Get Mystery Box with random crypto!

መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemarian — መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemarian — መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል
የሰርጥ አድራሻ: @zemarian
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 15.65K
የሰርጥ መግለጫ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤት የሚከናወኑ ተግባራቶች አስመልክቶ ቆየት ያሉ ያሬዳዊ ዝማሬ በሰንበት ትምህርት ቤት ውስጥ ፣የሰንበት ት/ቤታችን ወቅታዊ ትምህርቶና የቤተክርስቲያን ወቅተዊ ጉዳዮችን ለማግኘትና ለመማማር @zemariann ይቀላቀሉን፡፡
ለማንኛውም አስተያየት @mzbot_bot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-05-12 20:42:33
ቅዱስ ሲኖዶስ በ3ኛ ቀን ውሎው
በተለያዩ ጉዳዮች ውሳኔ አሳልፏል።

ግንቦት ፬ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም

አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
""""""""""""""""""""

ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) ዕለታዊ ማብራሪያ የሰጡት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ በሦስተኛ ቀን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን በተመለከተ ውሳኔ ማሳለፉን ገልጸዋል።
በዚህም ብፁዕ አቡነ ዲዎስቆሮስ የደቡብ ትግራይ ማይጨው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና መተከል ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቀደም ሲል ያገለግሉባቸው በነበሩ አህጉረ ስብከቶች አገልግሎታቸውን እንዲቀጥሉ ጉባኤው ወስኗል።

ጉባኤው በዛሬው ውሎው እንዲነጋገርበት ተይዞ የነበረው የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ጉዳይ የጉባኤው የመጨረሻ አጀንዳ እንዲሆን የአጀንዳ ሽግሽግ አድርጓል።

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) በሰጡት ዕለታዊ ማብራሪያ ጉባኤው የዋልድባ ዳልሻህ ኪዳነምሕረት ማህበረ ደናግል ገዳምን በተመለከተ፣ የያዘው አጀንዳ ላይ መወያየቱን እና ለውሳኔ በይደር መቆየቱን አረጋግጠዋል።
EOTC TV
2.0K views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 20:42:21 ቅዱስ ሲኖዶስ በ2ኛ ቀን ውሎው የተከፋፈለ  ሲኖዶስ እንደሌለ እና ከዚህ  ሐሳብ ውጪ  የሆነ አካል  ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን  ሕግና ሥርዓት ውጪ የሆነ መሆኑን በመግለጽ መንግሥትን የሚያነጋግሩ ል ዑካን ሰይሟል።
በቅዱስ ሲኖዶስ በትግራይ ያሉ አባቶችና  አባላቱን በአካል የሚያነጋግሩ  ብፁዓን  አባቶች ተመርጠው  ኃላፊነት  ተሰጥቷቸዋል።


የ2015 ዓ.ም  የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት የሁለተኛው ቀን ውሎን አስመልክቶ  ብፁዕ  አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር)  የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባባቢዋ  አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ማብራሪያ ሰጡ።
ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) ዕለታዊ ማብራሪያ የሰጡት ብፁዕነታቸው በሁለተኛው ቀን በነበረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ 
ሁለት ርዕሰ ጉዳዮች መወያያየቱን ገልጸዋል።
ቅዱስ ሲኖዶስ በቀዳሚነት በሀገር ሰላም ዙሪያ በተነሳው ርዕሰ ጉዳይ ጉባኤው ብዙ ሲወያይ  ከቆየ በኋላ  በመጨረሻም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሁሉን ማድረግ ትችላለች ምእመናንም የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ይሰማሉ የሚለው ሐሳብ አሸንፎ በዚህ ጉዳይ ላይ ቅዱስ ሲኖዶስን ወክለው  የሚሰሩ ሦስት ብፁዓን  አባቶች ተመርጠው  የሀገር ሰላምን በተመለከተ  ረዥም ርቀት በመሔድና ከሚመለከተው አካል ጋር ሁሉ በመነጋገር   በሀገር ሰላም ዙሪያ  ከፍተኛ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉና አሁን ካለንበት መከራ የምንወጣበትን  መፍትሔ እንዲያመጡ ተመርጠዋል።
በቀጣይነት በወቅታዊ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ችግር አስመልክቶ በትግራይና በኦሮሚያ አህጉረ ስብከት የነበሩትን ችግሮች መነሻ በማድረግ
ሀ) በትግራይ ክልል የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት የትግራይ አባቶችና  አባላቱን በአካል የሚያነጋግሩ  ብፁዓን  አባቶች ተመርጠው  ኃላፊነት  ተሰጥቷቸዋል።
_ በተጨማሪም ተቋርጦ የነበረው በጀት እንዲለቀቅ
_ የማጽናኛ  መርሐ ግብር  እንዲካሄድና በተቻለ መጠን   አስቸኳይ  እርዳታ እንዲደረግ   በጉባኤው ተወስኗል።
ለ) በጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም የተከሰተውን የቤተ ክርስቲያን ፈተና በተመለከተ
ሰፊ ውይይት ከተደረገ እና  ወደ  መግባቢያ ሐሳቦች መደረሱን ገልጸው
በስድስት አኅጉረ ስብከቶች ምንም ዓይነት  የቤተ ክርስቲያን  አገልግሎት  እየተሰጠ አለመሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ የደረሰውን  መረጃ መነሻ በማድረግ
የማያዳግም የመፍትሔ ለመስጠት  ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው ከሦስቱ ብፁዓን አባቶች  ጋር አራት ብፁዓን አባቶችን ተጨማሪ በማድረግ
በቀጥታ የነበረው ችግር ሙሉ በሙሉ መቀረፉንና ከአንድ ሲኖዶስ ውጪ ሌላ አለመኖሩን ለመንግሥት አካላት  በጋራ ሔደው  የተደረሰበትን  ስምምነት  ተገቢውን  መረጃ እንዲሰጡ
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስን
ብፁዕ አቡነ  ሩፋኤልን
ብፁዕ አቡነ ናትናኤልን
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስን
ብፁፅ አቡነ  ሳዊሮስን
ብፁዕ  አቡነ ዜና ማርቆስን
እና  ብፁዕ  አቡነ ኤዎስጣቴዎስን
በመመደብ እነዚህ ሰባት ብፁዓን  አባቶች  በአንድ  ላይ  ከመንግሥት  ጋር በመነጋገር  ፍጹም በሆነ የመግባባት ስምምነት መፈጠሩን ገልጸው ከእንግዲህ በኋላ   የተከፋፈለ  ሲኖዶስ እንደሌለ እና ከዚህ  ሐሳብ ውጪ  የሆነ አካል  ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን  ሕግና ሥርዓት ውጪ የሆነ መሆኑን በአንድነት ለመንግሥት  እንዲያሳውቁ  መወከላቸውንም ገልጸዋል።
በቀጣይም ያሉንን የመወያያ ርዕሰ ጉዳዮች በዚህ መልኩ በመግባባትና በመተማመን  በመፍታት  በሀገርና በቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሰላምና አንድነትን በማያዳግም ሁኔታ የሚያውጅ ቆይታ ይሆን ዘንድ መላው ሕዝበ ክርስቲያን  በጸሎት አስቡን በማለት ብፁዕነታቸው አባታዊ መልእክታቸውንና ቡራኬአቸውን በመስጠት
የሁለተኛውን ቀን የቅዱስ ሲኖዶስ ውሎ አጠር ባለ መልኩ  ገልጸውልናል።
EOTC TV
1.5K views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 20:42:21 የግንቦት ርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ  ፲፰ የመወያያ ርእሶች  አጽድቆ ውይይት መጀመሩን  የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ  ገለጹ።

የ፳፻፲፭ ዓ/ም ርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ  በዛሬው ዕለት የጀመረ ሲሆን ይህን አስመልክቶም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሊቀ ጳጳስ  የጉባኤውን የቀን ውሎ አስመልክቶ  ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV)  መረጃ ሰጥተዋል።

ብፁዕነታቸው እንኳን አደረሳችሁ  የቤተ ክርስቲያናችን ጉባኤ በመሆኑ የሁላችም ጉባኤ ነው በማለት መረጃ መስጠቱን ጀምረዋል።

ብፁዕነታቸው ጉባኤው በቅዱስነታቸው ቃለበረከት እና ቡራኬ እንዲሁም  ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተኙበት መከፈቱን ተናግረዋል።
ቀጥለውም የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ሪፖርት   ጽ/ቤቱ ዓመቱ ያከናወናቸውን  ዝርዝር ሥራዎች  ለጉባኤው መቅረቡንና በቤተ ክርስቲያናችን ጉዳይ ራሳቸውን መስዋእት አድርገው ላቀረቡ፣  ለታሰሩ ለተንገላቱ፣ ብዙ መከራ ለደረሰባቸው  ወገኖች ቤተ ክርስቲያናዊ ምስጋና በጉባኤው ፊት መሰማቱንም ገልጸዋል።

ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ  አክለውም በአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴ የተለይተው የቀረቡትን አጀንዳዎች በጽሞና ከተመለከተና ከመረመረ በኋላ ፲፰ የመወያያ አጀንዳዎች  ማጽደቁንም ገልጸዋል።

የቅዱስ ሲኖዶስ  ምልዓተ ጉባኤ  ካጸደቃቸው አጀንዳዎች መካከል
፩. የሀገራችን ሰላም ጉዳይ
፪. ስለቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ችግሮች
፫. የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫን  በተመለከተ
፬. ተጨማሪ መንፈሳዊ ኮሌጆች ማቋቋምን በተመለከተ
፭. የውጭ ሀገራት ላሉ አህጉረ ስብከት መተዳዳሪያ ደንብ በተመለከተ
፮. የ10 ዓመት መሪ ዕቅድን በተመለከተ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ እንደሆኑ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ከእነዚህም በዛሬው ዕለት የቅዱስነታቸው የመክፈቻ ቃለበረከትና  የሰላም ጉዳይ ላይ ውይይት ማድረጉን  አብራርተዋል።

በመጨረሻም ጉዳዩ የሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በመሆኑ  ማኅበረ ካህናት ወምእመናን ጉባኤው እስኪጠናቀቅ   በብርቱ ጸሎት ሊያግዙንና ሊያስቡን ይገባል በማለት አባታዊ ተማጽኗቸውን ገልጸዋል።
EOTC TV
1.3K views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 20:26:13 የግንቦት 2015 ዓ.ም ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ መክፈቻ የጸሎት ሥነ ሥርዓት ዛሬ ግንቦት 1 ቀን በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተካሔደ።


የግንቦት 2015 ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ መክፈቻ የጸሎት ሥነሥርዓት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተካሂዷል!


በዕለቱ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዮርክና አካባቢው ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕአቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተገኝተዋል።

ለሁለት ሰዓታት ያህል የቆየው ሥርዓተ ጸሎት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የተመራ ሲሆን፤ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስዊድንና የስካደናቪያን አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አማካይነት ደግሞ ትምህርት ተሰጥቷል።

የ፳፻፲፭ ዓም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ረቡዕ ግንቦት ፪ ቀን ፳፻፲፭ ዓም በቅዱስ ፓትርያርኩ መልእክት የሚከፈት ይሆናል። ምንጭ፦ Eotc.

https://t.me/zemarian
1.1K views17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 20:26:07
868 views17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 19:53:18 የጃቴ መካነ ህይወት ቅድስት ኪዳነ ምህረት ካቴድራል ፍኖተ ሰማዕታት ሰንበት ትምህርት ቤት
መዘምራን
ክራር ኢዮሲያስ አበራ
@zemarian
862 views16:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 19:52:30 ዮም ፍሰሃ ኮነ
በዘማሪ ሃብታሙ/አሼ/
ክራር ኢዮሲያስ አበራ
@zemarian
834 views16:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 21:35:12 “ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ”
"ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም ፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ።"
አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡

43 04:19 ጥዑመ ልሣን
@Bekurk
1.5K views18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 21:35:12 #ግንቦትና_ልደት_መርገምና_በረከት
@zemarian
#ክፍል ፪

#ግንቦት
• ኢዮብ የተወለደበት
• እመቤታችን የተወለደችበት
• ጌታ ያረገበት
• መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ የወረደበት ወር ነው፡፡
ግንቦት በጥንት ዘመን የሚፈራ ወር ነበር፤ በብዛትም በዚህ ወር ሠርግ አይደረግበትም ነበር፤ ዋናው ምክንያት ደግሞ ኢዮብ የተወለደበት ወር በመሆኑ ነው፡፡ ከልደተ ኢዮብ ጋር ምን አገናኘው? ቢሉ ኢዮብ የተወለደበትን ቀን እንዲህ ብሎ ረግሞታል፦
"""" ከዚያም በኋላ ኢዮብ አፉን ከፍቶ የተወለደበትን ቀን ረገመ።
ያ የተወለድሁበት ቀን ይጥፋ፥
ያም ወንድ ልጅ ተፀነሰ የተባለበት ሌሊት።
ያ ቀን ጨለማ ይሁን፤
እግዚአብሔር ከላይ አይመልከተው፥ ብርሃንም አይብራበት።
ከቀኖች መካከል ደስ አይበለው፤ በዓመቱ በወሮች ውስጥ ገብቶ አይቈጠር።
እነሆ፥ ያ ሌሊት መካን ይሁን፤ እልልታ አይግባበት። """"" ኢዮ 3፡1-7፡፡
በማለት ረግሞታል፡፡ ይህ ወር ሰይጣን ጻድቃንን የከሰሰበት፤ ኢዮብን የፈተነበት ወር ነበር፤ (ኢዮ 2፡1-10)፤ በአንፃሩ የሰይጣን ወዳጆች ራሱን ሰይጣንን የሚጠሩበት ለሰይጣን መሥዋዕት የሚያቀርቡበት ወር ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት የጥንት ሰዎች ሩቅ መንገድ መጓዝ፤ ጋብቻ መፈጸም የመሳሰሉ ትልልቅ ጉዳዮችን አያከናውኑ ነበር፤ ወሩ ሰይጣን የሚሰለጥንበ ነው ተብሎ ስለሚታሰብ፡ ይህ ልማድ በብሉይ ኪዳን ነበር፡፡ እግዚአብሔር ቸር ነውና የዚህን ወር ርግማን ወደ በረከት ይቀይረው ዘንድ በዚህ ወር #ሦስት ታላላቅ ነገሮችን አከናወነበት፡፡
1. #ልደተ_ማርያም፦
እመቤታችን የተፀነሰችው ነሐሴ ሰባት ቀን ሲሆን የተወለደችው ግንቦት አንድ ቀን ነው፡ የእመቤታችን ልደት የመዳናችን ዋና መሠረት ነው፤ እርሷ ካልተወለደ ክርስቶስ በሥጋ አይወለድም፤ እርሱ በሥጋ ካልተወለደ ቤዛ የሚሆነን ዘመድ አይኖረንም ነበር፤ ቅዱስ ያሬድ " ከመ ትቤዙ ነቢያተ ወጻድቃነ.." (ለነቢያትና ለጻድቃን ቤዛ ትሆን ዘንድ (ክርስቶስን በመውለድ)) ብሎ ተናግሯል፤ የዕለቱ ምልጣን፡፡፡፡ የእመቤታችን ልደት የእውነተኛው ፀሐይ ክርስቶስ ልደት እስኪገለጥ ድረስ ሌሊቱን እንደ ጨረቃ እያበራ ያቆየን ተስፋች ነበር፡፡ እመቤታችን በራእዬ ቴክታ በጨረቃ የተመሰለችውም ይህንን ምሥጢር ያሳያል፡፡
• ኢዮብ የተወለደበት ይህ ወር እንዲጎድል ተረግሞ ነበር እመቤታችን ግን ሙሉ ጨረቃ ሆና እያበራች ወሩን ሙሉ (30) አደረገችው፡፡
• የኢዮብ ጨረቃ 29 ቀን ብቻ የምታበራ 1 ቀን ያጨለመች ናት (ኢዮብ ማለት ጨረቃ አበባ ማለት ነው) እመቤታችን ግን ሶልያና ተብላ 30ውን ሌሊት ሙሉ ያበራች ሙሉ ጨረቃ ናት (ሶልያና ማለት ሙሉ ጨረቃ ማለት ነው፤ የጨለመብንን ሌሊት ታብራልን!)
• ኢዮብ የተወለደበትን ቀን ጨለማ እንዲሆን ብርሃን እንዳይኖርበት የረገመውን ቀን ድንግል "የብርሃን እናት" ሆና ተወለደችበት፤ ቅዱስ ያሬድ "ዮም ተወልደት እመ ብርሃን ማለቱም ለዚህ ነበር፡፡
• ኢዮብ የተወለደበትን ቀን "እልልታ አይደረግበት" ብሎ ረግሞት ነበር እመቤታችን ስትወለድ ግን እርግማኑ ተሻረ፤ ፍጥረት ሁሉ "እልል.." አለ፤ የሊባኖስ ተራሮች ብሥራተ ልደቷን ተናገሩ፤ እናት አባቷ እልል አሉ፤ እኛም ከቅዱስ ያሬድ አሁንም " ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም" እያልን እልል...... እንላለን፡፡
• ኢዮብ የተወለደበትን ከቀኖች ተለይቶ ቀን መካን ይሁን ብሎ ቢረግመው "ድንግል እልፍ ሆና" ተወለደችበት፤
"መልአት ምድረ ወሰማያተ ወሊዳ ዋሕደ ወተወሊዳ አሐተ ፤ መልአት ምድረ ወሰማያተ" እንዳለ ባለቅኔ (አንድ ሆና ተወልዳ፣ አንድ ብቻ ወልዳ ሰማዩን ምድሩን ሞላችው)፡፡፡
• ክርስቶስ አዳምን የረገመበትን ዕለተ ዓርብ ተሰቅሎበት መርገምን ሽሮ ዓርብን ቅዱስ ቀን እንዳደረገው ሁሉ እመቤታችንም ኢዮብ ተወልዶ የረገመውን ወር ተወልዳበት ባረከችልን!!!
• ድንግል ሆይ ልደትሽ በረከታችን ነው!!!
• ድንግል ሆይ የልደትሽ ቀን ሙላታችን ነው!!!
2. #ዕርገተ_ክርስቶስ፦
ጥንተ ዕርገት ግንቦት 8 ቀን ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ሰይጣን እስከ ሶስተኛው ሰማይ ድረስ ሄዶ ሰዎችን የመክሰስ ሥልጣን ነበረው፤ አሁን ግን አይችልም! ከምድር እስከ ሰማይ ድረስ በደመ ክርስቶስ ማኅተም ተዘጋ፤ ወደላይ የሚወጡት ክርስቶስና መላእክት፤ ክርስቶሳውያን ብቻ ናቸው፡፡ ከሳሽነት ቀረ፤ አዳም ነጻ ወጣ፤ መንገድ ሁሉ ተባረከ!! ጌታችን ሲያርግ እጆቹን አመሳቅሎ እየባረከን ነበር!!! እየባረከ እንደባረከን የሰይጣንን ክስ አስቀርቶ በአባቱ ቀኝ ተቀመጠ!!! እንጠራለን እንጂ አንከሰስም! በዚህ ወር እስከ ሶስተኛው ሰማይ የወጣው ሰይጣን በዚህ ወር ተባረረ!!!
3. #ልደተ_ቤተ_ክርስቲያን (ርደተ ጰራቅሊጦስ)፦
መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የወረደላቸው በዚህ ወር (ግንቦት 18) ነበር፡፡ ይህ ልደተ ቤተ ክርስቲያን እርግጥ የሆነበት ከ 3000 ሕዝብ በላይ የተጠመቀበት ዕለት ነበር፡፡ ኢዮብ መካን (መኻን) እንዲሆን የረገመውን ቀን መንፈስ ቅዱስ ባርኮት እልፍ አእላፍ ሆነን ተወለድንበት!!!!

#ይህን_ያደረገ_አምላካችን_የተመሰገነ_ይሁን!!!
#የእመቤታችን_የልደቷ_በረከት_ይደርብን!
#ምልጃዋ_ሀገራችን_ይጠብቅልን !!
#ሕሙማንን_ይፈውስልን!!!
#የተወለድንበትን_ቀን_ከምንረግምበት_ፈተና_ሁሉ_እግዚአብሔር_ይሠውረን!!!!
#አሜን!!

#መጋቤ_ሀዲስ_ኢንጂነር_ነቅዐ_ጥበብ
@zemarian
1.3K views18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 21:35:11 #ግንቦት_፩ #ልደታ_ለማርያም
ከሐምሌ 7ቱ
@zemarian
#ክፍል ፩
ጴጥርቃ እና ቴክታ የሚባሉ ቅዱሳን ሰዎች በኢየሩሳሌም በአንድነት ተጋብተው ይኖሩ ነበር:፡እነዚህም በእግዚአብሔር የሚያምኑ የተወደዱ ጻድቃን ደግ ሰዎች ነበሩ:፡ እነዚህም ሰዎች በእግዚአብሔርም በሰውም ዘንድ የበቁ ባለጸጎች ነበሩ:፡ ነገር ግን የሚወርሳቸው ልጅ አልነበራቸውምና መካን ነበሩ:፡አንድ ቀን ጴጥርቃም ቴክታን እኅቴ ሆይ ይህን ሁሉ የሰበሰብነውን ገንዘባችንን ምን እናደርገዋለን ሀብታችንን ልጅ የለን የሚወርሰን:፡ አንቺም መካን ነሽ እኔም ካንቺ በቀር ሌላ ሴት አላውቅም አላት:፡እርሷም ወንድሜ ሆይ አምላከ እስራኤል ለኔ ልጅ ቢነሳኝ አንተም እንደኔው ሆነህ ትቀራለህን? ከሌላ ደርሰህ ውለድ እንጂ ብላ ብታሰናብተው እንደዚህ ያለ ነገር እኳንስ ላደርገው በልቦናዬ እንዳላስበው አምላከ እስራኤል ያውቅብኛል አላት:፡ እሷም አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን የሚያውቅ የለም ትላንትና ማታ በህልሜ ነጭ ጥጃ ከማህጸኔ ስትወጣ ያችም ነጭ ጥጃ ሌላ ነጭ ጥጃ ስትወልድ እንዲሁ እስከ 7ት ትውልድ ሲዋለድ ሰባተኛይቱ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃዋም ፀሃይን ስትወልድ አየሁ አለችው:: እርሱም በጠዋት ከህልም ፈቺ ዘንድ ሂ የነገረችውን ሁሉ ነገረው:፡ ያም ህልም ፈቺ እግዚአብሔር በምሕረቱ አይቷችሇል በሳህሉ መግቧችሁአል 7 አንስት ጥጆች መውለዳቹ 7 ሴቶች ልጆችና የልጅ ልጆች ትወልዳላቹ ከቤታቹ ሰባተኛይቱ ጨረቃ መውለድዋ ከሰው የበለጠች ከመላእክትም የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላቹ የፀሃይ ነገር ግን አልታወቀኝም አለው:፡ እርሱም የነገረውን ሁሉ ሄዶ ነገራት እርሷም እንጃ አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን ማን ያውቃል ብላ ዝም አለች:ከዛም ፀንሳ በ9 ወሯ ሴት ልጅ ወለደች:፡ ስሟንም #ሄሜን ብለው አወጡላት:፡ ሄሜንም አድጋ ለአካለ መጠን ስደርስ አጋብተዋት ሴት ልጅ ወለደች በስምንተኛ ቀኗም #ደርዲ ብለው ስም አወጡላት: ደርዲም አድጋ እንዲሁ ሴት ወለደች እና #ቶና አለቻት:፡ ቶናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ #ሲካር አለቻት፤ ሲካርም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ #ሴትና አለቻት፤ ሴትናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ #ሄርሜላ አለቻት፤ሄርሜላም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ንጽሕት ቅድስት ክብርት የምትሆን እመቤታችንን የምትወልደውን #ሃናን ወለደች:: ይህቺም ሃና በስርዓት በቅጣት አደገች:፡ ለአእምሮ ስትበቃ አካለ መጠን ስደርስ ከቤተ መንግሥት ወገን ከነቅዱስ ዳዊት ወገን ከሆነው ከቅዱስ እያቄም ጋር አጋቧት:: እነዚህ ቅዱሳን እያቄምና ሐና በአንድነት ተጋብተው ሲኖሩ ልጅ አጡ ወደ እግዚአብሔር ዘወትር ሲያዝኑ ሲጸልዩ ውለው ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት አይታ አቤቱ ጌታዬ ለዚች ግእዛን ለሌላት እንስሳ ልጅ የሰጠህ አምላክ ምነው ለኔ ልጅ ነሳኸኝ ብላ ምርር ብላ አለቀሰች፡ እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲፀልዩ ውለው ከዘካርያስ ከሊቀ ካህናቱ ሄደው አቤቱ ጌታችን ሆይ ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ ቤተ እግዚአብሔርን አገልግሎ እንዲኖር እንሰጣለን ሴት ልጅም ብንወልድ ማይ ቀድታ መሶብ ወርቅ ሰፍታ መጋረጃ ፈትላ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር እንሰጣለን ብለው ስዕለት ገቡ::ዘካርያስም እግዚአብሔር ጸሎታችሁን ይስማላቹ ስእለታችሁን ይቀበልላቹ ጻህቀ ልቦናችሁን ይፈጽምላቹ ብሎ አሳረገላቸው፡፡ ከዚያም በኃላ ቅድስት ሐናና ቅዱስ እያቄም ዕለቱን ራእይ አይተው ነገር አግኝተው አደሩ፡፡ ራእዩም እንዴት ነው ቢሉ ኢያቄም 7ቱ ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ አላት ወፍ የተባለው ጌታች መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ነጭነቱ ንጽሐ ባህሪው ነው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ ማለቱ የኢያቄምን ባህርይ ባህር እንዳደረገው እወቅ ሲል ነው 7ቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ልዩ ልዩ ባህሪው፣ ምልአቱ፣ ስፍኀቱ ፣ ርቀቱ፣ ልዕልናው መንግሥቱ ናቸው፡፡ ሐናም እኔም አየሁ አለችው ፡፡ ምን አየሽ ቢላት ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማህጸኔ ስትተኛ አየሁ አለችው::ርግብ የተባለች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት ነጭነቷ ፣ ንጽህናዋ፣ ቅድስናዋ ፣ ድንግልናዋ ነው፡፡ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማኅጸኔ ስትተኛ አየሁ ማለቷ ብስራተ ገብርኤል በጆሮዋ ሰምታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችንን መፀነሷ ነው: ይህንኑም ራእይ ያዩት ሐምሌ 30 ዕለት ነው:: እነሱም እንዲህ ያለ ራእይ ካየን ነገር ካገኘን ብለው ዕለቱን በምንጣፍ አንድ ሣይሆኑ ፈቃደ እግዚአብሔር ቢሆን ብለው አዳምንና ሔዋንን ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሏት ብሎ የተናገረ አምላክ ለኛስ ይነግረን የለምን? ብለው ዕለቱን አልጋ ምንጣፍ ለይተው እስከ 7 ቀን ድረስ ለየብቻቸው ሰነበቱ: ነሐሴ በባተ በሰባተኛው ቀን ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች ዓለሙ ሁሉ ተሰብስቦ ቢመዘን አንድ የራሷን ፀጉር የማያህል ደግ ፍጥረት ትወልዳላቹህና ዛሬ በምንጣፍ አንድ ሁኑ ብሎአችኋል ጌታ ብሎ መልአኩ ለቅድስት ሐና ነገራት በፈቃደ እግዚአብሄር በብስራተ መልአክ #እመቤታችን_እግዝእትነ_ማርያም እሑድ ዕለት ተፀነሰች (በኦሪት ሥርዓት እሁድ ዕለት ባልና ሚስት መገናኘት ልማድ ነበርና እመቤታችን የተፀነሰች ዕለት አይሁድ ቀንተው ተነሱባቸው ቅናቱ እንዴት ነው ቢሉ ሳሚናስ የሚባል የጦሊቅ ልጅ ከኤዶቅ ካጎቱ ቤት ሄዶ ሞተ እነርሱም እንቀብራለን ብለው ባልጋ ይዘው ሲሄዱ ከመንገድ አሳረፉት የሐናም የአጎቷ ልጅ ነበርና ለማልቀስ ብትደርስ ዘመዶቿ ሁሉ ተሰብስበው ሲላቀሱ ቆዩአት: እርሷም አብራ እየዞረች ስታለቅስ ጥላ ቢያርፍበት መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ብድግ ብሎ ተነስቶ #ስብሐት_ለኪ_ማርያም_እሙ_ለፀሐየ_ጽድቅ ለአብ ሙሽራው ለወልድ ወላዲቱ ለመንፈስቅዱስ ጽርሐ ቤቱ ተፈስሒ ደስ ይበልሽ ብሎ ሰገደላት አይሁድ ከዛ ነበሩና ምነው ሳሚናስ ምን አየህ? ምን ትላለህ? ቢሉት ከዚች ከሐና ማህፀን የምትወለደው ኅፃን ሰማይ ምድርን እምቅ አየርን የፈጠረ አምላክ ትወልዳለች እያሉ መላእክት ሁሉ ሲያመሰግኗት ሰማሇቸው እኔንም ያነሳች የፈወሰችኝ ያዳነችኝ እርሷ ናት አላቸው በል ተወው ሰማንህ ብለው ቅናት ጀመሩ:: እመቤታችን እግዝትእነ ማርያም በተፀነሰች በ9 ወር ከአምስት ቀን የግንቦት መባቻ #ዕለት_ግንቦት_፩ተወለደች

#ምንጭ\ነገረ_ማርያም
......
971 views18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ