2023-04-21 21:24:21
"ርዕሰ አንቀጽ"
"…በሱዳን የርስ በእርስ ጦርነቱ እንደቀጠለ ነው። ዜጎች ከካርቱም ወጥተው ወደ አጎራባች ከተሞች እየሸሹ ነው። የከተማ ውስጥ ጦርነቱም እንደቀጠለ ነው። በ3 ቀን ብቻ 45 የጦር ጀቶች ካሉበት ሳይነሱ ወድመዋል። የታንኩና የተሽከርካሪዎቹ አይወራም። አይነገርምም። ሆስፒታሎችም ወድመዋል። በብዙ ቁጥር ዜጎች እየሞቱም እየቆሰሉም ነው። እንዲያም ሆኖ አሜሪካ ዜጎቿን ለማውጣት አላሰበችም። በእሱ ፈንታ በሱዳኑ ጦርነት ሰበብ ተጨማሪ ወታደሮች ምሥራቅ አፍሪካ ጅቡቲ ለማስፈር መወሰኗን ነው ያሳወቀችን።
"…የበረኸኞቹ 2 ኃያላንና 7 የአረብ ሃገራት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ የሚለው ትንቢት ብቻ የሚጠበቅ ይመስለኛል። በየመንና በሶሪያ ላይ የተራገፈው የምዕራባውያኑ የጦር መሣሪያ ከአሰብና ምጽዋ መጋዘን ወጥቶ በኢትዮጵያ ምድር ሊራገፍ ይችላል። ጅቡቲና ሱማሊያም የሠፈረው መንጋ ተፍተፍ ማለቱም አይቀርም። ነገርየው መቼ እንደሚጀመር አይታወቅምና ተዘጋጅቶ መጠበቁ ግን መልካም ነው የሚሉም አሉ። ከወር በፊት ካርቱም እንዲህ የጦር ቀጠና እሆናለሁ ብላ ለአፍታም አስባ እንዳልነበር ልብ ይሏል። አዲስ አበባም ሰምተሻል።
"…ሶሪያ ላይ የተፋጩት አማሪካ መሩ የምዕራቡ ዓለም ኃይልና ሩሲያ ናቸው። ሶሪያ ብትፈራርስም ፑቲን አላሳድንና መንግሥታቸውን ግን ታድጓል። የመን ስትወድም ሱዳን ሳኡዲን አግዛ በየመን ጦርነት ተሳታፊ ነበረች። የመን ፈራረሰች ሱዳን የየመን ርግማን በቶሎ የደረሰባት ይመስላል። የኦሮሞ ቦለጢቀኞች ዐማራን ካላንበረከኩ እረፍት የሚያገኙ ስለማይመስላቸው ከዐማራ ጋር ጦር መግጠማቸው የግድ መሆኑ ሳይታለም የተፈታ ነው። ዐማራም ለመመከት፣ መልሶ ለማንከትም ተዘጋጅቷል። ሱዳን እርስ በእርስ መፋጀቷ፣ ግብፅም በሱዳን መዋረዷ አቢይን ወደ ዐማራ በቶሎ እንዳይገባ ቢያደርገውም ይቀራል ማለት ግን አይደለም። ምንአልባት ኮሌራ፣ ራብና አመፅ ካላዘገየው በቀር አብይ አህመድ መሞከሩ እንደሆን አይቀርም። ግባ ትቀምሳታለህ።
"…የዓለም ጦርነቶች ሁሉ ማሳረጊያ ግን ኢትዮጵያ ናት። እስልምናን የፈጠረችው የሮም ካቶሊክ እንደሆነች የሚተረጉሙ መተርጉማንም አሉ። ሮም ኃጢአት በይፋ ትሠራለች። እስልምና የሮምን ኃጢአት በይፋ ይቃወማል። ሕዝብም እስልምናን አድንቆ ትክክል ብሎም እንዲቀበል ጥቅሴ መሆኑ ነው። ኢትዮጵያ የሃይማኖቶች ሁሉ መነሃሪያ እንድትሆን ተበጅቶ ወደ ሥራ ከተገባ ቆየ። እስልምናና ፕሮቴስታንቲዝም በአንድ ፖፖ ካልተጠቀምን ካሉም ቆዩ። ተዋሕዶን የጋራ ጠላት ያደረጉት በዶግማና በቀኖና አንድ ሆነው እኮ አይደለም። ጥላቻው ነው ያገናኛቸው። ያስተሳሰራቸውም።
"…አስመራ ተወላጁ ትግሬ ቴዎድሮስ አድሃኖም፣ መሠረቱ የወሎ ዐማራ የጴንጤ እስላሙ የኦሮሞ ወኪል አቢይ አህመድ ለዓለም አቀፍ ከፍተኛ ሹመትና ሽልማት የታጩት በዕቅድ ነው። ደመቀ መኮንን የእንግሊዝ፣ ዐቢይ የአማሪካና የዓረብ ቋሚ ተቀጣሪ ናቸው እኮ የሚሉ አሉ። ሬድዋን ሁሴን፣ ሙፈሪያት ካሚል፣ አደም ፋራህ፣ የሰላም ሚንስትሩ ብናልፍ አንዷለም፣ ሽመልስ፣ አዳነች እና ጁላም በፀረ ዐማራነት ተጠምቀው ጉዳይ ለማስፈጸም የተሾሙ ናቸው።
"…በኦሮሞ ጴንጤና እስላሞች በኩል ክርስቶስ መሠረቷ የሆነችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን የማፍረሱ ተግባር የሰይጣኑ ዓለም ዕቅድ መሆኑን የሚናገሩም አሉ። ሶሪያ፣ ህንድ፣ ግብጽ፣ አርመን በኦርቶዶክሳዊነታቸው ዋጋ ከፍለዋል። ዐማራና ትግሬም በኦርቶዶክስነታቸው በአረመኔዋ ኮሚኒስት በህወሓት ፈቃድ በጴንጤና በእስላሞቹ የብልፅግና መሪዎች ሴራ ተፈሳፍሰዋል። ገዳማትም ፈርሰዋል። ቅዱሳት መጻሕፍት ተዘርፈዋል። ካህናት መነኮሳት ታረደዋል። በዐማራም በኦሮሚያም እንደዚሁ ኦርቶዶክስ በመናፍቃንና በአህዛቦቹ ገዢዎች ፍዳቸውን ዓይተዋል። እያዩም ነው። ዩክሬንና ሩሲያም ኦርቶዶክስ መሆናቸውን ልብ ይሏል። ዐቢይ ለቡራኬ ሮም የሚመላለሰው ወዶ መስሎሃል።
"…በኢትዮጵያ የተሸነፈው የአውሬው መንፈስ ኢትዮጵያን በማፈራረስ ድልን ለመጎናጸፍ የቋመጠ ይመስሏል። በሶዳማዊነት ጉዳይ ሚጢጢየዋን እስላማዊት ሃገር ኳታርን የሚያከብረውና አንዳች ነገር በተቃውሞ የማይተነፍሰው ዓለም በዚሁ ጉዳይ ሩሲያን ግን ሚሳኤል ተኩሼ ካላንበረከኩ ይላል። በኢትዮጵያ ሕግ ሰዶማዊነት ፀያፍ ቢሆንም ዛሬ ሥልጣን ላይ ለመውጣት፣ በንግድ ሃብት ለማፍራት የዚህ ነውር ተጠቂ መሆን ግድ ይላል። ይሄ ኢትዮጵያን የማንበርከኪያው አንደኛው መንገድ ነው።
"…አርቴፍሻል ራብ፣ የኢኮኖሚ ድቀት፣ ሕዝብን አስጨንቆ መግዛት። ነውረኛው የተደላደለ ኑሮ ሲኖር፣ አማኙና ሃቀኛው እንዲቆረቁዝ በማድረግ ነውረኛው የብልጭልጩ የብልፅግና መንገድ ትክክለኛ ነው በማለት ሰው ሁሉ የሞራል፣ የግብረገብ እና የሃይማኖት አሴቱን አሽቀንጥሮ ወደ ነውሩ ዓለም እንዲቀላቀል ማድረግም የዚሁ ዓለም አቀፍ ተልእኮ አንዱ አካል ነው። ለመዘነጥ እንኳ መጰንጠጥ የግድ እንደሚልህ ብዙ ሰው እንዲያምን እየተደረገ ነው። ባንኮች ለብድር ገንዘብ የሚያፈሱልህ ከጰነጠጥክ ወይ ከሰለምክ መሆኑን ሠርተውበት ተግባራዊ አድርገውታል። ጴንጤም እስልምና ባለባንክ ናቸው።
"…እስላሙ የዓረቡን፣ ጴንጤው የምእራቡን ዓለም ባሕል በነፃነት እንዲያስፋፉ ነገሮች ተመቻችተውላቸዋል። ብሔራዊ ቋንቋ፣ ፊደል ወዘተረፈ እንዳይኖረን በብርቱ ተሠርቶ ተግባራዊ ተደርጓል። ሱሉልታና ቃሊቲ አማርኛ ከትምህርትም ከሥራም ቋንቋነት ተወግዷል። አማርኛ የዐማራ ነው ተብሎ ስለተከሰሰ ዜጎች እስላሙ ዓረብኛን፣ ጴንጤው እንግሊዝኛን ብሔራዊ ቋንቋው እንዲያደርግ ተወስኖ ወደ ሥራ ተገብቷል። ነውር በሃገሪቱ ተንሠራፍቷል።
"…ሕዝብ ከመጠን በላይ በዝቷል። የሃገር ኢኮኖሚ ተንኮታኩቷል። ኢትዮጵያን የሚመሩት ጎረምሶች ከዚህ ድቀት የሚወጡበት ዕውቀት የላቸውም። ሕዝብ መቀነሥ አለበት ብለው በመወሰናቸው ሕዝብን በራብና በጦርነት፣ በጭንቀት፣ በማሳበድ፣ በማሰደድ፣ በማሰር፣ በበሽታም በመጨፍጨፍ ላይ ተጠምደዋል። የዐማራና የአፋር፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሳይጨመር ከትግሬ ብቻ አንድ ነጥብ 2 ሚልዮን ወጣት ህጻን ሽማግሌ በጦርነቱ እና በጥይት ተጨፍጭፎ አልቋል። ይሄ ዘግናኝ ነው። አሁን ደግሞ የዐማራው ቁጥር ይቀንስ ዘንድ ቢለዋው እየተሳለለት ነው።
•…ከኤርትራ በረሃ እና ከዐማራ ገጠሮች በሚነሱ ጥቂት የመስቀሉ ጦረኞች አማካኝነት ኢትዮጵያም ምሥራቅ አፍሪካም ነፃ ይወጣሉ። እስከዚያው ግን የተማረ ይግደለኝ፣ ምላስ ያለው ያግባኝ ባልነው መሠረት በአፈ ቅቤ ሆደ ጩቤው በአቢይ አሕመድ አርጩሜ ምዕራባውያኑ እነሱ ወዳዘጋጁልህ ወጥመድ የግድህን እስክትገባ ድረስ ተራ በተራ ትዠለጣታለህ። ዳዊትህን ያነሣህ፣ ማዕተብክን ያልበጠስክ ግን እልል እያልክ ትሻገራታለህ። ፈሳሙን አትፍራው። አባቴ ይሙት እውነቴን ነው። ስቃዥ የምጽፈው መሆኑ ይታወቅልኝ ብሏል።
• ድርጅቱ…!
2.1K views18:24