Get Mystery Box with random crypto!

Ethio 19

የቴሌግራም ቻናል አርማ coronaethiopiaa — Ethio 19 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ coronaethiopiaa — Ethio 19
የሰርጥ አድራሻ: @coronaethiopiaa
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 1
የሰርጥ መግለጫ

Y

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2021-02-10 19:28:18
14.6K views16:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-10 15:36:18
ጉዳፍ ፀጋይ ፈረንሳይ ሌቪን በተካሄደው የ1500 ሜትር የቤት ውስጥ ሩጫ የዓለም ክብረ ወሰንን በማሻሻል አሸነፈች።


በማሻሻል አሸነፈች።
ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ የዓለም ክብረ ወሰን በ2 ሴኮንድ በማሻሻል 3፡53፡09 በሆነ ሰዓት ውድድሩን አጠናቃለች።ጉዳፍ ያሻሻለችው ክብረ ወሰን በሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት ገንዘቤ ዲባባ በ2014 (እአአ) ካርልስሩሄ ላይ የተያዘ ነበር።


"የዓለምን የቤት ውስጥ ሩጫ ክብረ ወሰን በማሻሻሌ እጅግ ደስተኛ ነኝ" ያለችው አሸናፊዋ ጉዳፍ፤ "ጠንከራ ልምምድ ሰርቼ ስለነበር የዓለምን ክብረ ወሰን ለመስበር ራሴን አዘጋጅቼ ነበር" ብላለች።

ትናንት ምሽት በወንዶች በተደረገ የ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ሩጫም ኢትዮጵያውያን ተወዳዳሪዎቻቸውን በፍጹም የበላይነት አሸንፈዋል። ኢትዮጵያውያኑ ከአንድ እስከ አራት ያለውን ደረጃ ይዘው ሲያጠናቅቁ የዓለም ሁለኛው ፈጣን ሰዓትም በውድድሩ ተመዝግቧል።


CONGRATULATIONS SHARE SHARE SHARE
14.9K viewsedited  12:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-10 01:04:36
ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ውስጥ እስከ 9 ሚሊዮን የኮቪድ-19 ክትባት ለማስገባት እየሰራች መሆኑን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ተናገሩ።

የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ይህንን ያሉት ዛሬ፣ ማክሰኞ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።
ለክትባቱ በዋናነት ቅድሚያ የሚሰጣቸው ዜጎች ተጋላጭ ይሆናሉ ተብለው የተለዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ናቸው ብለዋል።

በዚህ መሰረት የጤና ባለሙያዎች፣ የማህበራዊ ጤና ሰራተኞች፣ የህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ አካላት ቅድሚያ ይሰጣቸዋል ያሉ ሲሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተቋቋመው ግብረ ሀይልም የተሳለጠ የክትባት አሰጣጥና ቁጥጥር እንዲኖር ያደርጋል ብለዋል ዶ/ር ሊያ።

ሚኒስትሯ አክለውም ኢትዮጵያና መሰል ሀገራት ከኮቫክስ የክትባት ትብብር ተቋም ጋር በመሆን እስከ ፈረንጆቹ 2021 መጨረሻ 20 በመቶ የሚሆነውን ህዝባቸውን ለመከተብ እየሰሩ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ክትባቱን ወደ ሃገር ውስጥ የምታስገባው ‹‹ኮቫክስ›› በተሰኘው ዓለም አቀፍ የክትባት ሸማች ማህበር በኩል ነው።
15.0K views22:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 22:25:48
ዛሬ ታዋቂ ፖለቲከኞች እና የሃይማኖት አባቶች ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተገኝተው ተከሳሾች የረሃብ አድማቸውን እንዲያቆሙ ቢጠይቋቸውም ፈቃደኛ ሳይሆኑ መቅረታቸውን አቶ ከድር ለቢቢሲ ተናግረዋል።

"ከፖለቲከኞች የኦነግ ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ፣ አቶ ሌንጮ ለታ፣ አቶ ባቴ ኡርጌሳ፣ ከሃይማኖት አባቶች ደግሞ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ቃሊቲ ተገኝተው ቢለምኗቸውም ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል"
ሌላኛው የእነ አቶ ጃዋር ጠበቃ አቶ ሙስጋኑ ሙለታ፤ ፖለቲከኞቹ እና የሃይማኖት አባቶች የረሃብ አድማውን እንዲያቆሙ ሲጠይቁ በስፍራው እንደነበሩ ይናገራሉ።

"እነ አቶ ጃዋር በጣም ተዳክመዋል። ብዙ መናገር እና መራመድ አይችሉም። ሰውነታቸው ዝሏል። ሃኪሞችም ብዙ አታውሩ ብለዋቸዋል" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።


"ለሽምግልና የሄዱት ሰዎች 'ምግብ ብሉ። በራሳችሁ ላይ ጉዳት አታደርሱ' ሲሉ ነበር የጠየቋቸው። ይሁን እንጂ ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል" ሲሉ አቶ ምስጋኑ ተናግረዋል።
አቶ ከድር ቡሎ በበኩላቸው የረሃብ አድማ እያደረጉ ካሉ ተከሳሾች መካከል የሕክምና እርዳታ አስፈልጓቸው ወደ ጤና ተቋም እየተወሰዱ ያሉ ተከሳሾች መኖራቸውን ተናግረዋል።

ባሳለፍነው እሁድ የእነ አቶ ጃዋር መሐመድ ሃኪሞች "ምርመራ ካደረጉላቸው በኋላ ውሃ ካልወሰዱ አንዳንድ የሰውነት አካላቸው ሥራ ሊያቆም እንደሚችል ከነገሯቸው በኋላ ነው በግድ ውሃ እየወሰዱ ነው ያሉት። ምግብ የሚባል ነገር አፋቸው ጋር እየደረሰ አይደለም" ሲሉ ከእነ አቶ ጃዋር ጠበቆች መካከል አንዱ የሆኑት ምስጋኑ ሙለታ ለቢቢሲ ተናግረው ነበር።
12.8K viewsedited  19:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 21:49:51 የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ፦

ዛሬ የካቲት 2/2013 ዓ.ም ከቀኑ 6፡20 ጀምሮ 'ሰበር ዜና Breaking News' በሚል በማረሚያ ቤት በሚገኙት በአቶ ጃዋር መሃመድ እና በሌሎችም ግለሰቦች ዙሪያ የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ደብዳቤ እንደጻፈ ተደርጎ በተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ገጾች እየተናፈሰ ያለው ጉዳይ ፍጹም ስህተት እና ከእውነት የራቀ መሆኑን የፌዴራል ማረሚያ ቤት ባወጣው አጭር መግለጫ አሳውቋል።

በደብዳቤው የተካተቱ ቁጥር ፣ ቀን ፣ ሎጎ እንዲሁም ማህተም በፎቶ ሾፕ የተቀነባበሩ እንጂ ከፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን መዝገብ ቤት የወጣ ደብዳቤ እንዳልሆነ ማረሚያ ቤቱ ያረጋግጣል ብሏል።
12.1K views18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 21:49:02
በሀገሪቱ የመጀመሪያ መሆኑ የተገለፀው ዘመናዊ የእናቶችና ህፃናት ሆስፒታል መጠናቀቁ ተገለፀ !

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተገነባው በሀገራችን የመጀመሪያው ትልቁና ዘመናዊ የእናቶችና ህፃናት ሆስፒታል መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዛሬ ምሽት ገልጿል።

ሆስፒታሉ ፦

- በ20,000 ካሬ ላይ ያረፈ፣
- 400 በላይ ተኝቶ መታከሚያ አልጋዎች ያሉት፣
- 100 የልህቀት ማዕከል አገልግሎት መስጫ ክፍሎች ያሉት፥
- በተመሳሳይ ሰአት ለ7 እናቶች የኦፕራሲዮን አገልግሎት መስጠት የሚያስችለው ዘመናዊና ወረቀት አልባ መስተንግዶ የሚሰጥ ዘመናዊ የህክምና ቁሳቁሶች የተሟሉለት ነው ተብሏል።

የእናቶች እና ህጻናት ሆስፒታሉ የካቲት 4 ቀን 2013 ዓ/ም በምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ተመርቆ ስራ ይጀምራል ተብሏል።

ግንባታው ቀድሞ ለ "መለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ" ተብሎ የተጀመረ ሲሆን የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ በከተማው ትልቅ የአገልግሎት ችግር ያለበት የእናቶችና ህጻናት ጤና ቅድሚያ በመስጠት 700 ሚሊየን ብር በመመደብ ተጨማሪ ግንባታ በማድረግ እና ነባሩን ግንባታ በማሻሻል ወደ ሆስፒታልነት እንዲቀየር ማድረጉን የከተማ አስተዳደሩ ፕሬስ ሴክሬተሪያት አሳውቋል።
12.0K views18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 20:49:08
0919870785

ያሻዎትን ፈልገው የማያጡበት Čalzado Ĉollections አዳዲስ ፣ ጥራት እና አስተማማኝ ዋስትና ያላቸውን ስልኮች ፣ የተለያዩ ኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎች ፣ laptops ፣ እንገዛለን እንሸጣለን አቅርቦታችንን ለማየት join our channel ለበለጠ መረጃ ይደዉሉ።

ኦርጅናል እና አዳዲስ ጫማዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ ከበቂ አቅርቦትጋ በሱቃችን ያገኛሉ።


ቢትኮይን(BITCOIN)
መሸጥም ሆነ መግዛት የምትፈልጉ አሁኑኑ በ 0919870785 ይደዉሉልን። ብዛት ለሚገዙ በተመጣጣኝ ዋጋና በታማኝነት እናቀርባለን።


አድራሻ : ቦሌ ሚሊንየም አዳራሽ ፊትለፊት እንዲሁም ቦሌ ኦሮሚያ ህንፃ። አሁኑኑ ይደውሉልን!

0919870785 @Raeye

ቤተሰብ ይሁኑ

https://t.me/joinchat/AAAAAEMAkUfIXbwkbFPC3w
12.2K views17:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-09 15:32:50
አዲሱ የCOVID-19 ዝርያ ያለው
ቫይረስ እየተስፋፋ ነው!!! SHARE

እንግሊዝን እያስጨነቃት ያለው አዲሱ የኮሮናቫይረስ ዝርያ በአሜሪካም በፍጥነት እየተስፋፋ እንደሆነ አንድ ጥናት ይፋ አድርጓል።
በከፍተኛ መጠን የመተላለፍ ባህርይ አለው የተባለው ይህ ዝርያ በአሜሪካ በባለፉት ቀናት በእጥፍ እየተስፋፋ መሆኑን ይኼው ጥናት አስታውቋል።

የዝርያው የመስፋፋት ፍጥነት ቢ1117 የሚል መጠሪያ የተሰጠው ሲሆን በአለም አቀፉ የክትባት ሂደቶችም ላይ ከፍተኛ ጫና አሳርፏል ተብሏል።


የአሜሪካው የበሽታዎች ቁጥጥርና ክትትል (ሲዲሲ) የዩኬው የኮሮናቫይረስ ዝርያ በመጋቢት ወር ዋነኛው ኮሮና ይሆናል በማለት ተንብይዋል።
ጥናቱ የተለያዩ ተመራማሪዎችና ሳይንቲስቶች የተጣመሩበት ሲሆን ሜድርክሲቭ በተባለ ድረገፅም ላይ ወጥቷል።


የአዲሱ ዝርያ ከተመዘገበባቸው ግዛቶች መካከል ፍሎሪዳ የምትመራ ሲሆን ካሊፎርኒያ ትከተላለች።


"ጥናታችን እንደሚያሳየው ሌሎች አገሮች ላይ ቢ117 በከፍተኛ ሁኔታ ተስፋፍቶ ዋነኛው የኮቪድ-1ዝርያ መሆን እንደቻለው እኛም ወደዛ እየገሰገስን ነው። የኮሮናቫይረስን አስከፊነትና ገዳይነት ለመቀነስ አስቸኳይና ወሳኝ እርምጃዎች እንደሚያስፈልጉም ማሳያ ነው" ብለዋል የሪፖርቱ ፀሃፊዎች።


በሪፖርቱ መሰረት አዲሱ የቫይረስ ዝርያ ከቀድሞው በበለጠ 35-45 በመቶ ብልጫ ፍጥነት ይተላለፋል።
ሲዲሲ አዲሱ የቫይረስ ዝርያ መኖሩን ባሳወቀበት ባለፈው ወር ከሚመዘገቡት ህሙማን ቁጥር በአዲሱ ዝርያ የተያዙት 0.5 ያነሰ ቢሆን በቅርቡ ግን ከ3.6 በመቶ በላይ በፍጥነት እየገሰገሰ እንደሆነ ጥናቱ አመላክቷል፥

በአሜሪካ በየቀኑ የሚመዘገበው የህሙማን ቁጥር ከባለፈው ወር ጀምሮ መቀነስ ቢያሳይም የሟቾች አማካይ ቁጥር አሁንም እንዳሻቀበ ነው።


Share Share Share Share
14.0K viewsedited  12:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-01 20:51:03 የዛሬ ሰኞ ጥር 24/2013 ዓ.ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች

1፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ትግራይ ክልልን ለሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ክፍት እንዲያደርግ የሚጠይቅ ዘመቻ እንደጀመረ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ረድዔት ድርጅቶች ዕርዳታ ለማጓጓዝ ያቀረቧቸው በርካታ ጥያቄዎች ፍቃድ እንዳላገኙ የገለጠው ድርጅቱ፣ የረድዔት ሠራተኞችም ለመግባት ፍቃድ እንዳላገኙ አውስቷል፡፡ በክልሉ የሰላማዊ ሰዎች ጭፍጨፋ፣ የዘፈቀደ የከባድ መሳሪያ ድብደባ፣ ከፍርድ ውጭ ግድያ እና ዝርፊያ ስለመበራከቱ በቂ ማስረጃ አለ- ብሏል አምነስቲ፡፡

2፤ በኢትዮጵያው ትግራይ ክልል እስካሁን ትርጉም ያለው ዕርዳታ ለተረጅዎች እንዳልደረሰ የኖርዌይ ስደተኞች ካውንስል ዋና ጸሃፊ ጃን ኢግላንድ ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ትግራይ እንዲሁም 2 የኤርትራዊያን ስደተኛ መጠለያዎች ለረድዔት ድርጅቶች እስካሁን ተደራሽ አልሆኑም፡፡ ተደራሽ የሆኑት መቀሌ እና ለአውራ ጎዳናዎች ቅርብ የሆኑ ተረጅዎች ብቻ ናቸው፡፡ ለረድዔት ድርጅቶች ፍቃድ አሰጣጡ ወጥነት የሌለው እና የተንዛዛ እንደሆነ የጠቀሱት ዋና ጸሃፊው፣ እንዲህ ያለ የተጓተተ አሠራር አይቼ አላውቅም ብለዋል፡፡ መንግሥት ሁኔታዎችን ማስተካከል ቢፈልግ ባንድ ቀን ማስተካከል ይችላል በማለትም አክለዋል፡፡ ረድዔት ድርጅቶች የችግሩን ክብደት አጉልተው አለማሳየታቸውም ውድቀት እንደሆነ አውስተዋል፡፡

3፤ በፊንላንድ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር የተመራ የአውሮፓ ኅብረት የሰብዓዊ ሁኔታ አጣሪ ቡድን ወደ ኢትዮጵያው ትግራይ ክልል እንደሚጓዝ ዩሮ ኦብዘርቨር ድረገጽ ተሰምቷል፡፡ የኅብረቱ ልዑክ በቀጣዮቹ ጥቂት ሳምንታት ወደ ሥፍራው ይጓዛል ተብሏል፡፡ በክልሉ ግጭት 3 የውጭ መንግሥታት ተሳትፈዋል ያሉት ውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ፣ ዐለማቀፉ ኅብረተሰብ በክልሉ የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን እንዲያጣራ ጠይቀዋል፡፡

4፤ በአማራ ክልል ከሌሎች ክልሎች የተፈናቀሉ 270 ሺህ ተፈናቃዮች እንደሚገኙ ተገለፀ። ተፈናቃዮቹ በተለያዩ ማንነትን መሠረት ባዳረጉ ጥቃቶች እና ግጭቶች ምክንያት ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ደቡብ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የተፈናቀሉ ናቸው፡፡ አብዛኞቹ ተፈናቃዮች የተጠለሉት፣ በምዕራብ ጎጃም፣ ሰሜን ሸዋ፣ ሰሜን ወሎ እና ራያ ቆቦ ነው፡፡

5፤ ደቡብ ሱዳን ከዐለም ሀገራት በሙስና ከመጨረሻው ሁለተኛውን ደረጃ እንደያዘች የሀገራትን የሙስና ደረጃ የሚያወጣው ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ባወጣው አዲስ ሪፖርት አስታውቋል፡፡ ሱማሊያ ደሞ ሦስተኛ ደረጃ ይዛለች፡፡ ደረጃው የወጣው ከ180 ሀገራት ሲሆን፣ መለኪያው በመንግሥት ተቋማት የሚፈጸም ሙስና ነው፡፡

6፤ አልሸባብ በሞቃዲሾ ባለሥልጣናት እና ፖለቲከኞች በሚያዘወትሩት አንድ ትልቅ ሆቴል ላይ በፈጸመው ጥቃት 15 ሰዎች እንደተገደሉ የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል፡፡ በአሸባሪዎቹ ጥቃት ከተገደሉት መካከል የቀድሞ መከላከያ ሚንስትር የነበሩ አንድ ጀኔራል ይገኙበታል፡፡ አሸባሪዎቹ ሆቴሉን ሰብረው የገቡት ትናንት ሌሊት ሲሆን፣ ዛሬ ከ7 ሰዓታት ተኩስ ልውውጥ በኋላ የመንግሥት ወታደሮች ሆቴሉን ተቆጣጥረዋል፡፡ ጥቃቱን ያደረሱት 4ቱ ታጣቂዎች ተገድለዋል ተብሏል፡፡
5.7K views17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-01 20:32:59
ነገ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ሰላማዊ ሰልፍ ይካሄዳሉ

በነገው እለት በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች የዶክተር ዐቢይ መንግስትን የሚደግፍ እና ኦነግ ሼነን የሚቃወሙ ሰልፎች እንደሚካሄዱ ተገለጸ፡፡

ሰልፉ አሁን በመንግስት እየተካሄዱ የሚገኙ የልማት ስራዎችን እና አጠቃላይ የለውጥ እርምጃዎችን የሚደግፉ የድጋፍ እንዲሁም ፀረ ሰላም ቡድኖችን የሚያወግዝ የተቃውሞ ሰልፍ እንደሆነ ታውቋል፡፡

ሰልፉ ከሚካሄድባቸው አካባቢዎች የአሰላ ከተማ አንዱ ሲሆን፣ በሰልፉ ላይ በዞኑ ከሚገኙ 28 ወረዳዎች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ ይሆናል ተብሎም ይጠበቃል።

የድጋፍ ሰልፉ ከህዝብ የመጣ ጥያቄ እንደሆነ የተነገረለት ሲሆን፣ ከ100 ሺህ በላይ የሚሆን ተሳታፊ ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ የአሰላ ከተማ አስተዳደር መረጃ ያመለክታል።
6.1K views17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ