Get Mystery Box with random crypto!

AMN-Addis Media Network

የቴሌግራም ቻናል አርማ addismedianetwork — AMN-Addis Media Network A
የቴሌግራም ቻናል አርማ addismedianetwork — AMN-Addis Media Network
የሰርጥ አድራሻ: @addismedianetwork
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 36.65K
የሰርጥ መግለጫ

This is an official Telegram channal for Addis Media Network (AMN) We trive to be the prime informer of issues. Hence, our motto says so, 'first to inform'
ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ !!
contact us via:- E-mail:- addisaammaa@gmail.com
twitter.com/AmnAddis

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-02-11 15:50:33
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ኩነቶች መረጃና ምዝገባ ኤጀንሲ ባለፉት ሁለት ቀናት በከተማ ደረጃ ከሰጣቸው አገልግሎቶች በከፊል፦
4.6K viewsedited  12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 11:23:53
ማላዊ ዳግም በአስከፊ የኮሌራ ወረርሽኝ ተጠቃች፡

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኤ ኤም ኤን) የካቲት 3/2015 ዓ.ም

ማላዊ ዳግም በአስከፊ የኮሌራ ወረርሽን መጠቃቷ ተሰማ
የአልም ጤና ድርጅት አገሪቱ ከዚህ በፊት አጋጥሟት በማያውቅ ሁኔታ በወረርሽኙ መጠቃቷን አመልክቷል፡፡

አገሪቱ ከዚህ ቀደም በወረርሽኙ 1200 ዜጎቿን ያጣች ሲሆን አሁን ላይ 29 ግዛቶች በወረርሽኙ መጠቃታቸው ተመልክቷል፡፡

በአሁን ወቅት የወረርሽኙን መስፋፋት ለመግታት የህክምና ባለሙያዎች ክትባት እየሰጡ ቢሆንም የአቅርቦት ችግር አጋጥሟል ተብሏል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጤና ባለሙያዎች ቡድን ለወረርሽኙ ምክንያት የሆነውን የማህበረሰቡን የንጽህና አጠባቅ ችግር ለመቅረፍና ንጹህ የመጠጥ ውሀ አቅርቦትን ለማስፋፋት እየሰራ መሆኑን አመልክቷል፡፡

በቀጣይ ወረርሽኙ በሌሎች ሀገራትም ሊከሰት ስለሚችል አገራት ከወዲሁ ጥንቃቄ እና ቅድመ ዝግጅት ሊያደርጉ እንደሚገባም ድርጅቱ ማሳሰቡን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
2.2K views08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 18:38:17
በቱርክ 39 አባላትን ያቀፈው የታዳጊ ልጃገረዶችና ወንዶች የመረብ ኳስ ተጫዋቾች እንዲሁም የመምህራኖቻቸው ቡድንን በህይወት የማግኘቱ ስራ መቀጠሉ ተገለጸ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኤ ኤም ኤን) የካቲት 2/2015 ዓ.ም

በቱርክ 39 አባላትን ያቀፈው የታዳጊ ልጃገረዶችና ወንዶች የመረብ ኳስ ተጫዋቾች እንዲሁም የመምህራኖቻቸው ቡድንን በህይወት የማግኘቱ የነብስ አድን ስራ መቀጠሉ ተገለጸ፡፡

በቱርክና ሶሪያ በተከሰተው አስከፊ ርእደ መሬት አደጋ ምክንያት በየቀኑ አዳዲስ ዜናዎች እየወጡ ይገኛሉ፡፡

በቱርክ በተከሰተው ርእደ መሬት የ 2 መምህራንና አንድ ታዳጊ የመረብ ኳስ ተጫዋች አስከሬን ተገኝቷል፡፡

39 አባላትን ያቀፈው የታዳጊ ልጃገረዶችና ወንዶች የመረብ ኳስ ተጫዋቾች እንዲሁም የመምህራኖቻቸው ቡድን ርእደ መሬቱ በተከሰተበት ወቅት ኢሳያስ በተባለ ትልቅ ሆቴል ውስጥ ከልምምድ መልስ እረፍት በማድግ ላይ ነበሩ ተብሏል፡፡

አዲያማና በተባለው የቱርክ ከተማ ለግጥሚያ ልምምዳቸውን አጠናቀው በሆቴሉ ውስጥ እረፍት እያደረጉ ባሉበት ሰአት ነው የርእደ መሬቱ አደጋ የተከሰተው ተብሏል፡፡

አራት የቡድኑ አባላት አደጋው በተከሰተበት ወቅት ከ7ኛ ፎቅ ራሳቸውን ወደ ምድር በመወርወር በህይወት መትረፍ መቻላቸው ተገልጿል፡፡

ቀሪዎቹ እስካሁን በህይወት ይኑሩ አይኑሩ የታወቀ ነገር የለም የተባለ ሲሆን የማፈላለጉ ስራ በነብስ አድን ሰራተኞቹ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተነግሯል፡፡

የታዳጊዎቹ ቤተሰቦች በህንጻው ፍርስራሽ አካባቢ ተገኝተው የልጆቻቸውን በህይወት መገኘት እየተጠባበቁ ነው መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል።
3.4K views15:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 12:30:03
የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ኃይልን ለማጠናከር  የሚያስችል የፖሊሲ ማሻሻያ ውይይት በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ(ኤ ኤም ኤን) የካቲት 2/2015 ዓም

የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ኃይልን ለማጠናከር እና በቀጠናው ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የሚያግዝ የፖሊሲ ማሻሻያ ውይይት በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።

ውይይቱ ከሁሉም የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል አባል ሀገራት የተውጣጡ ባለሙያዎችን ያገናኘ ሲሆን በተለያዩ የፖሊሲ ጉዳዮች ላይ በመወያየት ለውሳኔ ሰጪዎች ምክረ ሀሳብ ያቀርባልም ተብሏል።

ለአራት ቀናት የሚቆየውን የውይይት መድረክ የከፈቱት የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል  ሊቀ መንበር እና የኢፌዴሪ መከላከያ የውጭ ግንኙነት ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክተር ሜ/ጄነራል ተሾመ ገመቹ የፖሊሲ ማሻሻያው የቀጠናውን ሰላም ለመጠበቅ እና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በተጠናከረ መልኩ ለመመከት የሚያግዝ ነው ብለዋል።

ኢሳፍ 10 ሀገራትን በአባልነት ያቀፈ ቀጠናዊ ተቋም ሲሆን ከተመሰረተም 20 ዓመታትን አስቆጥሯል።

በአሰግድ ኪ/ማርያም
5.6K views09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 11:52:00
#መረጃ
#Update

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ የተለያዩ የወሳኝ ኩነት አገልግሎቶችን በየዕለቱ እየሰጠ ይገኛል፡፡

ተገልጋዮችም በየዕለቱ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለጠፋ አዲስ ትክ መታወቂያ የመስጠት፣ ነባር መታወቂያን የማደስ፣ የጋብቻ ውል ሰርተፍክት፣ የፍቺ ሰተፍኬት ...ወዘተ) በኤጀንሲው ቅርንጫፎች ተገኝተው መገልገል እንደሚችሉ የኤጀንሲው የሲስተምና መረጃ ቋት ቡድን መሪ አቶ ሙዘሚን አሰን አሊል ለኤ ኤም ኤን ዲጂታል ገልፀዋል።

በዚሁ መሰረት ያለፉት ሶስት ቀናት (ከጥር 29-የካቲት/2015 ዓ.ም) በከተማ ደረጃ 9366 ለሚሆኑ ተገልጋዮች የመታወቂያ ህትመት አገልግሎት መስጠት የተቻለ ሲሆን በነዚህ ቀናት ኤጀንሲው 920 የሚሆኑ ጥንዶችንም ህጋዊ የጋብቻ ውል ማፈራረም ችሏል። በሌላ በኩል ኤጀንሲው በቀናቱ 1806 ለሚሆኑ የአገልግሎቱ ጠያቂዎች የልደት ማረጋገጫ ሰጥቷል።

ትክክለኛውን የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዲጂታል ሚዲያ የትስስር አውታሮችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑን!
YouTube ➲ http://bit.ly/3itThRr
Telegram ➲ http://bit.ly/3W4puw9
Facebook ➲ https://bit.ly/3CJVgI8
Twitter ➲ http://bit.ly/3IKQ3TZ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የካቲት 02/2015 ዓ.ም
5.5K views08:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 16:36:09
#Update

በቱርክዬ እና በሶሪያ በተከሰተው የርዕደ መሬት አደጋ ምክንያት የሟቾች ቁጥር ጨምሯል
አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኤ ኤም ኤን) የካቲት 01/2015 ዓ.ም

ሰኞ ዕለት በቱርክዬ እና በሶሪያ በተከሰተው የርዕደ መሬት አደጋ ምክንያት የሟቾች ቁጥር 11,000 መድረሱን አልጄዚራ ዘግቧል።

ከ11 ሺህ ሟቾች መካከል ከቱርክዬ 8,574 የሚሆኑት ሲሆኑ ከሶሪያ ደግሞ 2,530 ሆነው መመዝገባቸውን ዘገባው አመልክቷል።

የነፍስ አድን ስራው አሁንም መቀጠሉ የታወቀ ሲሆን የሟቾች ቁጥር ከዚህም ሊጨምር እንደሚችል የመረጃ ምንጩ ጠቁሟል።
7.4K views13:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 12:03:55
በሰሜናዊ ቱርክ በደረሰው ርዕደ መሬት ከወደሙ የህንጻ ፍርስራሾች ውስጥ አዲስ የተወደለች ህፃን በህይወት ተገኘች

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኤ ኤም ኤን) የካቲት 01/2015 ዓ.ም

የህፃኗ እናት አደጋው በተከሰተበት ቅጽበት ምጥ ይዟት ስለነበር ከወደለች በኃላ ህይወቷ ሊያልፍ እንደቻለ ተዘግቧል፡፡

በአደጋው አባቷ፣ አራት ወንድሞችና እህቶቿ ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ህፃኗ ከህንፃ ፍርስራሽ ውስጥ በአደጋ ጊዜ ሰራተኞች መገኘት መቻሏ ታውቋል፡፡

የሕፃኗ አጎት ኻሊል አል-ሱዋዲ ሲናገሩ ህንፃው ሲደረመስ ከአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ጋር ወደ ቦታው ደርሰን ስንቆፍር ድምጽ ሰማንና ህፃኗን አገኘናት ብለዋል፡፡

የህፃናት ዶክተር የሆኑት ዶ/ር ሃኒ ማሩፍ ሲናገሩ “ህፃኗን ወደ ሆስፒታላችን ሲያመጧት መላ ሰውነቷ ተጫጭሮና ከባድ ቅዝቃዜ ውስጥ ገብታ ስለነበር ወደ ሙቀት ክፍል እንድትገባ ካልሺየምም እንድታገኝ አድርገናል›› ሲሉ ተናግረዋል።

በቱርክ በደረሰው ርዕደ መሬት ምክንያት እስካሁን ወደ 5 ሺህ የሚጠጉ ዜጎች መሞታቸውንና በመቶዎች የሚቆጠት ደግሞ በፍርስራሹ ውስጥ እንዳሉ ተዘግቧል፡፡

ቱርክ ርዕደ መሬት ከደረሰባቸው ግዛቶቿ አንዱ በሆነው ኢድሊብ ግዛት በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ በርካታ ህንፃዎቿ መውደማቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
2.9K views09:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 17:36:13
ክርስቲያን አቱስ በነብስ አድን ሰራተኞች ከህንጻ ፍርስራሸ ውስጥ በህይወት መገኘቱ ተገለጸ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኤ ኤም ኤን) ጥር 30/2015 ዓ.ም

በቱርክ ለሀታይስፖር ክልብ የሚጫወተው ጋናዊው የእግር ኳስ ተጫዋች ክርስቲያን አቱስ ቆስሎ በህይወት መገኘቱ ተገዘግቧል፡፡

በቱርክ በተከሰተው የርእደ-መሬት አደጋ ክርስቲያን አቱስ ደብዛው ጠፍቶ በነብስ አድን ሰራተኞች በየፍርስራሹ ሲፈለግ ቆይቷል፡፡ አደጋው ከተከሰተ በኋላ ተጫዋቹ የደረሰበት እንዳልታወቀ የክለቡ አመራሮች ሲያስታውቁ አስታውቀው ነበም፡፡ ተጫዋቹ አደጋው ከመከሰቱ ከሰአታት በፊት እሁድ እለት ክለቡ በነበረው ጨዋታ የማሸነፊያዋን ጎል ማስቆጠሩ ይታወቃል።

የቀድሞው የኒው ካስትልና ቸልሲ ተጨዋች የነበረው የ31ዓመቱ ክርስቲያን አቱ በህይወት ይገኝ ዘንድ ጋናውያንም ሆኑ በአለም ዙሪያ ያሉ አድናቂዎቹ ፈጣሪያቸውን ሲማጸኑ ቆይተዋል፡፡

አቱ እና የቱርኩ ለሀታይስፖር ክልብ ዋና ዳይሬክተር ታነር ሳቩት በህንጻ ፍርስራሽ ስር ታግተው ሊኖሩ እንደሚችሉ ተገምቶ ፍለጋው ሲካሄድ እንደቆየም ተነግሯል፡፡

ዳይሬክተሩ እስካሁን እንዳልተገኘ ተገልጿል፡፡ የክለቡ መቀመጫ የሆነችው ሃታይ ከተማ በርእደ መሬቱ በእጅጉ ከተጠቁ ከተሞች አንዷ ናት ተብሏል፡፡

ክርስቲያን አቱስ ቆስሎ ከህንጻ ፍርስራሽ ውስጥ በነብስ አድን ሰራተኞች በህይወት መገኘቱን ማናጀሩ ሙስተፋ ኦዛት ለቱርክ ሬዲዮ ገልጸዋል፡፡

የተጨዋቹ በህይወት መገኘት ተጨንቀው ለነበሩ ብዙዎችን እፎይታን እንደሰጠ ይታመናል ሲል የዘገበው ቢቢሲ ነው።
4.7K views14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 10:09:43 የአክስዮን ጉዳይ ጉዳያችሁ ለሆነ

ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ የተሰጠ ወቅታዊ መረጃ፦

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ስላዘጋጀው አዲስ አማራጭ ካሁን ቀደም ማሳወቃችን ይታወሳል። በዚህ አማራጭ ለመጠቀም እየታየ ካለው ፍላጎት እና በሂደቱ ካስተዋልነው በመነሳት ከአሁን ቀደም የቀረበውን መረጃ በዚህ ምልኩ በድጋሚ ለማስታወስ ወደድን!!

በባንኩ የቀረበው አማራጭ ምንድነው?
→ ባለፉት ሶስት ዙሮች ሰልጥነው የምስክር ወረቀት/ሰርተፊኬት የተቀበሉ እና ፍላጎቱ ያላቸውን ሰልጣኞች የባንኩን ፖሊሲና መመሪያ በጠበቀ መልኩ በአክሲዮን ማህበር አደራጅቶ ወደ ቢዝነስ እንዲገቡ ማድረግ፡፡

የአማራጩ አስፈላጊነት ምን ላይ ነው (ከብዙ በጥቂቱ)?
→ ለሥራ ማስኬጃ የሚሆነውን 20% መዋጮ ለማዋጣት አቅሙ ለሌላችሁ ነገር ግን የባንኩን ሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት ለምትሹ በጋራ ሆናችሁ ይህንን አቅም የምትፍጥሩበትን ዕድል ማመቻቸት
→ ለበርካቶች የሥራ ዕድል መፍጠር እና
→ ልማትን በማፋጠን የልማት አጋርነቱን ማስቀጠል

በአክስዮን ለመደራጀት ምን ያስፈልግዎታል?
→ በአክስዮን ማህበር ለመደራጀት ሼር መግዛት ያስፈልግዎታል።

ለመደራጀት የሚያስፈልግዎ ትንሹ ወጪ (ገንዘብ) ወይም ድርሻ (ሼር) ስንት ነው?
→ እያንዳንዱ ሼር 1000 ብር ዋጋ ያለው ሆኖ ዝቅተኛው የሚሸጥ የሼር መጠን አምስት ወይም 5000 ብር ነው ስለሆነም ትንሹ በአክስዮን ለመደራጀት የሚያስፈልግዎት የብር መጠን 5,000 ነው።

ለአክስዮን ስለመመዝገብ
→ ሰልጣኞች በአክሲዮን ለመሥራት ራሳቸውንና ሌሎች አብረዋቸው ሊሠሩ የተዘጋጁ የአክሲዮን አባላቶቻቸውን በማስመዝገብ የዚህ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ

ሰለማህበሩ እና ስለአባላቱ
→ የምታስመዘግቧቸው ሌሎች አባላቶች ሥልጠናውን ያልወሰዱ ከሆኑ በቀጣይ በሚኖሩ የሥልጠና ዙሮች መሠልጠን ይኖርባቸዋል፡፡
→በአክሲዮን ማኅበር ለመሥራት የምትመዘገቡ የአክሲዮን ባለቤቶች አብራችሁ ለመሥራት ተስማምታችሁ የቆያችሁ፣ ሕጋዊ ለመሆን በሂደት ላይ ያላችሁና በጋራ የምትጠሩበት ስም ካላችሁ ማስመዝገብ ትችላላችሁ፡፡
→በአዲስ መልክ የሚቋቋሙ ከሆነ ግን በምትመዘገቡበት ቀን የባንኩ ቅርንጫፍ ለጊዜው በሚሰጣችሁ መለያ ስም ወይም ቁጥር ትመዘገባላችሁ፡

ስለማህበሩ መሪ
→ በሚፈጠረው የአክሲዮን ማኅበር ውስጥ አስተባባሪ የሚሆኑት ሥልጠናውን ወስደው የምስክር ወረቀት ያገኙ አባላቱ ናቸው፡፡

ሌሎች ጉዳዮች
→ ተመዝጋቢዎች  ኢንቨስት የምታደርጉበትን ዘርፍ ተዘጋጅታችሁበት ለምዝገባ መቅረብ ይኖርባችኋል፣ ሼር መግዛት የምትችሉት በመረጣችሁት ዘርፍ ስለሆነ፡፡
→ እንዲሁም ምን ያህል ሼር እንደምትገዙ ቀድማችሁ እንድትዘጋጁበት ይሁን፡፡
5.6K views07:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 19:18:07
የፌዴራል መንግሥት እና የህወሓት የሰላም ስምምነት ኮሚቴ አባላት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ለመጀመሪያ ጊዜ ተገናኙ

የፌዴራል መንግሥት እና የህወሓት የሰላም ስምምነት ኮሚቴ አባላት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ለመጀመሪያ ጊዜ በሐላላ ኬላ ተገናኝተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለመጀመያ ጊዜ ከሰላም ስምምነት ትግበራ አስተባባሪ ኮሚቴ ጋር ምክክር አድርገዋል።

በውይይታቸው እስካሁን በሰላም ስምምነቱ አፈፃፀም ዙሪያ የተከናወኑ ተግባራት የተገመገሙ ሲሆን በቀጣይ ትኩረት በሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ተቀምጧል።

የሰላም ስምምነት ኮሚቴ አስተባባሪዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የመጀመሪያውን የገፅ ለገፅ ግንኙነት ያደረጉት የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል በሆነው ሐላላ ኬላ መሆኑን የኢቢሲ ዘገባ ያመለክታል።
3.6K views16:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ