Get Mystery Box with random crypto!

AMN-Addis Media Network

የቴሌግራም ቻናል አርማ addismedianetwork — AMN-Addis Media Network A
የቴሌግራም ቻናል አርማ addismedianetwork — AMN-Addis Media Network
የሰርጥ አድራሻ: @addismedianetwork
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 36.65K
የሰርጥ መግለጫ

This is an official Telegram channal for Addis Media Network (AMN) We trive to be the prime informer of issues. Hence, our motto says so, 'first to inform'
ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ !!
contact us via:- E-mail:- addisaammaa@gmail.com
twitter.com/AmnAddis

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-02-03 14:19:17
ቦቢ የተባለው ውሻ ለ30 ዓመታት መኖሩን ጊነስ ወርልድ ሪከርድ አረጋግጫለው አለ፡፡

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኤ.ኤም.ኤን) ጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም 


የዓለማችን ትልቁ የ30 ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረው ውሻ በጊነስ ወርልድ ሪከርድስ ላይ ሊሰፍር መቻሉ ተዘግቧል፡፡

ቦቢ እ.ኤ.አ በ1992 የተወለደ ሲሆን ዕድሜውም 30 አመት ከ266 ቀን መሆኑን ጊነስ ወርልድ ሪከርድስ ገልጿል።

ጊነስ ወርልድ ሪከርድስ በመግለጫው ፖርቹጋላዊው ውሻ ቦቢ ሪከርዱን የወሰደው ባለፈው ዓመት የአለማችን ትልቁ ውሻ ተብሎ ከተሰየመው ስፓይክ ከተባለ የ23 አመት ውሻ መሆኑ ተገልጿል።

ቦቢ ዕድሜውን በሙሉ ኮንኬይሮስ በተባለች የፖርቹጋል ገጠራማ መንደር ውስጥ ከአሳዳጊዎቹ
ጋር እንደሚኖር ታውቋል።

ትክክለኛውን የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዲጂታል ሚዲያ የትስስር አውታሮችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑን!
YouTube ➲ http://bit.ly/3itThRr
Telegram ➲ http://bit.ly/3W4puw9
Facebook ➲ https://bit.ly/3CJVgI8
Twitter ➲ http://bit.ly/3IKQ3TZ
አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ጥር 26/2015 ዓ.ም
5.3K views11:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 09:42:36
የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜ ዛሬ ጥር 26/2015 ዓ.ም ከቀኑ 11፡30 ላይ ያበቃል: - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ(ኤ ኤም ኤን) ጥር 26/2015 ዓ.ም

የ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜ ዛሬ አርብ ጥር 26/2015 ዓ.ም ከቀኑ 11፡30 ሰዓት የሚያበቃ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል።

ቀድመው ቅሬታ ያቀረቡ ተፈታኞች የቅሬታቸውን መልስ www.neaea.gov.et:8081 ድረ ገጽ ላይ የመለያ ቁጥራቸውን (Registration Number/ID) ብቻ በማስገባት ከዛሬ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ማየት የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል።

የቀረቡ ቅሬታዎች ተጣርተው ሲጠናቀቁ የቅሬታዎቹን ምላሽ በቀጣይ ቀናት የሚያሳውቅ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጾ፤ የቅሬታ ምላሽ ያልደረሳችሁ ተፈታኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ አሳስቧል።

በተመሳሳይ ያልተሟላ ወይም የተሳሳተ ወይም የሌላ ሰው መለያ ቁጥር በመጠቀም ቅሬታ ያቀረቡ ተፈታኞች የስም ዝርዝራቸውን ዛሬ ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ከላይ በተጠቀሰው ድረ ገጽ ላይ በመመልከት ቅሬታቸውን በትክክለኛ መለያ ቁጥራቸው በድጋሚ ማቅረብ የሚችሉ መሆኑንም መገለጹን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
5.7K views06:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 17:51:20 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በቅርቡ ለ4ኛ ዙር ሰልጣኞች ለሚሰጠው ስልጠና በሶስተኛው ዙር ስልጠና የነበሩ ገለዳዮችን ትምህርት ይሆኑ ዘንድ ሰልጣኞች ይወቁልኝ ብሎ ተከታዮቹን ሃሳቦች አቅርቧል፦

በሶስተኛው ዙር ስልጠና ምን ምን ጥንካሬ እና ድክመቶች ነበሩ? ከ4ኛው ዙር ሰልጣኞች ምን ይጠበቃል??

ጥንካሬዎች?

1.  በሺዎች የሚቆጠሩ ሰልጣኖች እራሳቸው በእውቀትና እና በኢኮኖሚ ተቀይረው ሀገራቸውን ለመቀየር  የፀና አቋም ያሳዩበት  ነበር፡፡
2. ብዙዎች በሚያስገርም ሁኔታ ንቁ ተሳታፊ ነበሩ፣ በጥያቄም በመልስም!
3.  ብዙዎች ሰአት አክባሪ ነበሩ፣  መግቢያ ሰአትን አክብረው በስልጠና ማዕከላት ተገኝተዋል ከዛም ስልጠናው ሲጠናቀቅ ብቻ ወጥተዋል!
4.  ብዙዎች በስልጠናው የኢትዮጵያ ልማት ባንክን የሊዝ ፋይናንሲንግ የብድር ስርአት ለመጠቀም ቅድመ ሁኔታ ስለሆነ ስልጠናውን ለመካፈል ሲሉ ብቻ  የመጡ የነበረ ቢሆንም ከመጀመሪያው ቀን አንስቶ ለማንኛውም በንግዱና በህይወቱ መቀየር ለሚፈልግ ሰው ስልጠናው ወሳኝ ክህሎትንና እውቀትን ማስጨበጫ መሳሪያ እንደሆነ እየመሰከሩ ስልጠናዎች ተጠናቀዋል።
5.  በከፍተኛ ደረጃ እርስ በርስ መግባባትና መከባበር በሰልጣኖች መሀከል ዳብሮ ነበር፡፡ አንዳንዶች ደግሞ ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም በጋራ ለመስራት እድሉን ያገኙበትና እውቂያ የፈጠሩበት ሁኔታም ነበር፡፡
6. በአንዳንድ ስልጠና ማዕከሎች ሙቀት የነበረ ቢሆንም ተቋቁመው ስልጠናቸውን በፍላጎት ተከታትለዋል፡፡
7. በተሳታፊዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች፣ በአሰልጣኞች እና በባንኩ አስተባባሪዎች፣ እንዲሁም እጅግ ቁልፍ የሆኑ ጥያቄዎች በባንኩ ፕሬዚደንት አመርቂ መልስ የተሰጠበት ሁኔታ ነበር።
8. አራስ እናቶች እና ነፍሰ-ጡሮች በስልጠናው የተካፈሉበትና የበቁበት ሁኔታ ነበር፡፡

ድክመቶች?

1.  አንዳንድ ሰልጣኞች በጣም እያረፈዱ መምጣት
2.  አንዳንድ ሰልጣኞች ከስልጠና ማዕከሎች ጠፍቶ መሄድ
3.  አንዳንድ ሰልጣኞች በስልካቸው ላይ   ያለአግባብ እና ያለምክንያት በተደጋጋሚ እና ለረዥም ደቂቃዎች ማሳለፍ
4.  አንዳንድ ሰልጣኞች ከስልጠናው አላማና ጭብጥ ውጪ ውይይቶችን በተሳታፊዎች መሀከል እንዲፈጠር ምክንያት መሆን
5.  ከስልጠና መቅረት
6.  አቴንዳንስ ላይ የሰውን ስም እያጠፉ/እየቀየሩ የራስን ስም ማድረግና መፈረም
7.  ለሰው አስመስሎ ለመፈረም ሙከራ ማድረግ
8.  በስልጠና ወቅት የውይይት ሰአት ሳይደለ ድምፅን አጉልቶ ከጎን ካለ ሰው ጋር ማውራት
9.  በአንዳንድ ሰልጣኞች አማካኝነት ለስልጠና ከተመዘገቡና ከተጠበቁ ሰዎች ውጪ ሌሎች እንዲመጡ ማድረግና በተለይም በምግብና ሰዓት አካባቢ ያለአግባብ ግርግር መፍጠር

ማጠቃለያ፡

በነበሩ ጥንካሬዎች አማካኝነት የሚፈለገው እውቀትና ክህሎት ተጨብጧል፣ ግሩም የሆነ የእረስ በእርስና የንግድ ትስስር ለመመስረት ተሳታፊዎች በራሳቸው ተነሳሽት በራሳቸው መንገድ መሠረት ጥለዋል፣ በባንኩና በተሳታፊዎች መሀከል  ለዘለቄታው ጠቃሚ መስተጋብር ተገንብቷል ፣ ሰልጣኞች ለሊዝ ፋይናንሲንግ ብድር ብቁ የሚያደርጋቸውን ሰርተፊኬት ተረክበው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል።

በድክመቶች ምክንያት በዋናነት የክስተቱ ምንጭ የነበሩ ሰዎች ከዚህ ውድ ዕውቀት መቋደስ አልቻሉም። ከስልጠና የጠፉና የቀሩ ደግሞ ለሰርተፊኬት ብቁ ባለመሆናቸው  ምክንያት በሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግልታችን መጠቀም የሚገባቸውን ዕድል አምክነዋል።
4.3K views14:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 17:43:47 ማስታወቂያ
ይህ የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ትክክለኛው የትዊተር አድራሻ ነው።
ይወዳጁንና ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ!!

https://twitter.com/AmnAddis?t=Dbyu5HmIQRjYAgB9gYa98A&s=09
4.1K views14:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 17:40:26
#ውሎ#አዲስ!

ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ
በአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ
አዲስ ቴሌቪዥን እና
በዲጂታል ሚዲያ አውታሮቻችን በእየሩሳሌም ወሰንየለህ አጋፋሪነት በቀጥታ ወደ እናንተ ይደርሳል።

አብራችሁን ስለምትሆኑ እናመሰግናለን!!

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ
ጥር 25/2015 ዓ.ም
3.7K views14:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 17:40:00
መንግስት በጦርነቱ በተጎዱ አካባቢዎች መልሶ ማቋቋም እና ግንባታ ዙሪያ ከልማት አጋሮች ጋር በጋራ እየሰራ ነዉ፡-የፕላን እና ልማት ሚኒስቴር

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኤ ኤም ኤን) ጥር 25/2015 ዓ.ም

መንግስት በጦርነቱ በተጎዱ አካባቢዎች መልሶ ማቋቋም እና ግንባታ ዙሪያ ከልማት አጋሮች ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን የፕላን እና ልማት ሚኒስትሯ ዶ/ር ፍጹም አሰፋ ገለጹ፡፡

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ በኢትዮጵያ ከጃፓን አምባሳደር ኢቶ ታካኮ ጋር በጽህፈት ቤታቸዉ ተወያይተዋል፡፡
በዉይይታቸዉም በሃገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ዝግጅትና ይዘት ላይ ሚኒስትሯ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን ሪፎርሙ የሃገሪቱን ቀዳሚ የኢኮሞሚ እድገት ፍላጎቶችና መሰረቶች ታሳቢ አድርጎ በመንግስት እየተዘጋጀ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በሃገሪቱ የነበረዉ ጦርነት ተወግዶ በተደረሰዉ የሰላም ስምምትና ስምምነቱን ተከትሎ መንግስት እያከናወናቸዉ ያሉ ልዩ ልዩ ተግባራትን በተመለከተም ሚነስትሯ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን በመልሶ ማቋቋም እና ግንባታ ዙሪያ መንግስት ከልማት አጋሮች ጋር በጋራ እየሰራ ነዉ ብለዋል፡፡
3.4K views14:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 17:39:20 የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር እና ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ 212 ሚሊዮን ብር የድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኤ ኤም ኤን) ጥር 25/ 2015

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር እና ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ የ2023 የሁለትዮሽ ትብብር ስምምነት ተፈራረመዋል።

የትብብር ስምምነቱ ለግጭት ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች በተለይም በትግራይ፣ አማራ፣ አፋር፣ ኦሮሚያ እና ቤንሻንጉል-ጉሙዝ የሰብዓዊ ድጋፎችን በተደራጀ መንገድ ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል።

በመሆኑም እ.ኤ.አ. በ2023 በጀት ዓመት 212 ሚሊዮን 493 ሺህ ብር በጥሬ ገንዘብ እንዲሁም 44 ሚሊዮን ብር በዓይነት ለማህበሩ ድጋፍ እንደሚደረግለት በስምምነት ስነ ስርአቱ ላይ ተገልጿል፡፡

ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ዋና ፀሃፊ አቶ ጌታቸው ታዓ እና የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ የኢትዮጵያ ልዑክ ኃላፊ ኒኮላስ ቮን አርክስ ናቸው።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ዋና ፀሃፊ አቶ ጌታቸው ታዓ ትብብሩ የማህበሩን ሁለንተናዊ አቅምን ለመገንባት፣ የልማት ስራዎችን ለማገዝ እና በግጭት የተጎዱ ሰዎችን ለማቋቋም የተጀመረውን ስራ በሚፈለገው ደረጃ ማሳለጥ ያስችላል ብለዋል፡፡

ዋና ፀሃፊው አያይዘውም ማህበሩ በመላ ሀገሪቱ በጦርነትና በተፈጥሮ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረግ እና ግጭቶችን ለመፍታት ለሚያደርገው ጥረት የላቀ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል፡፡

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ የኢትዮጵያ ልዑክ ኃላፊ ኒኮላስ ቮን አርክስ በበኩላቸው ስምምነቱ በአደጋ ጊዜ የሰብዓዊ ድጋፎችን ምላሽ ለመስጠት የማይተካ ሚና እንዳለው አስረድተዋል።
በስምምነቱ መሰረትም በጦርነት፣ በድርቅና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ተባብረው እንደሚሠሩም ኃላፊው ገልጸዋል።

ስምምነቱ አጋርነትን ለማጠናከር፣ የልማት ስራዎች ለመተግበር፣ የቤተሰብ ትስስርን መልሶ ለማቋቋም እንዲሁም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ዜጎች በኢኮኖሚ፣ በጤናና ስነ ተዋልዶ ዙሪያ አቅም መገንባት እንደሚያስችል ተመልክቷል።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር እና ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ጉዳዮች የተጎዱትን ዜጎችን ለመጠበቅ እና ለመርዳት ከ80 ዓመታት በላይ በቅንጅት እየሰሩ እንደሚገኙ ከማህበሩያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
3.1K views14:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 17:38:53 የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከሶማሊያ ሀገር ለፖሊሳዊ ትምህርት ስልጠና ለመጡ የፖሊስ መኮንኖች አቀባበል አደረገ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኤ ኤም ኤን) ጥር 25 / 2015 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የመጀመሪያ ዲግሪና የሁለተኛ ዲግሪ ፖሊሳዊ ሳይንስን ለመቅሰም ከሶማሊያ ሀገር ለመጡ የፖሊስ መኮንኖች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ማድረጉን ገለፀ።

በአቀባበል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል እና የወቅቱ የምስራቅ አፍሪካ ፖሊስ አዛዦች ኅብረት ድርጅት ፕሬዚዳንት ደመላሽ ገ/ሚካኤል ወደ ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ዕድል በማግኘት እንኳን ደህና መጣችሁ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለረጅም ዘመናት ከሀገራችን አልፎ የጎረቤት ሀገራት የፖሊስ አመራሮች እና አባሎችን በማስተማር ለቀጠናው ሰላም እና ደህንነት ግንባታ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም ኮሚሽነሩ ገልጸዋል፡፡

ከጎረቤት ሀገራት ጋር ተባብሮ መስራትና የፖሊስ ተቋማቱን በትምህርትና ስልጠና ማጠናከር ድንበር ተሻጋሪ ወንጀልን ለመከላከል እንደሚያግዝም ኮሚሽነር ደመላሽ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለተለያዩ ሀገራት የፖሊስ አባሎች የትምህርት እድል በመስጠት ሲያስተምር እና ሲያሰለጥን የቆየ ሲሆን በቅርቡም ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ከሶማሊያ አቻቸው ሜጀር ጀነራል አብዲ ሀሰን መሀመድ ጋር በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሶማሊያ ወጣት ፖሊስ አመራሮች ትምህርትና ስልጠና እንዲያገኙ የሚያስችላቸውን ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል።

በዚህ ስምምነት መሠረት ነው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና እና በሁለተኛ ዲግሪ በተለያዩ የትምህረት ፕሮግራሞች 38 የሶማሊያ ፖሊስ መኮንኖችን በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ለማስተማር የተቀበለው።

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከሶማሊያ ፖሊስ በተጨማሪ ከደቡብ ሱዳን የመጡ የፖሊስ መኮንኖችን ተቀብሎ በማስተማር ላይ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ምክትል ኮሚሽነር ተሻለ ተሾመ ገልጸዋል፡፡

ለትምህርት የመጡት የሶማሊያ የፖሊስ መኮንኖች በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባለፉት አራት አመታት የተከናወኑ ተጨባጭ የሪፎርም ስራዎችን ተዘዋውረው መመልከታቸውን ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
3.3K views14:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 11:52:14
#ዜና#አዲስ!

ከቀኑ 6:30 ጀምሮ
በአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ
አዲስ ቴሌቪዥን እና
በዲጂታል ሚዲያ አውታሮቻችን  በይፍቱስራ ቱጁ አጋፋሪነት በቀጥታ ወደ እናንተ ይደርሳል።

አብራችሁን ስለምትሆኑ እናመሰግናለን!!

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ
ጥር 25/2015 ዓ.ም
5.2K views08:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-01 17:47:45
#ውሎ#አዲስ!

ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ
በአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ
አዲስ ቴሌቪዥን እና
በዲጂታል ሚዲያ አውታሮቻችን  በሶሎሞን ጥዑመልሳን አጋፋሪነት በቀጥታ ወደ እናንተ ይደርሳል።

አብራችሁን ስለምትሆኑ እናመሰግናለን!!

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ
ጥር 24/2015 ዓ.ም
4.0K views14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ