Get Mystery Box with random crypto!

ዘመድኩን በቀለ(ነጭነጯን)

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkunbekele3 — ዘመድኩን በቀለ(ነጭነጯን)
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemedkunbekele3 — ዘመድኩን በቀለ(ነጭነጯን)
የሰርጥ አድራሻ: @zemedkunbekele3
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 15.85K
የሰርጥ መግለጫ

እንደ ፌስቡክ፣ እንደ ዩቲቡ ሁሉ በዚህ መንደርም ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክ ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-07-05 20:55:50
"…የአይጥ ምስክሯ…

"…ኦቦ ተስፋዬ ይሄ አምቡላ መጋፊያ አረቄ ቤት አይደለም። እንከባበር። ይሄ የጋራ ሃይማኖታችን የከበረ የቅድስና ሥነ ሥርዓት የሚፈጸምበት ሃይማኖታዊ ጉዳይ ነው። ተጣድፎ ምስክርነትህን እዚያው በጃምቦ ቤት አድርገው። ምዕራብ አሩሲ አለፈላት ይላል እንዴ ደግሞ እንዲያውም ጉድ ፈላባት በል እንጂ አባው።

"…በዚህ የማይረባ የጎጥ ኔትወርክ ውስጥ ያላችሁ በሙሉ በሙሉ ከሀ እስከ ፐ የቅርብ ሰዎቼንም ሆነ የሩቅ ወዳጆቼን በሙሉ በአስቸኳይ አቁሙ። እኔ ዘመዴ አልፋታችሁም። ሸዋን በዚህ መልክ አትጠቅሙትም። ሸዋም በዚህ መልክ አይከብርም። ሌሎች ሰዎች ጠፍተው ነው…?

"…ምንአልባትም የማከብርዎት አረጋዊው ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስም በዚህ ጉዳይ ቢተዉ ነው የሚሻለው። ኧረ ደስ አይልም በማርያም። ገና ለገና… ብቻ ደስ አይልም። በቃ መጠጡ ነው ችግሩ እሱን እንዲተው እንመክረዋልን ይለኛል እንዴ በማርያም። አዛረ ምን ጉድ ነው።

"…ደጀኔ ቶላም በማኅበራዊ ሚድያው ላይ የማኅበረ ቅዱሳን አንዳንድ የሸዋ ጎጠኞች፣ እንደ ተስፋዬ ሞሲሳ ዓይነት የአምቡላ ጋን ስር ሰባኪዎች በየፌስቡኩ ስለመሰከሩ፣ ስለተጯጯሁልህ እንዳትኮፈስ። አይገባኝም አይሆንም በል። ይሄን ስታይ ቢያንስ የቀሲስ አብርሃምስ እህት ምን ትላለች አይባልም እንዴ…?  ቀሲስ በላይ መኮንንም እኮ የ3 ልጆች አባት ነው። እንዲያ ከሆነ እሱስ የማይሾም ለምንድነው…?

• አባ ሩፋኤል
• አባ ሕርያቆስ
• አባ ሳዊሮስ
• እና ሌሎችም በዚህ ጉዳይ ላይ ወጥራችሁ ከሸዋ ጳጳስ መብዛት አለበት ብላችሁ የተሳተፋችሁ በሙሉ በየሄዳችሁበት አንገታችሁን ከመድፋታችሁ በፊት በቶሎ ነገርየውን አስተካክሉ። ሌሎቹም ላይ እንዲሁ እቀጥላለሁ።

• ወይ ምስክርነት መች በፍሬንድስነት ሆነና…? ሃኣ…!
2.4K views17:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 21:38:20
“አዳሜና ሔዋኔ ሆይ…!

"…ብር ቆጥቡ፣ በባንክ ማስቀመጥ ልመዱ የሚባለው እኮ ዝም ብሎ ለላንቲካ አይደለም። በደስታችሁ ጊዜ እንዲህ አውጥታችሁ እንደፈለጋችሁ ትበትኑት ዘንድ ነው። ብር እንዲህ የሚረገጠው፣ የሚዘራው በደንብ የባንክ ደንበኛ ሲኮን ነው። ባንክ ቤት ደንበኛ የሆነ ሰው እንዲህ በብር የመጫወት መብትም አቅምም አለው።

"…አሁንም አልረፈደም ሁላችሁም ፍጠኑ። ባንክ ቤትን እንደ ሸኔ ደጋግማችሁ ጎብኙ፣ ሥራ የለም፣ ገቢ ጠፍቷል፣ ብር ማግኘት አልተቻለንም ምናምን እያላችሁ ደግሞስ ምኑን እንቆጥብ እያላችሁ አታለቃቅሱ። አታላዝኑ። የጫካውን ሸኔ ተመልከቱ እንጂ። አያርሱ፣ አይዘሩ፣ አይቆፍሩ… እና ከየት አመጡ ልትሉ ነው…?

"…ደግሞ ይሄን እንደ አበባ፣ እንደ ፈንዲሻም የተበተነ የተዘራም ብር አይተህ በቄሮ ከባንክ ተዘርፎ፣ ሸኔም ሰው አግቶ የተገኘ የደም ገንዘብ ነው ብላብላ እያልላክ እኚኚኚኚ በልብኝ አሉህ። እኚኚብላ ሁላ… ቲሽ…

• በሉ እየተዘረፋችሁ…!
3.9K views18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 20:41:41
ማስታወሻ…!

፩ኛ፦ ቲክቶክ ደግሞ ምን እንደነካው አላውቅም Live እንዳልገባ መልሶ ከልክሎኛል። ያው የፈረደበት ዲያቆን አማኑኤል ተጨቃጭቆ እስኪያስለቅቀኝ ድረስ ለዛሬ በቲክቶክ መንደር ሚሊዮኖች በጉጉት የሚጠብቁት መርሀ ግብር አይኖረንም ማለት ነው።

፪ኛ፦ መረጃ ቲቪን በተመለከተ የምሥራች አለኝ። በኤልያስ ክፍሌ በሥራ ምክንያት ክፍለሃገር ለክፍለ ሃገር መንከራተት የእለተ እሁድ "ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር" የሚለውን ተወዳጅ፣ ደግሞም ተናፋቂ፣ ለወዳጅ ማርና ወተት፣ ለጠላት ሬትና በረኪና፣ የአይጥ መርዝም የሆነ መርሃ ግብሬ በቴክኒሽያን እጦት መቋረጡን፣ ቢያንስ 5 ወይም 6 ወራት ያህል ፕሮግራም ላይሮን እንደሚችል ነግሬአችሁ ነበረ።

"…ከፕሮግራሙ መቆምም ጋር ምንአልባት በሃገረ አሜሪካ ያላችሁ፣ በአይቲ ሙያ ዕውቀት ያላችሁ፣ የኤልያስን ቦታ ተክታችሁ የምታግዙኝ ካላችሁ አናግሩን ብዬም ነግሬአችሁ ነበር። በዚህ ጥሪ መሠረት እስከአሁን 5 ያህል ልጆች ፈቃደኝነታችሁን ያሳያችሁኝ መሆኑን ለኤልያስም ነግሬው እሱም ተደስቷል።

"…ስለዚህ በቁጥር በዛ ማለቱ አይከፋም በሃገረ አማሪካ የምትኖሩ እና ሌሎችም ፈቃደኛ የሆናችሁ ወንድም እህቶች ካላችሁ ፈቃደኝነታችሁን በውስጥ መስመር ንገሩኝ እና ጋዜጠኛ ኤልያስ ክፍሌ በተገኘበት አንዲት አጭር ስብሰባ እናደርጋለን። የመብዛት ጥቅሙ አንዱ ባይችል አንዱ ይኖራል ማለት ነው። በዚያ ላይ ኤልያስ ክፍሌንም እናሳርፈዋለንም ማለት ነው።

"…በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ምሽት ከ1:00 ሰዓት ጀምሮ የሚመቻችሁ ወንድም እህቶች አናግሩኝ። ፍጠኑ።

• ፌስቡክ…
• ዩቲዩብ …
• ቲክቶክ…
• ራምብል…
• ቴሌግራም…

"…ቢሆንም እጅ መስጠት ብሎ ነገር አይታሰብም። ወደፊት ብቻ።
4.0K views17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 21:59:01
በነገራችን መሃል…!
የነቢያት ምረቃ ዜና ተከታትለን እንመለሳለን።

"…Senior prophet ሄኖክ ግርማ ለ አንድ ዓመት ያሰለጠናቸውን 127 የጌታ ወንድና ሴት ነብያትን በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመርቋል። የ jPS prophetic foundation class 2023 graduates እንኳን ደስ አላችሁም ተብለዋል።

"…የሰማዕታት ምርቃት ብሎ ነገር በዚያ ቤት የለም እንጂ ከነቢያት ምረቃ ቀጥሎ የሐዋርያት እና የመጋቢ፣ ተመጋቢ ምርቃት ሳይኖርማ አይቀርም የሚሉም መተርጉማንም አሉ።

"…ጋሽ ነቢዩ ሄኖክ ግርማ የሴቶች ቀሚስ በመልበስ ወንዶችን መስበክ ያዘወትራልም ተብሏል። ወሴ…
4.5K views18:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 21:49:47
ቀጠልኩ…

"…አጠቃላይ ዘገባቸው ሲጨመቅ ትግሬ ሲበደል ዝም ብላችኋልና እሰይ ይበላችሁ… የ27 ዓመቱን ፋሽስታዊ ወንጀል በማረሳሳት ስለዐማራ የዘገቡ በማስመሰል በሆነች ዓረፍተ ነገር የዐማራ cause ላይ ውኃ በመቸለስ demoralized ለማድረግ መጣር።

፫ኛ፦ ለወያኔ የእንጀራ ቤት፣ የነዳጅ ጉድጓዷ የነበረውን አብዲኢሌን በመደገፍ በወያኔ ኮንትሮባንዲስት ጀነራሎች ጉሮሮ ላይ የተሰካ አጥንት የሆነውን አቶ ሙስጠፌንና በብአዴን ሰበብ ዐማራን በሆነው ባልሆነው መውቀጥ።

"…ለዚህ ነው በቀደም መጀመሪያ ሙስጠፌ ተመርዞ ዱባይ ሆስፒታል ገብቷል ብለው ያጮሁት። ዜናው በተሠራ ማግስት የኢድ በዓል ላይ ሙስጠፌ ጅጅጋ ላይ ታይቶ ውኃ ሲቸልሰባቸው ቆይተው ትናንት ደግሞ በዛው በሙስጠፌ ላይ አሁንም ሌላ የሙስና ክስ አመጡበት።

"…ሙስጦፌን አጀንዳ የሚያደርጉት እነሒዊ የአብዲሌ ክንፍ ስለሆኑ ነው። አብዲሌ ክልሉን የሂዊ ኮንትሮባንዲስቶች የሚፈነጩበት አድርጎት ነበር። ሚስጠፌ ደግሞ እንደ አብዲሌ አያሠራቸውም። አብዲሌ ጋዜጠኞቹን ስፖንሰር የሚያደርገው የህወሓት የገንዘብ ምንጭ ስለነበር ነው። ሂዊ የፌደራል መንግሥቱን ተጠቅማ ሙስጠፌን መምታት ትፈልጋለች። በዚህ ግርግር ሙስጠፌ ተወግዶ አብዲሌ ከተፈታላት ደግሞ እንደገና ተመልሳ ቀጠናውን ያዘች ማለት ነው። ኦህዴድ ደግሞ ዓይኑ እያየ ያንን ቀጠና ለሒዊ አሳልፎ መስጠት አይፈልግም። ሂዊ አውጥታው በኮንትሮባንድ ስትቸበችበው የነበረውን ነዳጅ አቢይ ሆዬ ገና ሥልጣን ላይ እንደወጣ ከነገ ጀምሮ ለገበያ እናቀርበዋለን ብሎ ሲበጠረቅ ኦሮሞዎቹ ተረባርበው እኛም ሳንዘርፍ የምን ጻድቅ መሆን ነው ዝጋ ብለው ዝም አሰኝተውት ይኸው ነገር ሁሉ ተዳፍኖ ቀርቷል።

"…አልጨረስኩም ተመልሼ እመጣለሁ። ምንደ ወያኔና ተጎታቹ ወነግ እንደ ጉድ ነው ያበዱብኝ። አይ ዘመዴ…
4.4K views18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 20:21:00
"…ፊልም እና ሚዲያ ማለት እኮ ከአውቶሚክ ቦንብ የበለጠ አውዳሚም፣ አልሚም እንደሆኑ የዘርፉ ባለሙያዎች ይናገራሉ። የአማሪካ ትልጉ የገፅታ ግንባታዋ ነፀብራቆች ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል ሆልዊዶች የሚሠራቸው ፊልሞች እና እነ ሲኤንኤን የሚያመርቷቸው ወሬዎች መሆናቸው ይነገራል።

"…አንድ የሆልዊድ ፊልሞችን የሚያይ ሰው በዘመናዊ ካሜራዎች፣ በምርጥ ዳይሬክተሮች የተቀረፁ፣ የተፈበረኩ አምሳለ ገነት የመሳሰሉ ፊልሞችን ሲያይ ወዲያው ፊልሙን ማየት እንደጨረሰ ብድግ ብሎ እንጦጦ ኪዳነምህረት፣ ቅዱስ ዑራኤል በመሄድ የዲቪ ሎተሪ እንዲደርሰው ስለት የሚሳል ሰው የትየለሌ ነው። አሜሪካ ለማኝ ያለ፣ አውሮጳ ደሀ ያለ የማይመስለው ነፍ ነው። ሁሉም ሴቶች አንጀሊና ጆሊ የሚመስሉ የሚሰሉትም ነፍ ነው። ብር ከየዛፉ የሚሸመጠጥ የሚመስለውም የትየለሌ ነው። ይሄ የሆልዩድ ተጽዕኖ ነው።

"…የምዕራቡ ዓለም የመገናኛ ብዙሃንም እንደዚያው ነው የሚያደርጉት። የውሸት ዜና አምርተው ከመሸጥ እስከ መንግሥት መገልበጥ ድረስ አቅም ያላቸው ናቸው። ዋናው ሥራው የሚሠራው ጭንቅላት ላይ ነው። ከወደዱህ እንደወያኔ ደሴ ደርሰህ ኮተቤ ነህ ብለው ያጮሁልሃል፣ ካልወደዱህ ጨፍጫፊ፣ ምዕራብ ትግራይ እያሉ ሊያካልቡህ ታያቸዋለህ። ፈረንሳይ እየነደደች እንዲች ብለው አይዘግቧትም። የጠሉት ሃሀገር እና መንግሥት ከሆነና ለእነሱ ካልተመቻቸው ግን እንደ ሊቢያው መሀመድ ጋዳፊ አካልበው ወተትና ማር የሚያጠጣውን መንግሥቱን ገልብጦ እከካም እንዲሆን ያደርጉታል። ስለዚህ ሚዲያም አደገኛ ነው ማለት ነው።

"…ወያኔ ይሄን አሳምራ ታውቃለች። 27 ዓመት ቀጥቅጣ የገዛችው በሚዲያ ነው። ፓርቲዋን ገንብታ ተፈሪ የሆነችው በሚዲያ ነው። አቢይ ያን አይቶ ነው ጋዜጠኛና አክቲቪስት ላይ ኢንቨስት የሚያደርገው።

"…ምን ለማለት ፈልጌ መሰላችሁ…?
4.6K views17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-01 21:29:33
"…በነገራችን ታች…

"…በዚህ አካባቢ እየተካሄደ ያለውን የካርታ ጫወታ በደንብ እየተከታተልነው ነው። ወፎቼም ውሎና አዳራቸውን በ4 ኪሎ መንበረ ፓትርያርክ ግቢ፣ በቦሌ ደንበል ህንጻ አጠገብ የኦሮሚያ ጽ/ቤት ፊት ለፊት በለ ፔኒሲዮንና መቀሌ ከተማ እየንተንፈላሰሱ ሥራ ላይ ናቸው።

"…እኔና ወፎቼ በአሁኑ የቅዱስ ሲኖዶስ መንፈስ ቅዱሳዊ ጉባኤና ምስጢራዊ ሂደቱ ላይ በፍፁም ጣልቃ አንገባም። እነሱም ምርጫውን ምስጢራዊ እንዳደረጉት እኔም አስቀድሜ ምንም አልተነፍስም። ይግፉበት።

"…ቃል የምገባላችሁ ግን አንድም ከቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቀኖና ውጪ በአቢይ አሕመድ፣ በሽመልስ አብዲሳ፣ በኦሮሚያ ወሐቢስት፣ በወለጋና በደቡብ ጴንጢስት በኪሳራዋ ወያኔም ፈቃድ የሚሾም ጳጳስ እንደማይኖር ነው።

"…አይ ሕዝቡ ምንአባቱ ያመጣል? ተብሎ የማንም ሸርሙጣ፣ አመንዝራ፣ ጋለሞታ፣ የማንም ወንድኛ አዳሪ፣ የማንም ወሴ፣ የተጠመቀ እስላም የአራት ሚስት ባል፣ የማንም ዘራፊ፣ ማፍያ፣ ጋጠወጥ ነውረኛ፣ የማንም ዘረኛ፣ ተረኛ፣ ወታደር፣ የማንም አቅለቢስ፣ ቀትረ ቀላል፣ ቀልበቢስ፣ ድልብ መሃይም፣ አራጅ፣ አሳራጅ፣ ነፍሰገዳይ አረመኔ ወንበዴ፣ የማንም ዘረኛ አስማተኛ ዶሮ ቀባሪ መተተኛ ግን አይሾምብንም። አበደን አይሾምብንም።

"…አይደለም እንዲህ ያለ ነውረኛ ሊሾምብን ቀርቶ አሁን ካሉት መካከል ያበጠውን እያፈነዳን ደፍርሶ እንዲጠራ እንፋለጣለን ላመጣላትም እንሞክራለን። የግድ ከሆነ ግን ጉዳዩ የሃይማኖት ነውና ይፍቱኝ አባቴ እያልን ወደ ፍልሚያው እንገባለን።

#ማስታወሻ፦ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስ ሆይ አሜሪካ ድረስ ስሜን እየጠሩ ብዙ ባይደክሙ መልካም ነው። እኔ አሁን አልደረስኩብዎትም እርሶም ባይደርሱብኝ መልካም ነው። እርስዎ በተለየ የሚጠብቋት እኔ ዘመዴ የማፈርሳት ኢትዮጵያ የለችም።

•ይፍቱኝ አባቴ…!
5.9K views18:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-01 18:27:59
"…አቢይ አሕመድ በሚመራት ሃገር በምዕራብ ወለጋ ቂልጡ ካራ እና በአዲስ አበባ ይሄን ይመስላል።

• ጨበርበርቱ…!
6.0K views15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-29 21:51:38 "ርዕሰ አንቀጽ"

"…የዛሬ ርዕሰ አንቀጽ የተጻፈው በራሴ ጉዳይ ዙሪያ ነው። በጀርመን ቆይታዬ እስከ አሁን ሁለት ጊዜ ተከስሻለሁ።  ሁለቱንም ክሶች ዐቃቤ ሕግ ሳይደርስ፣ ወደ ፍርድ ቤት ክርክርም ሳይመራ በፌደራል ፖሊስ ምርመራ፣ ቃሌን በሰጠሁ ጊዜ የቆመ ነው። የመጀመሪያው በኢትዮጵያ ጽንፈኛ እስላሞች ውትወታ በሐሰት በእኔ ባልሆነ ነገር ግን በእኔ ስም በፌስቡክ ገጽ ላይ በተጻፈ የአሸበርቲነት ጦማር ነበር።

"…ከምርመራ በኋላ ፖሊስ እንዲህ ብሎኝ ነበር። ከሳሾችህን መክሰስ ትችላለህ። እኔም መለስኩ። አልከሳቸውም። እነሱም እንደ እኔው ስደተኛ ናቸው። ባያውቁ፣ ባይረዱ፣ ባይገባቸው፣ ቢመስላቸው በስሜት፣ በንዴት፣ ለሃይማኖታቸው ቀንተው ያደረጉት ነው። እኔ እንደተንከራተትኩ መንከራተት የለባቸውም። ይልቅ ንገሯቸው። አስተምሯቸው ብዬ ፋይሉን ዘጋሁት።

"…ቆይቶም ባለፈው የገና ሰሞን ድጋሚ ከሰሱኝ። ያኔ እንኳን የከሰሱኝ በኦሮሞ እና በትግሬ ጽንፈኛ አክቲቪስቶች ጫና አዲስ አበባ የሚገኘው የጀርመን ኤምባሲ በደረሰበት ጫና ምክንያት በተፈጠረ ምክንያት ነበር ከፖሊስ ጋር የተገናኘነው። የተከሰስኩትም ይሄንኑ አራጅ ከሃዲ የአቢይ ጦር "በፌክ ፎቶ ሲከሱት በፍጹም ስንትና ስንት የፈጠጠ ወንጀል እያለው ይሄን ፌክ ፎቶ መጠቀም ነውር ነው በማለቴና ዘመቻውን በማክሸፌ ምክንያት የተበሳጩ ነውረኞች የፈጠሩት ነበር። እሱም ውድቅ ሆኗል።

"…የአሁኑ ለሦስተኛ ጊዜ መሆኑ ነው። ከሳሾቼን አላወቅኳቸውም። ያው አሸበርቲ ስላለኝ መንግሥት ይሁን፣ ግለሰቦች ይሁኑ፣ ማኅበራት ወይም ድርጅቶች አላወቅኩም። የአሁኑን ግን በብዙ ምክንያት ነገርየውን እንዲሁ በዋዛ ማለፍ አልፈለግሁም። አዎ ከሳሾቼን ወይም ከሳሼን ማወቅ እፈልጋለሁ። ከፖሊስ ጣቢያ በዘለለ ፍርድቤት ቀርቤ ከከሳሾቼ ጋር መሟገት እፈልጋለሁ። ለሚደርስብኝ ቁሳዊም ሆነ አዕምሮአዊ ጉዳት በሕግ አግባብ የሚጠየቀውን መጠየቅ እፈልጋለሁ። በዚያ ላይ ካሳሼን በስም በአካል ማወቁ በራሱ ለእኔ የግድ አስፈላጊም ጠቃሚም ነው።

"…በሌሊት ነው በጠዋት ከመኖሪያ ከተማዬ ተነሥቼ የሕግ ባለሙያ ጠበቃዬ ወደሚገኝበት ከተማ ከመንፈሳዊ ወንድሜ ከኢሱ ጋር የሄድኩት። ከእንግዲህ የሚፈልገኝ፣ የሚከሰኝ ሰው በሙሉ ከእኔ ጋር በአካል ግንኙነት አይኖረውም። ለእኔ መጥሪያ መስጠት ቤተሰቤንም ማጨናነቅ አይጠበቅበትም። ይከሰኛል የክስ ወረቀቱ ለጠበቃዬ ይደርሰዋል። ስፈለግ እቀርባለሁ እሟገታለሁም። ይሄንን ጨርሼ አሁን ገና ከጠበቃዬ ቢሮ ወጥቼ የጓደኛዬ የኢሳያስን ልጆች ጠይቄ፣ ለማታው የኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ መርሀ ግብሬ ለመድረስ ባቡር እና አውቶቡስ ይዤ ወደ ራየን ወንዝ ማዶ ጎጆዬ እመለሳለሁ። የሚያበሳጨው ግን እስከአሁን ድረስ ስንትና ስንት ምን የመሳሰሉ ቃሪያ በሚጥሚጣም የሆኑ ጦማሮች እንዳልለቅ ጌዜዬን መበላቴና ስለራሴ ማውራት የማልፈልገውን የግድ ስለራሴ ለማውራት መገደዴ ነው።

"…ቀጥሎ ከእኔ ጓደኞች ከእናንተ ከቤተሰቦቼ ምን ይጠበቃል? ስለሚለው ጉዳይ እሱን ቆይቼ እመለስበታለሁ። እንግዲህ ዛሬ በእኔ ጉዳይ ነው ስናወጋ የምንውለው። በእኔ በኩል ግን እንደ ዜጋ ስለ ሃገሬ፣ እንደ አማኝ ስለሃይማኖቴ ደሀ ተበደለ፣ ፍርድም ተጓደለ ብዬ ለመጮህ የማንም ፈቃድ አያስፈልገኝም። ከመቃብር በቀር ማንም ምንም አያስቆመኝም።

• ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው።
7.6K views18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-28 20:52:36
ይሄ የዘር ጭፍጨፋ ነው።

"…በአቢይ አሕመድ፣ በደመቀ መኮንን፣ በሽመልስ አብዲሳ የአስተዳደር ዘመን፣ በብራኑ ጁላ፣ በይልማ መርዳሳ፣ በደመላሽ ገብረ ሚካኤል፣ በተመስገን ጥሩነህ የአስተዳደር ዘመን፣ ቅዱስ ሲኖዶስ እና መጅሊስ፣ የጴንጤዎችም ኅብረት ባለበት ዘመን፣ በእ አህመዲን ጀበል፣ ጃዋር መሃመድ፣ በእነሙጂብ አሚኖ፣ በእነ ኦኤም ኤን፣ በኦቢኤን፣ በሀሩን ሚዲያ እንደ ጉድ አሠራጭተው ዐማራ እንደ ዜጋ ሳይሆን እንደ ጠላት እንዲታይ፣ በዘሩ ተለይቶም እንዲህ እንደምታዩት ቤት ለቤት እየሄዱ ዐማራ የትነው ብለው እድሜ፣ ፆታ ሳይመርጡ ጨፍጭፈው በጅምላ እንዲህ ነው የቀበሩት።

"…ይሄ ጭፍጨፋ ያለው ረቅ ወለጋ ነው እኔ ጋር አይደርስም። እኔ ያለሁት ጎንደር ነው፣ ወልድያ ባህርዳር ነው። ደሴ ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ማርቆስ ደብረ ታቦር ነው። እኔ ያለሁት አዲስ አበባ ነው ብለህ ተዘናግተህ የተቀመጥክ ዐማራ በሙሉ የሚጠብቅህ እንዲህ አይነት ጭፍጨፋ ነው።

"…ኩሽ ነን የሚሉት የኦሮሞ ፅንፈኞች ሴማውያን የሚባሉትን ዐማሮች በዚህ መልክ ነው የጨፈጨፏቸው። ይሄንን ነው ያ ማቶ ጭንቅላት መሃይም መሪ " ይሙቱ፣ ይገደሉ ፀሐይ ለአስከሬናቸውን እንዳይመታው ችግኝ እንተክልላቸዋለን" ብሎ በፓርላማ ያላገጠው።

"…ይሄን እያየ ለፍትሕ ያልታገለ፣ ለፍትሕ ያልጮኸ በሙሉ የጊዜ ጉዳይ እንጂ ፈጣሪ በአንድም በሌላ መልኩ ቢሆን ክንዱን ያነሣባቸዋል።

"…ዐማራ ለመታገል ሃቅ አለው። ወጥር ዐማራ፣ መክት አንክት። ይሄንን ለዐማራው፣ ለኦሮሞው፣ ለትግሬው፣ ለደቡቡ፣ ለሐረሬው፣ ለሱማሌ፣ ለአፋሩ አሳያው። ምን ተሰማችሁ የብልፅግና ካዳሚ ካድሬዎች…?

• ሌሎችም አሉኝ፣ እያረፍኩ እለቅላችኋለሁ።
7.8K views17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ