2023-05-08 14:51:56
"ርዕሰ አንቀጽ"
"…የዐማራ ክልልን በተመለከተ ተደጋግሞ የሚነሣ ነገር አለ። ያም ምንድነው ያልን እንደሆነ "የዐማራ ክልል መሪዎች ለምንድነው በሚመሩት ሕዝብ ላይ ጨካኝ፣ አረመኔ የሆኑት? ለምንድነው እንደ ኦሮሞ፣ እንደ ትግሬና ደቡብ ወንድሞቻቸው ቢያንስ ከሌላ ነገድ ተወልደውም እንኳ ቢሆን መሪ ሆነው ለተሾሙበት ለዐማራ ነገድ ጥብቅና የማይቆሙት? ለሰላሙ፣ ዲሞክራሲና ለልማቱ የማይተጉት? ለምንድነው ሌሎቹ ለሚመሩት ሕዝብ ሽንጣቸውን ገትረው እንደሚሟሟቱት፣ እንደሚሟገቱት የዐማራዎቹም የማይሟገቱት ብለው ሲጠይቁ ይደመጣል። ለዚህ ጉዳይ መልስ ለመስጠት የበኩሌን ሚጢጢ ሃሳብ ለመሸጥ ነው በርዕሰ አንቀጽ የመጣሁት።
"…እውነት ነው ለምሳሌ አቢይ አህመድ የወሎ ዐማራ ነው ኦሮሞነትን በኦሮሞ ምድር ላይ በመወለዱ እና ኦሮሚኛ ቋንቋ በመናገሩ ብቻ ኦሮሞነትን የተቀበለ የዐማራ ሰው ነው። መለስ ዜናዊ ኤርትግ፣ ስብሐት ነጋ ኤርትግ፣ ቴዎድሮስ አድሓኖም፣ ኬሪያ ኢብራሂም ወዘተ ኤርትግ ናቸው። ገብሩ አሥራት፣ ጌታቸው ረዳ ወዘተ ዐማትግ ናቸው። ነገር ግን እነዚህ ግለሰቦች በተሾሙበት ክልል ለተሾሙበት ሕዝብ እጅግ ሲበዛ ታማኝ ደማቸውን የሚሰጡ፣ የሰጡም እስከሞትም የታመኑ ናቸው።
"…ወደ ዐማራ ክልል ስንመጣ ግን የተለየ ጠባይ፣ የተለየ ማንነት፣ የተለየ ስብዕና ነው የምናገኘው። ክልሉ በራሱ እንዲቆም አይፈለግም። ክልሉ ውስጥ የሚኖረው የዐማራ ነገድ በክልሉ የሥልጣን እርከን ስፍራም የለው። የክልሉ የዐማራ አመራሮች ቀደም ሲል በሕወሓት በጥንቃቄ ተመርጠው የተፈጠሩ፣ የተሠሩ ናቸው። ብልፅግናም ያንኑ የህወሓትን ፖሊሲ ነው ያስቀጠለው። ሕዝባቸውን የሚፀየፉ፣ በመረረ ጣላቻም የተሞሉ፣ ሊበቀሉት የሚፈልጉትን ሕዝብ የሚመሩ ናቸው በወረንጦ ተለቅመው እንዲመሩት የሚደረጉት። ምሳሌም እናንሳ ብዙዎች እንደሚሉት፦
"…አገኘሁ ተሻገር (የቅማንት ዐማራ ማንነት ያለው) ሰካራም በትግሬ የተመረጠ፣ በመለስዜናዊ በበረከት ስምኦን የተመለመለ ነው ይሉታል። ተመስገን ጥሩነህ፣ ሰማ ጥሩነህ፣ ኢንጂነር ሀብታሙ፣ ይልቃል ከፍአለ የጎጃም አገው ሸንጎ አባላት ሲሆኑ ጄነራል አበባው ታደሰ ደግሞ በአባቱ የሀውዜን ትግሬና በእናቱ የዋግኽምራ አገው ሸንጎ አባል ነው ይሉታል። ደመቀ መኮንን ምንጩ የባሌ ኦሮሞ ሲሆን ወሎ ተወልዶ በ77 ድርቅ ቤተሰቡ ቻግኒ ጎጃም ያደገ ነው ይባላል። መለስ ዜናዊና በረከት ስምኦን እጅግ የደከሙበት የእንግሊዝ የስለላ ድርጅት ከቦታው ንቅንቅ እንዲል የማይፈልገው ሰው ነው ይሉታል። እስላም ሆኖ ያውም ፅንፈኛ ዐማራ ጠል እስላም። እነዚህ ሰዎች ሙሉ ዐማራ ያለመሆናቸው ችግር የለውም ምክንያቱም ሌሎቹም እንዲሁ ናቸውና። በኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ ንፁሕ ሌላ ዘር ያልተቀላቀለብኝ ነኝ የሚል የለም። ሆኖም ግን ሌሎቹ ለተሾሙበት ክልል ሕዝብ ሟች ሲሆኑ እነዚህ ለምን ገዳይ ሆኑ? ነው ጥያቄው።
"…እነዚህ የዐማራ ሕዝብ ገዢዎች የራሳቸውን የሆነ ወሳኝ ኔትወርክ ፈጥረውም ነው ዐማራውን ቀፍድደው የያዙት። ከባዱ ነገር ይሄን ኔትወርክ ማፈራረሱ ላይ ነው። የዞን፣ የወረዳ፣ በቀበሌ ስምሪት፣ በፖሊስ ተቋማት፣ በተለይ ደግሞ በዞንና በወረዳ ወሳኙ ስፍራ ከዚያም ወረድ ሲል በቀበሌ በሚገኙ ማዘዣ ጣቢያዎች፣ ከፍ ሲል በልዩ ኃይል እና በአድማ ብተና፣ በዞን፣ በወረዳና በቀበሌ ካቢኔ ውስጥ በቀጥታ የመሳተፍ እና የማዘዙን ሥልጣን የተቆጣጠሩት እነዚህ ኃይሎች ናቸው። አሁን ከቀበሌ እስከ ክልል ወሳኙን የዐማራ የሥልጣን እርከን በብዛት እንዲቆጣጠሩ የተደረጉት እነዚህ በዐማራ ጥላቻ ያበዱ፣ ዐማራ ማንነት እንዲጠፋ፣ ክልሉም ፍርስርሱ እንዲወጣ በሚተጉ በደም ማንነታቸው የቅማንት፣ የአገው ሸንጎ፣ የከሚሴ ኦሮሞ እና የአርጎባ ተወላጅ የሆኑ ግለሰቦች ናቸው። እነዚህ አካላት በአሁኑ ጊዜ በክልሉ የፀጥታና የፖሊስ ተቋማት ውስጥ ወሳኞቹ አካላት ናቸው።
"…እንደ ድንገት በእነዚህ ተቋማት ውስጥ የገቡ ዐማሮች ከተገኙ በፍጥነት ነው እርምጃ የሚወሰድባቸው። ሳይታወቁ፣ የደም ማንነታቸው ሳይጣራ ተሽሎክሉከው አልፈው ሥልጣን የሚይዙ ካሉም በዲሞክራትነታቸው፣ በእኩልነት፣ በፍትሕ አቀንቃኝነታቸው ወዲያው ይታወቃሉ። ዐማራ ክልል ላይ ሆኖ ስለክልሉ መበደል፣ መጨቆን፣ ስለ ሕዝቡ መፈናቀል፣ መሰደድ፣ መገረፍ፣ መታረድ መናገር የጀምር ሰው ያኔ ዐማራ መሆኑ ይታወቃል። ዶር አምባቸው፣ ምግባሩ ከበደ፣ አቶ እዘዝ ዋሴ፣ ጄነራል አሳምነው ጽጌ ሰለባ የሆኑት በእነዚሁ የዐማራ ማንነት በሌላቸው ቀድሞ በህወሓትና ኋላ በአዲሱ ባርያ አሳዳሪያቸው በኦህዴድ ኦነግ አማካኝነት በተሾሙ ፀረ ዐማራ ኃይሎች ነው።
"…ለዚህ ነው አገኘሁ ተሻገር እንደፈለገ ሰክሮ፣ ሰርቆ፣ ቀባጥሮ የማይነካው። ገና ክልሉ ያለቅጥ ሰፍቷል ተብሎ 8 ቦታ ሊሸነሽኑት መሆኑን ስትሰሙ ደግሞ ጉድ ትላላችሁ። ሲጠቃለል ዐማራ ትግሉን ከባድ የሚያደርግበት ይሄ ነው። ዐማራን የሚያሸንፈውም፣ የሚፈታተነውም ለዘመናት በተሠራበት መዋቅራዊ አስተዳደራዊ ሴራ ምክንያት ነው። ዐማራ ትግሉን ፈታኝ የሚያደርግበት ይሄን የሴራ መስመር በጸሎትም፣ በዱአም፣ በጉልበትም ቢሆን በጥበብ በጣጥሶ የራሱን የጸጥታ መዋቅር መዘርጋት ሲችል ብቻ ነው። ሌላው ቢቀር ፓርላማ ተመርጠው የሚገቡት እንኳ ለምሳሌ እንደ ዶር ሂሩት ካሰው አይነቷ በግልፅ "ዐማራ ጨቋኝ ነበረ" ብላ ዐማራውን ምረጠኝ ብላ የምረጡኝ ቅስቀሳም አድርጋ ጨቋኙ ዐማራም በደቡብ ጎንደር መርጧት የአበባ ምንጣፍ ተነጥፎላት ጨቋኙን ዐማራ ወክላ ፓርላማ የገባች ሴት ናት። ፓርላማ ገብተው ስለ ዐማራ መጨቆን የሚተነፍስ ሰው ካገኛችሁ እሱ በደም ማንነቱ ዐማራ ነው። ዝም፣ ጭጭ፣ የሚሉት በሙሉ ግን በጥንቃቄ ተመርጠው የዐማራን መጥፋት፣ የክልሉን መፍረስ፣ መድቀቅ፣ መበተን የሚፈልጉ አማርኛ ተናጋሪ ኃይላት ናቸው የሚሉ መተርጉማን አሉ።
"…እንግዲህ ይሄን ዐማሮች ሲያዩት ከባድ ነገር ግን ደግሞ ወስኖ ካመረረ፣ ጥርሱንም ነክሶ ቆርጦ ከታገለ ኢምንት የሆነ ሴራ ለመበጣጠስ ቀናትም አይፈጅበትም። በአንድ ጎን እያመረተ፣ ሌላውንም እየመከተ በሌላ ጎን ደግሞ ውስጡን እያጠራ መታገል ከጀመረ ድል አፍንጫው ስር ነው የምትንከላወሰው። ቢያንስ እነዚህ ፀረ ዐማራ የዐማራ ሹመኞች እንደ ትግሬና ኦሮሞ ሹመኞች ከነገዱ ባይወለዱ እንኳ እንደእነሱ ለሚመሩት ሕዝብ እንዲጨነቁ ማድረግ ተገቢ ነው። ሙፈሪያት ካሚል እንኳ ግማሽ የጅማ ኦሮሞ ሆና ለስልጤ ደሟን የምትሰጥ መሆኗን እነ ሂሩት ካሰው ቢረዱ መልካም ነው እላለሁ። እኔ የምጽፈው ጦማር ይመራል ነገር ግን ምንም ማድረግ አልችልም። ፈርዶብኝ ነው። እኔ አይስክሬም ብቻ አይደለም የምሸጠው። ኮሶ፣ እንቆቆ፣ ግራዋም፣ እሬትም እሸጣለው። ለወያኔና ለኦነግ ሰዎች ደግሞ በረኪናና የአይጥ መርዝ በስፋት አቀርባለሁ። 1 ሜትር ገመድም በተመጣጣኝ ዋጋ አቀርብላቸዋለሁ። ታነቅ…
"…ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ… አሸበርቲው።
5.8K views11:51