Get Mystery Box with random crypto!

መረጃ//mergaa

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethomergaa — መረጃ//mergaa
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethomergaa — መረጃ//mergaa
የሰርጥ አድራሻ: @ethomergaa
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.11K
የሰርጥ መግለጫ

@ethomergaa
🎩ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ ፣
🎩የአስተሳሰብ ምህዳሮች ፣
🎩የምሁራን እይታዎች እና መጽሐፈቶች ፣
🎩የአለም ሙሉ መረጃ እና የታሪክ ልዩ መዛግብቶች ።
ለማንኛውም መረጃ 👉 @Natiyt
ኢትዮጵያዊ ሆኘ የተወለድኩ ኢትዮጵያዊ ሆኘ ያደኩ ኢትዮጵያዊ ሆኘ መሞት የምፈልግ ኢትዮጵያዊ ነኝ። ኢትዮጵያ በክብር ለዘለአለም ትኑር አሜን !!!
የናንተው ቻናል ነው

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 23:56:16
የፖሊስ መልዕክት !

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ የሰጡት ቃል ፦

" ምንም በማያውቁት ጉዳይ በህጻናቱ ላይ የተፈጸመው ይህ አሰቃቂ ወንጀል ሁሉንም በእጅጉ አሳዝኗል።

ወላጆች የሚቀጥሯቸው የቤት ሠራተኞችን ማንነት ጠንቅቀው ማወቅ ይገባቸዋል።

እንደ ቤተሰብ ሆነው የሚኖሩ የቤት ሠራተኞች እንዳሉ ሁሉ እንደዚህ አይነት አሰቃቂ ወንጀል የሚፈጽሙም ስላሉ ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ አለበት። "

#ተጨማሪ መረጃ ፦

• በአንድ ቀን በአሰቃቂ ሁኔታ ሁለት ታዳጊ ልጆቻቸውን ያጡት ወላጆች በከባድ ሐዘን ውስጥ ይገኛሉ።

• ወንጀሉ በተፈጸመበት አካባቢ ያሉ ነዋሪዎችም በእጅጉ ተረብሸው ነው የሚገኙት።

• ፖሊስ በወንጀሉ ዙሪያ ተጨማሪ ምርመራ እያደረገ ነው።

- ተጠርጣሪዋ ህጻናቱን አንቃ እና ስለት ተጠቅማ በአስቃቂ ሁኔታ መግድሏ የሚያመላክቱ መላምቶች አሉ።

- ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን ለመፈጸም ምን እንዳነሳሳት ወይም የአእምሮ ጤና ችግር እንዳለበት ለማወቅ ምርመራዎች እየተካሄዱ ነው።

- በወንጀሉ የተጠርጠረችው ግለሰብ በቤት ሠራተኛነት ግድያው ለተፈጸመበት ቤተሰብ ስታገለግል ቆይታለች።

• ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን የፈጸመችው ወላጆች የሌሉበትን ሰዓት ጠብቃ ነው።

መረጃው ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ ከሰጡት ቃል የተወሰደ ነድ።
207 viewsmenty (ßoss), 20:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 23:56:16 ሰበር መረጃ

በወልቃይት በረከት እና ሉግዲ መሃከል በህወሓት ጉጀሌ ጀሌ ላይ በተወሰደው እርምጃ ህወሓት ወያኔ አስቀድሞ ከሰራቸው 5 ባለ ሶስት ደረጃ  ምሽጎች ውስጥ ሶስቱ ሙሉ በሙሉ በጥምር ሃይሉ ተሰብረዋል።
197 viewsmenty (ßoss), 20:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 19:20:13 ሰበር ዜና

በዋግ ኽምራ ዞን በዝቋላ ወረዳ ስር የነበረና ጁንታው ይተማመንበት የነበረው የቅዳሚት ማዕከል ምሽግ በጥምር ሃይሉ ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል:: በዚህም ምክንያት ጁንታው ወደ አብርገሌ ከተማ እየሸሸ ነው አብርገሌ ማለት ለሰቆጣ 65 ኪሎ ሜትር ይርቃል ለመቀሌ ደግሞ 45 ኪሎ ሜትር ይርቃል

እያመመው መጣ
569 viewsmenty (ßoss), 16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 18:27:41
የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ የሩሲያ ጦርነትን ጨምሮ በትልልቅ ጉዳዮች ላይ በመጠመዱ እንዲሁም በፌዴራል መንግሥት የቀረበለትን የሰላም አማራጭ በሰንካላ ምክንያት በማጓተቱ ዓለም ቸል ያለውና ትኩረት የነፈገው ህወሓት ጉዳዩ ሲያብሰከስከው ከርሟል፡፡ እናም ድጋሚ በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አጀንዳ ለመሆን በተለያዩ ግንባሮች የማያሸንፈውን ጦርነት ለኮሱ እየተለበለበ ይገኛል፡፡

በአሁኑ ወቅት የአሸባሪው የውጭ ክንፍ አስተባበሪ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ትኩረት ተነፍጎት የነበረው ህወሓት ዳግም እንዲያንሰራራ ከተሠጠው ሐላፊነት ውጪ በመላው ዓለም የቡድኑን ተልዕኮና አጀንዳ ማስፈጸም ዋናው ተግባሩ አድርጎታል።

የአሸባሪ ቡድኑ ቀደም ሲል ወደ ትግራይ የሚጓጓዘውን የሰብአዊ እርዳታ በማስተጓጎልና ለሕዝብ የተመደበ የሰብአዊ እርዳታን ለጦርነት እንዲውል በማድረግ ግንባር ቀደም ተጠያቂ ሆኖ ሳለ የዓለም አቀፍ የግንኙነት መረቡን በመጠቀም አሳሳች መረጃዎችን እያሰራጨ ይገኛል።

በቅርቡ እንኳን በኢትዮጵያ መንግሥት የቀረበለትን የሰላም ድርድር ወደ ጎን በመተው በተለያዩ ግንባሮች ወረራ ቢፈጽምም፤ የቡድኑ ቃል አቀባይ በራሱ ሚዲያ ወጥቶ ጦርነት ውስጥ የገባነው መንግሥት የከፈተብንን ጥቃት ለመመከት ነው ብሏል፡፡ የመከላከል ጦርነት ላይ ነን በሚል አንድም የትግራይ ሕዝብን ሁለትም የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ አደናግሮ እራሱን እንደተጠቃ በማድረግ የዓለምን ትኩረት ለመሳብም ሲፍጨረጨር ይታያታል።

ይህን የቃል አቀባዩን ሥራ ለማሰካትም ይመስላል የአሸባሪው ቡድን ደጋፊዎች አቋርጠው የነበሩትን የመንከባለል ትርኢታቸውን (እምቦር ተንከብላይነት) በአሜሪካና አውሮፓ ከተሞች ማሳየት ጀምረዋል።
586 viewsmenty (ßoss), 15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 18:27:40
524 viewsmenty (ßoss), 15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 18:27:40
የወልድያ ከተማ ሕዝብ ለወገን ጦር የሚያደርገው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ያነጋገራቸው የወልድያ ከተማ ነዋሪዎች እንደገለጹት፤ ለጀግኖቹ የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ለአማራ ልዩ ኀይል፣ ለፋኖ እና ለሚሊሻ በያሉበት ግንባር የምግብና የውኃ አቅርቦት እያደረሱ ነው።

አስተያየት ሰጪዎቹ ጀግኖቹ የወገን ጦር አባላት የኢትዮጵያን ጠላት እያርበደበዱ ባሉበት በዚህ ወቅት እኛ የምናደርገው ድጋፍ እጅግ ቀላሉ ነው ብለዋል። እናም የበለጠ እና ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡

ሶሪያውያን ሀገር ቢያጡ በመላው ዓለም ተበትነዋል ያሉት አስተያየት ሰጭዎቹ፤ ኢትዮጵያ እንድትኖር ስለምንፈልግ ሁሉንም መስዋዕትነት እንከፍላለን ብለዋል። ስለዚህ መላው ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያን ታሪካዊ ጠላት ለማጥፋት በሚደረገው ትግል ተሳታፊ እንዲሆኑ የከተማዋ ነዋሪዎች ጥሪ አቅርበዋል።

የወልድያ ከተማ አሥተዳደር ምክትል ከንቲባና የትምህርት ጽሕፈት ቤት ኀላፊ አቶ ደምስ አለባቸው፤ የወልድያ ከተማ ሕዝብ በየቀበሌው እና በየመንደሩ ተደራጅቶ ለፀጥታ ኀይሉ ሁሉን አቀፍ እና የተጠናከረ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ነግረውናል፡፡ ነዋሪው ትኩስ ምግቦችን ጭምር ግንባር ድረስ እያቀረበ መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል።

አቶ ደምስ ሕዝቡ የደጀንነት ተግባሩን በሚገባ እየተወጣ ነው፤ ለወገን ጦር
እየሰጠውም ያለው ድጋፍ አስደሳች ነው ብለዋል።
522 viewsmenty (ßoss), 15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 18:27:39
432 viewsmenty (ßoss), 15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 18:27:39
428 viewsmenty (ßoss), 15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 18:27:39
419 viewsmenty (ßoss), 15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 18:27:38
በቂ መሳሪያ ሳይሆን በቂ ሰው ስላለን ሕዝባዊ ማዕበል ችግር የለውም የአሸባሪው ሕወሓት አፈቀላጤ ጌታቸው ረዳ የጭካኔ ጥግ
417 viewsmenty (ßoss), 15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ