸው አሁን ባሉበት ሁኔታ የእምነት ክህደት ቃላቸውን መስጠት አይችሉም በማለት ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ዐቃቤ ሕግ ተለዋጭ ቀጠሮ ቢሰጥ እንደማይቃወም ለፍርድ ቤቱ ተናግሯል።

በዚህም መሠረት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የፀረ ሽብር እና ሕገ-መንግሥታዊ ጉዳዮች አንደኛ ችሎት የተከሳሾችን የእምነት ክህደት ቃል ለመቀበል ለመጋቢት 6/2013 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

https://telegra.ph/BBC-NEWS-03-01

Link
@coronaethiopiaa @coronaethiopiaa
480 viewsedited  14:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ