Get Mystery Box with random crypto!

AMN-Addis Media Network

የቴሌግራም ቻናል አርማ addismedianetwork — AMN-Addis Media Network A
የቴሌግራም ቻናል አርማ addismedianetwork — AMN-Addis Media Network
የሰርጥ አድራሻ: @addismedianetwork
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 36.65K
የሰርጥ መግለጫ

This is an official Telegram channal for Addis Media Network (AMN) We trive to be the prime informer of issues. Hence, our motto says so, 'first to inform'
ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ !!
contact us via:- E-mail:- addisaammaa@gmail.com
twitter.com/AmnAddis

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 62

2022-08-31 21:53:49
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ሴቶችን ማብቃት እና መደገፍ እንደሚገባ አስገነዘቡ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኤ ኤም ኤን) ነሐሴ 25/2014

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ሴቶችን ማብቃት፣ መደገፍ እና ክትትል ማድረግ የማይቋረጥ ተግባር ሊሆን እንደሚገባ አስገነዘቡ።

የአፍሪካ ሴቶች መሪዎች ጥምረት ስብሰባውን በአዲስ አበባ ያካሄደ ሲሆን፣ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ከጥምረቱ አባላት ጋር ተወያይተዋል።

በውይይቱ ወቅት ፕሬዚዳንቷ በሴቶች አመራር ሥልጠና እና ድጋፍና ክትትል በማድረግ በኢትዮጵያ እየተካሄዱ ስላሉ ፕሮግራሞች ገለጻ ማድረጋቸውን ከፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

የአፍሪካ ሴቶች መሪዎች ጥምረት በፈረንጆቹ 2017 በአፍሪካ ሕብረትና በተመድ የተቋቋመ ሲሆን፥ በ30 ሀገራት ብሔራዊ ቅርንጫፎችም አሉት።

የኢትዮጵያ ቅርንጫፍም ከሶስት ዓመታት በፊት በፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በይፋ ተቋቁሟል።

ጥምረቱ የልምድ ልውውጥ፣ የአሠራር ቅንጅት፣ ቅድሚያ ትኩረቶችን መንደፍ ላይ ትኩረቱን በማድረግ የሚሰራ መሆኑ ተመላክቷል።
4.1K views18:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 20:13:18 የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር በጋራ መስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኤ ኤም ኤን) ነሐሴ 25/2014

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ  ጋር በጋራ መስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

ስምምነቱ በዋናነት ስራ ፈጣሪ ዜጎችን መደገፍ የሚያስችል ሲሆን፤ በሥልጠና፣ሥራ ዕድል ፈጠራና በኢንቨስትመንት ስፍራዎች ላይ ምቹ የስራ ሁኔታን መፍጠር ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ተጠቁሟል፡፡

በተጨማሪም የፋይናንስ አቅርቦትና ተደራሽነትን በማሻሻል ረገድ ተቋማቱ በጋራ እንዲሰሩ ያስችላል፡፡

ስምምነቱንም የስራና ክህሎት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል እና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው ተፈራርመዋል፡፡

ሚኒስትሯ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ስምምነቱ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች የፋይናንስና ስልጠና ድጋፍ እንዲያገኙ ያደርጋል፡፡

የስራ እድል ፈጣራ ላይ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረውም ገልጸዋል፡፡

ስምምነቱ ከቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚወጡ ዜጎችን ወደ ስራ እንዲገቡ በማድረግ ረገድ ጠቀሜታ እንዳለው መናገራቸውንም ኢዜአ ዘግቧል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው በበኩላቸው፦ ባንኩ የሥራ ዕድል ፈጠራን ማሳደግ፣ ክህሎትን ማስፋት፣ ኢንቨስትመንትን ማስፋፋትና የኢኮኖሚ ዕድገት ፈጣን እንዲሆን ማድረግ ተልዕኮ ይዞ እየሰራ  መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም በገበያ ሥርዓት ሊፈጸሙ የማይችሉ ሥራዎችን በፖሊሲ ጣልቃገብነት ተግዳሮቶችን በመፍታት ምቹ ሁኔታዎችን  ለመፍጠር እየሰራ መሆኑን  ጠቅሰው፤ ከዚህ አኳያ የስራ ፈጠራ ሃሳብ ይዘው የፋይናንስ አቅም የሌላቸውን ዜጎች በማገዝ ኃላፊነቱን እንደሚወጣ ተናግረዋል፡፡

አክለውም ሥምምነቱ በሀገር ደረጃ በኢንዱስትሪ፣ በግብርና እንዲሁም በወጪ ንግድ ዘርፎች ላይ የተሻለ የስራ ፈጠራ እድል ለማምጣት እንደሚያግዝ   ገልጸዋል።
4.2K views17:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 13:48:05
በገፍ ሠው አስገብተህ የሚያልቀው ያልቃል ....

የጌታቸው ረዳ የጭካኔ ጥግ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ነሐሴ 25 ቀን 2014
5.2K viewsedited  10:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 12:33:06 "የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዉ የጎላ ነዉ"

የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ነሐሴ 25 ቀን 2014

የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት በህይወት ክህሎት ስልጠና፣ በሥራ ክህሎት ዝግጁነት፣ በስነ ምግባርና በሥራ ፈጠራ ክህሎት ንቁና ብቁ የሆኑ ወጣቶችን ወደ ገበያው በማስገባት ተጨባጭ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን እንደሚያስገኝ የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡

በስራ ኢንተርፕራይዝ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የሥራ ስምሪት ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ሰብሃዲን ሱልጣን፤ በቂ የሥራ፣ የክህሎትና የህይወት ክህሎት ስልጠና አግኝተው ወደ ሥራው ዓለም የሚቀላቀሉ ወጣቶች ከባለሀብቶች ጋር ተግባብተው የመስራት ዕድላቸው ሰፊ ስለሚሆን ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ለኢኮኖሚያዊ ዕድገቱ ቀጥተኛ አስተዋፅዖ ይኖራቸዋል ብለዋል።

በማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ አማካኝነት በተደረገ ጥናት መሠረት በአዲስ አበባ ደረጃ ከ18 እስከ 20 ዕድሜ ክልል ባሉ ወጣቶች ሥራ አጥነቱ ይከፋል ያሉት አቶ ሰብሃዲን፤ በተለይ ከ10ኛ ክፍል በታች የሆኑ የስራ አጥ ወጣቶች 82 በመቶዎቹ እንዲሁም ከሴቶችም በዚህ የዕድሜ ክልል ካሉት 30 ነጥብ 4 በመቶ ያህሎቹ ስራአጥ ናቸው፡፡

በትምህርት ዝቅ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ገበያው ላይ ያላቸው ተፈላጊነት አናሳ መሆኑ ለስራ አጥ ቁጥሩ መጨመር ምክንያት መሆኑን አንስተው፤ ፕሮጀክቱ ለእነዚህ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር በኢኮኖሚያዊ ዕድገቱ ላይ የጎላ አስተዋፅኦ እንዲኖራቸው ያስችላል የሚል ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በተመሳሳይ ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 25 ከሆኑ ወጣቶች 24 ነጥብ 6 በመቶ ያህሎች ሥራ የማግኘት ዕድላቸው ዝቅተኛ መሆኑን አቶ ሰብሃዲን ጠቅሰው፤ ፕሮጀክቱ እነዚህን ዜጎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ ላይ የሚያተኩር መሆኑንም አስገንዘበዋል፡፡

አክለውም፤ “በእነዚህ የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ወጣቶች ወደሥራው ዓለም መግባት የሚችሉት ክህሎት ሲኖራቸው ነው፡፡ ክህሎቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚያገኙት ደግሞ ወደቀጣሪዎች ተጠግተው ስልጠና ሲያገኙ ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ተቀርጿል፡፡ በዚህ ፕሮጀክት ሳቢያ ወጣቶቹ በየፋብሪካው ውስጥ ገብተው ለ6 ወራት የሥራ ላይ ልምምድ ስልጠና ይወስዳሉ” ብለዋል።

ወጣቶቹ ለስድስት ወር በፋብሪካዎች ውስጥ ሲሰለጥኑ በወር 1 ሺህ 980 ብር እንደሚከፈላቸው የገለፁት አቶ ሰብሃዲን፣ ከስልጠናው በኋላም ልምምድ ያደረጉበት ፋብሪካን ጨምሮ በተለያዩ ድርጅቶች ውስጥ ቅጥር እንዲፈፀምላቸው ይደረጋል፡፡

ከስልጠና በኋላ የሥራ ማፈላለጊያ የሶስት ወር ደመወዝ ይሰጣቸዋል፡፡ ከ70 በመቶ በላይ የሆኑት ሰልጣኞች ግን እዚያው የሥራ ልምምድ ባደረጉባቸው ተቋማት ውስጥ እንዲቀጠሩ ይደረጋል ሲሉ አሳውቀዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ህፃን ላላቸው ሴቶች 600 ብር የህፃናት ማቆያ ክፍያ እንደሚፈፀምላቸው ታውቋል፡፡ ከስራ ልምምድ ስልጠናው በተጓዳኝ ገበያው ላይ ተፈላጊነታቸውን የሚያሳድጉላቸው ተያያዥ ስልጠናዎች እንደሚሰጧቸው የገለፁት አቶ ሰብሃዲን፤ ከእነዚህም ውስጥ የእርስ በእርስ መማማሪያ ዕድል፣ የህይወት ክህሎት ስልጠና እና መሠረታዊ የኮምፒዩተር ሥልጠና ይሰጣቸዋል ብለዋል፡፡

ፕሮጀክቱ ለሶስት ዓመታት የሚቆይ ሲሆን፤ በአዲስ አበባ ደረጃ 49 ሺህ ወጣቶች የሥልጠናውና የሥራ ዕድሉ ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ ታቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ተመዝግበው የህይወት ክህሎት ስልጠና ወስደዋል፣ ወደ 21 ሺህ የሚሆኑት አሁንም በህይወት ክህሎት ስልጠና ላይ ይገኛሉ ተብሏል፡፡

10 ሺህ 500 ወጣቶች በቀጥታ የሥራ ትስስር እንዲፈጠርላቸው ከተመረጡ 1 ሺህ 500 እንደ የማፋክቸሪንግ፣ የኮንስትራክሽን፣ የአገልግሎት እና መሰል ዘርፎች ላይ በተሰማሩ ድርጅቶች ውስጥ ገብተው የሥራ ልምምድ እንዲያካሄዱ እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በአዲስ አበባ ደረጃ የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክትን በ36 ወረዳዎች ለመተግበር የሚያስችል ዝግጅት ማጠናቀቁ ታውቋል፡፡ የሙያ ክህሎት የሌላቸውን ወጣቶች የክህሎት ባለቤት ለማድረግ ቢሮው በመረጣቸው ተቋማት ለ6 ወር የስራ ላይ ልምምድና ስልጠና የሚወስዱ ሲሆን፤ ፕሮጀክቱን በአለም ባንክ ድጋፍ በሀገር ዓቀፍ ደረጃ በ11 ከተሞች ተግባራዊ የሚደረግና 70 ሺህ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ተብሏል፡፡

አዲስ አበባ ከተማም በዚሁ ፕሮጀክት 49 ሺህ ወጣቶችን የክህሎት ባለቤት በማድረግ ተጠቃሚ እንደሚሆኑም አቶ ሰብሃዲን ገልፀዋል። በመጀመሪያው ምዕራፍ በተመረጡ 36 ወረዳዎች 10 ሺህ 500 ወጣቶችን በፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት ሥራ መከናወኑን ገልፀዋል፡፡

በመጀመሪያው ዙር ተጠቃሚ የሚሆኑ ወጣቶች ከነሐሴ 18 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ገብተው እየሰለጠኑ መሆኑም ተገልጿል፡፡

በተካልኝ አማረ
4.9K views09:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 12:13:55 የሕወሐት ዕብሪት ለሰላም የተዘረጉ እጆች እንዲታጠፉ እያስገደደ ነው!

መንግሥት ለሰላም አማራጭ ዕድል ለመስጠት ሲል የሕዝብ ማዕበል አስነሥቶ ሕጻናትን፣ ወጣቶችንና አረጋውያንን ለመማገድ የመጣውን የሕወሐት ታጣቂ፣ በምሥራቅ አማራ በኩል በጀግንነት ሲከላከል ቆይቷል።

ሕወሐት በምሥራቅ አማራ በኩል በቆቦና አካባቢው የከፈተው ወረራ በጀግናው የመከላከያ ሠራዊትና በደጀኑ ሕዝብ ጠንካራ የመከላከል ብቃት የተነሣ ባሰበው ልክ አልሄደለትም።

በዚህም ምክንያት ለሰላም የተሰጠውን ሁለንተናዊ አማራጭ አሽቀንጥሮ ጥሎ ወረራውን ወደ ሌሎች አካባቢዎች እያስፋፋ ይገኛል።

ያለ ጦርነት መኖር የማይችለው ሕወሐት በዋግ፣ በወልቃይት አቅጣጫና በሱዳን ድንበር አካባቢ ወረራ ከፍቷል።

ይሄንን የሕወሐት ወረራ ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት በተሟላ ዝግጅትና በጽኑ ቁመና እየተከላከለ ይገኛል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በተለያዩ አቅጣጫዎች የተከፈቱበትን ጥቃቶች በጽናት እየተከላከለ፣ አሁንም ለሰላም አማራጮች የዘረጋቸውን እጆች ዛሬም ድረስ አላጠፈም።

ለሰላም የተዘረጋው እጅ በሕወሐት ዕብሪታዊ ወረራ ምክንያት እንዳይታጠፍ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የሚቻለውን እንዲያደርግ የኢትዮጵያ መንግሥት አሁንም ያሳስባል።

ወገናችን የሆነው የትግራይ ሕዝብም ይሄንን የዕብሪት ወረራ በማውገዝ ሕወሐት ከሚያስከትልበት መከራ ራሱን ነጻ እንዲያወጣ ጥሪ እናቀርባለን።

ነሃሴ 25 ቀን 2014 ዓም አዲስ አበባ
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
4.2K viewsedited  09:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 10:39:23 የሀይማኖት መገናኛ ብዙሀን ትውልድ ግንባታ ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለጸ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ነሐሴ 25ቀን 2014 ዓ.ም

የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ጋር በመተባበር የሀይማኖት መገናኛ ብዙኃን ለአብሮነት እሴቶች መጠናከር በሚል መሪ ሀሳብ ሀገራዊ ሰላምና የአብሮነት እሴቶች ግንባታ ላይ ያተኮረ ሀገራዊ ምክክር እያደረገ ነው።


በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መሃመድ እንድሪስ ኢትዮጵያ የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን የሚኖራቸውን ሀገራዊ ፋይዳ በመረዳት ፍቃድ የሚያስገኛቸዉን አዋጅ ማዉጣታቸዉን አዉስተዉ፤ መገናኛ ብዙሀኑ የሀገር አንድነት ግንባታ ላይ አስተዋጽኦ እንዲኖራቸው ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀሀፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን ሌሎችን በማክበርና ከግጭት ቀስቃሽ ስራዎች በመቆጠብ የግብረ ገብነት ግንባታ ላይ አስተዋጽኦ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል።

በዚሁ መድረክ 23 የሃይማኖት መገናኛ ብዙሀን የምዝገባ ሰርትፍኬት የሚሰጣቸዉ ሲሆን፤ የሀይማኖት መገናኛ ብዙሀን የአብሮነት እሴቶችን በማጠናከር ዙሪያ ሊጫወቱት ስለሚገባው ሚና እና በሰላም አብሮነትና በልማት ግንባታ የሚዲያ ሚና በሚሉ ርዕሶች ዙሪያ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።

በ ዘለቃሽ ግርማ እና ሞሀመድ ፈንታዉ
ኢትዮጵያን በዘላቂነት እናልማ!

የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ!

ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ!

የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ መረጃዎችን በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ፤
በዮቱብ
https://www.youtube.com/channel/UC9lAZ1l0TvJG65R-QeCDHkg
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/Amnaddistv
በቴሌግራም
https://t.me/addismedianetwork
በትዊተር
https://twitter.com/AmnAddis
3.9K views07:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 09:43:06
የልደታ ወጣት ጥፋተኞች ማቆያ ማእከል ፕሮጀክት ግንባታው ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ነሐሴ 25ቀን 2014 ዓ.ም

የአደስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲያስገነባው የቆየው ባለ17 ብሎክ ዘመናዊው የልደታ ወጣት ጥፋተኞች ማቆያ ማእከል ፕሮጀክት ግንባታው ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን የአስተዳደሩ ከንቲባ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

ይህ አለም አቀፍ የጥፋተኞች አያያዝ መስፈርትን ያሟላና ወጣቶች ስራ ወዳድነትን እንዲሁም የስፖርትና የመዝናኛ ለወጣቶቹ ሁለንተናዊ ግንባታ የሚያግዙ ጉዳዮች የተካተቱበት ማእከል ግንባታ ከተማ አስተዳደሩ በፍጥነት ገንብቶ በማጠናቀቅ ለአግልግሎት ማብቃቱ ተመልክቷል፡፡

በአጠቃላይ 1,213.38 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፉ 2 የወንዶችና የሴቶች ስፖርትሜዳዎች ተሰርተውለታል፡፡ፕሮጀክቱ አጠቃላይ 17 ብሎኮች ሲኖሩት፤ የአስተዳደር ህንፃ፣የመማሪያ ክፍሎች፣ቤተ መፅሐፍት፣መመገቢና ማብሰያ ክፍሎች፣ክሊኒክና የምክር አገልግሎት መስጫ ክፍል፣ዎርክሾፕ፣ ፣3 የወንዶችና 2 የሴቶች ዶርሚተሪ፣ላውንደሪ፣ሁለገብ አዳራሽ እና ሌሎችም መሰረተ ልማቶች የተሙሉለት መሆኑን የጽህፈት ቤቱ መረጃ ያመለክታል፡፡


ኢትዮጵያን በዘላቂነት እናልማ!

የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ!

ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ!

የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ መረጃዎችን በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ፤
በዮቱብ
https://www.youtube.com/channel/UC9lAZ1l0TvJG65R-QeCDHkg
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/Amnaddistv
በቴሌግራም
https://t.me/addismedianetwork
በትዊተር
https://twitter.com/AmnAddis
4.3K views06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 06:09:36 የኦሪጎን የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በጥሩ ውጤት ውድድራቸውን ጀምረዋል።

አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (ኤ ኤም ኤን) ሐምሌ 09/2014 ዓ.ም

አርብ ለሊት በተደረጉ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተሳተፉባቸው የማጣሪያ ውድድሮች ሁሉም አትሌቶች ወደ ቀጣዩ ዙር ተሸጋግረዋል።

በወንዶች የ3,000 ሜትር መሠናክል የግማሽ ፍፃሜ ማጣሪያ እና የ1,500 ሜትር የሴቶች ሩብ ፍፃሜ ማጣሪያ ውድድሮች የተሳተፉ ሁሉም አትሌቶች ናቸው ወደ ፍጻሜ እና ግማሽ ፍጻሜ ማለፍ የቻሉት።

የፊታችን ሰኞ ለሚደረገው የወንዶች 3,000ሜ መሠናክል ፍፃሜ ውድድር ጌትነት ዋለ፣ ለሜቻ ግርማ እና ሀይለማርያም አማረ ተሸጋግረዋል።

ከአንደኛ ምድብ ጌትነት ዋለ 8:17.49 በሆነ ሰአት አራተኛ በመውጣት የተሻለ ሰአት በማስመዝገብ ወደ ፍፃሜው ሲያልፍ ከሁለተኛው ምድብ ለሜቻ ግርማ 8:19.64 በሆነ ሰአት አንደኛ እንዲሁ በተመሳሳይ ሶስተኛው ምድብ ላይ የተወዳደረው ሀይለማርያም አማረ 8:18.34 በሆነ ሰአት አንደኛ በመውጣት ፍፃሜውን ተላቅሏል።

በሴቶች 1500 ሜትር የማጣሪያ ውድድር የተሳተፉት ሂሩት መሸሻ፣ ፍሬወይኒ ሀይሉ እና ጉዳፍ ፀጋዬ ቅዳሜ ለሚደረገው ግማሽ ፍፃሜ ውድድር ማለፍ ችለዋል።

ከአንደኛ ምድብ ሂሩት መሸሻ 4:07.05 በሆነ ሰአት አንደኛ ስትወጣ በሶስተኛው ምድብ የተወዳደረችው ጉዳፍ ጸጋዬ 4:02.68 በሆነ ሰአት በተመሳሳይ አንደኛ በመውጣት ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅላለች።

ሁለተኛው ምድብ ላይ የተሳተፈችው ፍሬወይኒ ሃይሉ 4:04.85 በሆነ ሰአት ሦስተኛ በመውጣት ውድድሯን አጠናቃለች።

በሀዋርያው ጴጥሮስ
2.0K viewsedited  03:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 20:19:17 የክልልነት ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኙ ከመንቀሳቀስ ይልቅ ጉዳዩን የአመጽና የሁከት መነሻ ለማድረግ በሚሞክሩ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ የፌዴራል የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ

የፌዴራል የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ መንግሥት በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል በተለያዩ ጊዜያት የሚነሱ የክልልነት ጥያቄዎችን በሀገሪቱ ሕግና በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እየሠራ ይገኛል፡፡

ነገር ግን አንዳንድ አካላት ይህንን ሂደት በሚቃረን መንገድ ሕጋዊ ጥያቄዎችን ሽፋን በማድረግ ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር በህቡዕ ዝግጅት ማድረጋቸውን የጋራ ግብረ ኃይሉ ባደረገው ክትትል ስለተደረሰበት ተገቢው እርምጃ ይወስዳል፡፡

መግለጫው እንዳብራራው፤ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት በስሩ የሚገኙ ዞኖችን በአዲስ መልክ ለማዋቀር እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል፡፡ ጌዲኦም በአዲስ መልክ ከሚዋቀሩ ዞኖች አንዱ ሲሆን፤ የኅብረተሰቡን ተሳትፎ በተጨባጭ ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ ሰሞኑን የማወያያ ሰነዶች ተዘጋጅተው የዞኑ ነዋሪ እየመከረበት ይገኛል፡፡

ይሁንና የጌዲኦ ዞን የክልልነት ጥያቄ መፍትሔ የማይሰጠው ከሆን ጥያቄያችንን በኃይል እናስፈጽማለን የሚሉ አካላት በህቡዕ ተደራጅተው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን የፌዴራል የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል በተጨባጭ መረጃዎች አረጋግጧል፡፡

በህቡዕ የተደራጁት አካላት የጥፋት እቅዶቻቸውን ለማሳካት ሀሰተኛ የማህበራዊ ትስስር ገጾች በመክፈት የተዛቡና የፈጠራ መረጃዎችን እያሰራጩ መሆኑን ያመለከተው የጋራ ግብረ ኃይሉ መግለጫ፤ ማኅበረሰቡንም በተሳሳቱ መረጃዎች ለማደናገር እየሞከሩ መሆኑን ጠቁሟል፡፡

እነዚህ አካላት ያደራጇቸው ግለሠቦችና ቡድኖች ቤት ለቤት ጭምር እየተንቀሳቀሱ ቅስቀሳ እያደረጉ እንደሚገኙ ይህም በደኅንነትና በጸጥታ አካላት እንደተደረሰበት አመልክቷል፡፡

የጋራ ግብረ ኃይሉ ለዚህ እኩይ ዓላማ የተደራጁና የተሰለፉ ግለሠቦችንና ቡድኖችን በደኅንነትና በጸጥታ መዋቅሩ አማካኝነት ለይቶ ክትትል እያደረገባቸው መሆኑን በማስገንዘብ፤ ከጥፋት ተልዕኳቸውም እንዲቆጠቡ በጥብቅ ያሳስባል፡፡

ይህን ተላልፈው በሚገኙ ላይም ተገቢውን ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ያስጠነቅቃል፡፡

አብዛኛው የዞኑ ኅብረተሰብ የጥፋት ተልዕኮ ያነገቡ አካላት ህቡዕ እንቅስቃሴ ተገቢ አለመሆኑን በማመን ለጸጥታና ደኅንነት አካላት ጥቆማ በመስጠት የሁከትና ብጥብጥ ተልዕኮው እንዲከሽፍ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን የጠቆመው የጋራ ግብረ ኃይሉ መግለጫው፤ በቀጣይም ከእንደዚህ አይነት የጥፋት ሴራ እራሱን በማቀብ አጠራጣሪ ሁኔታዎችን ሲመለከት ለመንግሥት አካላት መረጃ በመስጠት የአካባቢውን ሰላም ለማረጋገጥ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጠይቋል፡፡

የፌዴራል የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል

ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም
4.3K views17:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 17:42:21 ''ኢትዮጵያ ድርቅን ለመቋቋም ከጎረቤት ሀገራት ጋር ተቀናጅታ እየሰራች ነው'' -አቶ አደም ፋራህ

አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኤ ኤም ኤን) ሀምሌ 8 ቀን 2014ዓ.ም

ኢትዮጵያ ድርቅን ለመቋቋም ከጎረቤት ሀገራት ጋር ተቀናጅታ እየሰራች መሆኗን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሮዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለፁ።

ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሚስ ሃና ቴተህን ጋር በክልላዊና አገር አቀፋ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡

በውይይቱ ወቅት በአፍሪካ ቀንድ በአየር ንብረት መዛባት ምክንያት ያጋጠመዉን ድርቅ ለመቋቋም ኢትዮጵያ በሀገር ውስጥ እየተገበረች ያለውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በማስፋት ዕቅድ አዉጥታ ከጎረቤት አገሮች ጋር በመቀናጀት እየሰራች መሆኑን አቶ አደም ገልፀዋል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለዚህ የኢትዮጵያ እቅድ ድጋፍ እንዲያደርግም ጠይቀዋል፡፡

በትግራይ ክልል የተፈጠረዉን ግጭት በሠላማዊ መንገድ ለመፍታት በብልጽግና ፓርቲ የሚመራው መንግስት ዝግጁ መሆኑን ያመለከቱት ምክትል ፕሬዝዳንቱ በመንግስት በኩል እስካሁን የተደረጉ ጥረቶችንና የሰላም አማራጩ እውን እንዲሆን የተወሰዱ ርምጃዎችን ለልዩ መልዕክተኛዋ አብራርተዋል፡፡

መንግስት የህወሓትን ዓላማ ለማስፈፀም ሲንቀሳቀሱ ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የነበሩ እስረኞችን መፍታቱ፣ ለሰብዓዊነት ሲባል የጊዜ ገደብ የሌለው የግጭት ማቆም ተግባራዊ መደረጉ፣ አካታች ሀገራዊ ምክክር ለማድረግ ዝግጅት መጀመሩ፤ በአፍሪካ ህብረት ልዩ መልዕክተኛና የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ለሚመራዉ የሠላም ሂደት መንግስት ሙሉ ድጋፍ ማድረጉ ለሰላም አማራጩ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር የተወሰዱ እርምጃዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

የብልጽግና ፓርቲ የስራ አስፈጻሚ እና ማዕከላዊ ኮሚቴዎች በጉዳዩ ላይ በዝርዝር ተወያይተው ሕገ መንግስታዊነትንና ሀገራዊ ጥቅምን ባስከበረና በአፍሪካ ሕብረት የተመራ የሰላም አማራጭ መከተል እንደሚገባ አቅጣጫ በማስቀመጥ ለተግባራዊነቱም ርብርብ እንዲደረግ መወሳናቸውንም አብራርተውላቸዋል፡፡

ሌላኛዉ ወገንም የሠላም አማራጭን እንዲጠቀም የተባበሩት መንግስታት ግፊት ማድረግ እንደሚገባውም አቶ አደም አንስተዋል፡፡

ልዩ መልዕክተኛ ሚስ ሃና ቴተህ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ ጋር በመቀናጀት ድርቁን ለመቋቋም የምታደርገዉን ጥረት በማድነቅ የተባበሩት መንግስታት አስፈላጊዉን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ዋና ተልዕኮ ሠላም መገንባት በመሆኑ ተጨባጭ መረጃዎችን ለድርጅቱ በማቅረብ የሠላም ጥረቱን እንደሚደግፉ ሚስ ቴተህ መግለፃቸውን ከብልጽግና ፓርቲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
4.7K views14:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ