Get Mystery Box with random crypto!

Natnael Mekonnen

የሰርጥ አድራሻ: @natnaelmekonnen21
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 173.42K
የሰርጥ መግለጫ

በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ሲፈልጉና ማስታወቂያ ማሰራት ከፈለጉ 👉 @NatnaelMekonnen7
Facebook.com/natnaelmekonnen.et
Instagram.com/natnaelmekonnen21

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 14

2024-04-11 00:12:00 በአቋም ለሀገር መቆም Etv | Ethiopia | News zena


30.3K views21:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-10 19:40:45
የጽንፈኛው ኦነግ/ሸኔ ሽብር ቡድን ጸሃይ እየጠለቀች ነው::

በኦሮሚያ ክልል በቅርቡ በፀጥታ ሃይሎች በተወሰደው የህግ ማስከበር ዘመቻ እርምጃ በአሸባሪው የኦነግ/ሸኔ ቡድን ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን ሰሞኑን 110 አሸባሪዎች በመንግስት ጥሪ እጃቸውን የሰጡ ሲሆን 89 ሰዎች ደግሞ በቁጥጥር ስር ውለዋል:: በዚህ ወር ብቻ በኦሮሚያ ክልል በተደረገው ህግን የማስከበር ዘመቻ ባጠቃላይ በድምሩ 2237 የሚሆኑት የሽብርተኛው ኦነግ/ሸኔ ቡድን በቁጥጥር ስር ውለዋል።
34.5K views16:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 08:34:30 በኦሮሚያ ክልል ኦነግ ሸኔ ላይ እርምጃ ቀጥሏል

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ሲቡ ሲሬ፣ሌቃ ዱለቻ እና ጅማ አርጆ ወረዳዎች 71 የጽንፈኛው ኦነግ ሸኔ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው እጅ ሰጥተዋል።
13.1K viewsedited  05:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 07:44:57 SECURITY ALERT FOR U.S. CITIZENS

The U.S. Embassy in Nairobi has received information about threats to multiple locations in Mogadishu, including Aden Adde International Airport in Mogadishu. All movements of U.S. Embassy personnel have been canceled for Tuesday, April 9, 2024.

The U.S. Embassy in Somalia reminds U.S. citizens that terrorists continue to plot kidnappings, bombings, and other attacks in Somalia. They may conduct attacks with little or no warning, targeting airports and seaports, checkpoints, government buildings, hotels, restaurants, shopping areas, and other areas where large crowds gather and Westerners frequent, as well as government, military, and Western convoys. https://so.usembassy.gov/security-alert-for-u-s-citizens-april-8-2024/#:~:text=The%20U.S.%20Department%20of%20State,issues%2C%20kidnapping%2C%20and%20piracy
15.0K views04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 07:44:47
ELEGAS ENGINEERING PLC
የእርስዎ አሳንሰር መፍትሄ ባለሙያዎች

ለ Elevator እና ለEscalator ከፍተኛ ደረጃ የምህንድስና መፍትሄዎች ያስፈልጎዎታል? በኢንዱስትሪው ውስጥ ግንባር ቀደም ኩባንያ ከሆነው ELEGAS ኢንጂነሪንግ አለሎት። ባለን ሰፊ ልምድ እና እውቀት ላለፉት 17 አመታት በአስራ በአምስት ሀገራት በልዩ ጥራተ‍እ አገልግሎት ስናቀርብ ቆይተናል። አሁን ደግሞ ላለፉት ሁለት ዓመታት የአገር ውስጥ ገበያን እያገለገለ አዲሱን የግንባር መስሪያ ቤታችን በኢትዮጵያ መከፈቱን በደስታእንገልፃለን።
በ ELEGAS ምህንድስና፣ ልዩ ፍላጎቶችዎን ለማሟላት የተዘጋጁ ምርጥ የምህንድስና መፍትሄዎችን በማቅረበ‍ኣችን እንኮራለን። የድርጅታችን ባለ ሞያዎች በምንሰራው እያንዳንዱ ፕሮጀክት የላቀ ጥራት ለማቅረብ ቁርጠኛ ናቸው።

ሚለየን ምንድነው?

የገጠማ ስራን ጨምሮ በአራት ወራት ውስጥ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን አሳንሰሮች ከቱርክ የማድረስ ችሎታችን። ጊዜ ወሳኝ ነዋ

በተጨማሪም ከእያንዳንዱ ሊፍት ግዢ ጋር ጥቅል እናቀርባለን። በምርቶቻችን ላይ ለጋስ የሁለት ዓመት ዋስትና ያገኛሉ። በተጨማሪም የአሳንሰርህን ረጅም ዕድሜ እና ጥሩ አፈጻጸም ለማረጋገጥ የአንድ አመት ነጻ ጥገና እናቀርባለን።

የዋጋ አወጣጥን በተመለከተ፣ የፕሮጀክትዎን ፍላጎት የሚያሟላ ተለዋዋጭነት እናቀርባለን።

FOB፣ CIF፣ ወይም DDP፣ የዋጋ አወጣጥ አማራጮቻችንን ከተወሰኑ መስፈርቶች ጋር በማዛመድ እናዘጋጃለን።

ገጠማ የሚደርጉላችሁ የበርካታ
አመታት ከቱርክ የመጡ ልምድ ያላቸው crewዎች ናቸው።

We Care

አድራሻ:- ቡልጋሪያ ማዞሪያ የትራፊክ መብራት አጠገብ አዌባነ ህንፃ 1ኛ ፎቅ


+251 971 71 71 71
+251 994 69 69 69

www.elegas.com.tr

Email:- ethiopia@elegas.com.tr
13.5K views04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 18:48:36
የመጋቢት ፍሬዎች

አገራዊ ለውጡን እንደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅመው በለውጡ የተለውጡ ጠንካራ ተቋማት አሉ፡፡ የአገራዊ ለውጡ አንዱ ፍሬ ይህ ነው፡፡ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ለዚህ ማሳያ የሚሆን ተቋም ነው፡፡ ተቋሙ በለውጡ ብቻ በ6 ዓመታት ብቻ ከ 100 ቢሊየን ብር በላይ ተጨማሪ ሐብት መፍጠር የቻለ ነው፡፡

የኮንስትራክሽ ዘርፉን በማናቃቃትና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በማስታዋወቅ እና የሬልስቴት ገበያው ይታይበት የነበረውን ያልተረጋጋ የገበያ ሁኔታና የዋጋ ጭማሪ በማረጋገት የራሱን ሚና እየተጫወተ ነው፡፡ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እንደ ደቡብ ኮሪያና ሲንጋፖር የመሰሉ አገራት ያሏቸውን መንግስታዊ ቅርጽ የተላበሱ የሬል-ስቴት ተቋማት ጋር ተመሳሳይነት ባላው መልኩ፡- እራሱን በዘመናዊ መንገድ እያደረጃ ያለና ፍጹም ኢትዮጵዊነትና የአገር ፍቅር ጎልቶ ከሚታይባቸው ተቋማት መካከል የሚጠቀስ ነው፡፡ ተቋሙ ከነበረበት እጅግ ውስብስብ ችግር አንጻር ይለወጣል ብሎም የገመተ የነበረ ባይኖርም የመጋቢት ፍሬነቱን በተግባር እያረጋጋጠ ያለ ስኬታማ ተቋም ሆኖ ቀጥሏል፡፡
24.1K views15:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 17:27:37
ክፍለጦሮች በአሸባሪው ኦነግ ሸኔ ላይ የሚወስዱትን እርምጃ አጠናክረው መቀጠላቸው ተገለፀ።

በምስራቅ ወለጋ ዞን በዲጋ ወረዳ የማዕከላዊ ዕዝ አንድ ክፍለጦር በአሸባሪው ኦነግ ሸኔ ላይ ሰሞኑን ባደረገው የተቀናጀ ኦፕሬሸን የሸኔ ቡድን መደምሰሱን የክፍለጦሩ አዛዥ ሌተናል ኮሎኔል ታደሰ እንዳለው ገልፀዋል።

የህዝብን ሠላም መንሳት አላማው አድርጎ የሚንቀሳቀሰው አሸባሪው ኦነግ ሸኔ በማህበረሰቡ ላይ የሚያደርሰውን ጥቃት ለማስቆምና ቡድኑን ሙሉ በሙሉ በማጥፋት የሃገሩን ሰላም ለማረጋገጥ ክፍለጦሩ ተልዕኮውን በድል አድራጊነት ቀጥሏል ሲሉ አዛዡ ተናግረዋል።

ክፍለጦሩ ሰሞኑን በጠላት ላይ በወሰደው እርምጃ የሽብር ቡድኑ ለጥፋት ተግባሩ ይጠቀምበት የነበረውን  ብሬን ፣ ክላሽ ፣ የክላሽ መጋዘን ፣የብሬን ጥይት ፣ ቦንብ፣ የክላሽ ጥይት ፣ሽጉጥና የተለያዩ መድሃኒቶችን በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን ሌተናል ኮሎኔል ታደሰ እንዳለው አሳውቀዋል።

በተመሳሳይ በሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን በሀባቦ ወረዳ እየተንቀሳቀሰ ህብረተሰቡን ለስቃይ እና ለእንግልት ሲዳርግ እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ሲዘርፍ እና ሲያቃጥል የቆየዉ አሸባሪዉ የሸኔ ቡድን ክፍለ ጦሩ በሚወስደው የተቀናጀ እርምጃ እጅ እየሠጠ ይገኛል።

እጃቸውን ለሰራዊቱ  ከሰጡት መካከል ለሊሳ ዋሚ ላለፉት አመታት በሽብር ቡድኑ በቆየሁበት ጊዜ ህብረተሰቡን በማሠቃየት በዘረፋ ላይ ተሰማርቸ ነበር ግን ትክክል አልነበርኩም አሁን ወደ ሠላም ተመልሻለሁ ብሏል።

የአካባቢዉ ነዋሪዎች የሽብር ቡድኑ አባላት በሰላማዊ መንገድ ለመከላከያ ሰራዊቱ እጅ መስጠታቸውን እንዲቀጥሉበትና በአካባቢውም የልማት ሥራ እንዲሠራ ሃሳብ ሰጥተዋል።
25.6K views14:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 17:18:29
ወጣት ሶፎኒያስ አስራትን ገድለው ተሽከርካሪውን ዘርፈው የተሰወሩ ማንነታቸው ያልታወቁ ወንጀል ፈፃሚዎችን በ48 ሰዓት ውስጥ ከዘረፉት ተሽከርካሪ ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ ወንጀሉን የፈፀሙ አካላትን ለመቆጣጠር የምርመራና የክትትል ቡድኑ ሌት ከቀን በመስራት ውጤት ማምጣቱ ገልፆል፡፡

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ አካባቢ ወደ አቦ ቤተ-ክርስቲያን በሚወስደው መንገድ ላይ ወጣት ሶፎኒያስ አስራት ተገድሎ ይገኛል፡፡

የወጣቱ መገደል ሪፖርት የደረሰው አዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል ምርመራና የክትትል ቡድኖችን በማዋቀር የገዳዮቹን ማንነት በማወቅ ወንጀለኞቹን ህግ ፊት ለማቅረብ ወደ ስራ ይገባል፡፡
ሟች ወጣት ሶፎኒያስ መጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ/ም ከንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ናሆም ሆቴል አካባቢ ከሌሊቱ 8፡00 ሰዓት ላይ ማንነታቸው የማይታወቁ ሦስት ግለሰቦችን አሳፍሮ ወደ ቦሌ ሚካኤል ለማድርስ መሄዱን ጉዳዩን ለመከታተል የተቋቋመው የምርመራና የክትትል ቡድን አባላት ባደረጉት ክትትል ያረጋግጣሉ፡፡
ወንጀል ፈፃሚዎቹ ወንጀል ለመፈፀም አቅደው እና ተደራጅተው የትራንስፖርት አገልግሎት ፈላጊ መስለው ሹፌሩን በመቅረብ ከተሳፈሩ በኋላ አንገቱን በገመድ አንቀው በመግደል አስክሬኑን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ አካባቢ ወደ አቦ ቤተክርስቲያን በሚወስደው መንገድ ላይ በመጣል አይነቷ ቪትዝ የሴሌዳ ቁጥር ኮድ 2A 93488 ተሽከርካሪ ጨምሮ ሁለት ሞባይል ስልኮችን ዘርፈው ይሰወራሉ፡፡

ፖሊስ ሌት ተቀን ባደረገው ብርቱ ክትትል ልዩ ልዩ ፖሊሳዊ ቴክኒኮችን በመጠቀም ወንጀል ፈፃሚዎቹ የሰረቁትን ተሽከርካሪ ለመሸጥ እየተስማሙ መሆኑን በበቂ ማስረጃ ካረጋገጠ በሗላ ክትትሉን በመቀጠል ሦስቱን ዋና ወንጀል ፈፃሚዎች የሰረቁትን መኪና በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ለመሸጥ እየተደራደሩ እንዳለ በቁጥጥር ስር በማዋል የተሰረቀችውን መኪና ፣ ሁለት ሞባይል ስልኮችን ልዩ ልዩ ኤግዚቢቶችን ይዞ ምርመራውን መቀጠሉን ጨምሮ ገልፆል፡፡ ፖሊስ ባደረገው ክትትልና ምርመራ ማንነታቸው የማይታወቁ ወንጀል ፈፃሚዎችን በ48 ሰዓት ጊዜ ውስጥ በመለየት ሦስት ዋና ወንጀል ፈፃሚዎችንና ሦስት ግብራበሮቻቸውን በቁጥጥር ስር ማዋሉ ታውቋል፡፡

በመጨረሻም ለዚህ ስራ ስኬታማነት ቀና ትብብር ላደረጉ አካላት አዲስ አበባ ፖሊስ ምስጋናውን እያቀረበ የሜትር ታክሲ አገልግሎት የጥሪ ማዕከል ቁጥሮችን ሳይጠቀሙ አገልግሎት መስጠት ሆነ መቀበል እንዲሁም ከሚታወቀው የአገልግሎት አሰጣጥ ውጭ በዋጋ ድርድር የሚሰጥ የትራንስፖርት ግልጋሎት ለእንዲህ አይነት ወንጀል እየዳረገ ስለሆነ ተሳፋሪዎች ሆኑ አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ ፖሊስ መልእክቱን አስተላልፏል፡የምርመራ ሥራው እንዳበቃ የፍርድ ሂደት ውጤቱን በቀጣይ ለህዝብ እንደሚገለፅ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል ፡፡
21.2K views14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 14:53:09
በታላቅ ድምቀት የተከበረው የ2017 ዓ/ም የሲዳማ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ ፊቼ ጨምበላላ በዓል በሰላም መጠናቀቁን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ የበዓሉን ፍፃሜ አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ህብረተሰቡና ፖሊስ በጋራ ተቀናጅተው መስራት በመቻላቸው በዓሉ በሰላም ተከብሮ መጠናቀቁን ገልፀዋል።

በዓሉ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ኃላፊነት ለተወጡ ለሁሉም የክልሉ ህዝብ፣ ሌት ከቀን ደከመን ሰለቸን ሳይሉ የፀጥታውን ስራ ላከናወኑ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ ለፌደራል ፖሊስ፣ ለክልሉ ፖሊስ አመራርና አባላት እንዲሁም ለአጋዥ የፀጥታ ሀይሎች በኮሚሽኑ ስም ምስጋናቸውን ያቀረቡት ኮሚሽነሩ በቀጣይም በክልሉ ሁሉም ዞንና ወረዳዎች በዓሉ ቀጥሎ የሚከበር በመሆኑ የተለመደዉን ሰላም የማስጠበቅ ስራ በቅንጅት በመስራት ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
23.4K views11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 11:02:39
ትኩረት ለወላጅ አልባ ህፃናት

ሃሳቡ የተፀነሰው ከ6 ዓመታት በፊት ነው። መቅደስ የልጆች አድማስ ሙሉ በሙሉ አገር በቀል የሆነና በአርቲስት መቅደስ ፀጋዬ @mekdes_tsegaye_official የተመሰረተ የበጎ አድራጎት ድርጅት ነው::

ድርጅቱን ሙሉ ለሙሉ በመገንባትና በሙሉ አቅሙ ስራውን እንዲጀምር ለማድረግ እስከ አንድ ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ መሆኑን የገለፀችው አርቲስት መቅደስ በመጀመሪያው ዙር 200 ህፃናትን ከመላው ኢትዮጵያ እንደሚቀበል ተነግራለች።

ልዩ ትኩረት እና ጥበቃ ለሚያስፈልጋቸው ወላጅ አልባ ህፃናት ሁሉን አቀፍ እንክብካቤ በመስጠት በቀጣይ የሕይወት ጉዟቸው ስኬታማ እንዲሆኑ ለማድረግ ትኩረቱን አድርጎ የሚሰራ የበጎ አድራጎት ማዕከል እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ በተሰማሩ ተፅእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች በቦርድ አባልነት ተሰይመዋል፡፡ .

ያልተከፈለ ብዙ እዳ አለብኝ በማለት ህልሟን ይዛ ወደ ህዝብ የመጣችው አርቲስት መቅደስ፣ ማእከሉን እውን ለማድረግ ይፋ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብር በሳምንቱ መገባደጃ በስካይ ላይት ሆቴል አስጀምራለች።
25.1K views08:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ