Get Mystery Box with random crypto!

መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል

የቴሌግራም ቻናል አርማ zemarian — መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል
የቴሌግራም ቻናል አርማ zemarian — መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል
የሰርጥ አድራሻ: @zemarian
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 15.65K
የሰርጥ መግለጫ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤት የሚከናወኑ ተግባራቶች አስመልክቶ ቆየት ያሉ ያሬዳዊ ዝማሬ በሰንበት ትምህርት ቤት ውስጥ ፣የሰንበት ት/ቤታችን ወቅታዊ ትምህርቶና የቤተክርስቲያን ወቅተዊ ጉዳዮችን ለማግኘትና ለመማማር @zemariann ይቀላቀሉን፡፡
ለማንኛውም አስተያየት @mzbot_bot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-04-12 21:41:16 ዘማሪት መቅደስ መሃሪዬ
ክራር ኢዮሲያስ አበራ
@zemarian
232 views18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 21:41:16 ከቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን
በገና
ዘማሪ ዳግምና
ዘማሪት ብሩክታይት
@zemarian
226 views18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 21:41:16 @zemariian
220 views18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 21:41:16 አንድም፦ ዘይት መሥዋዕት ኦሪት ነው። አንተም መሥዋዕት ትሆናለህ መሥዋዕተ ሐዲስ ነህ ሲሉ ።

-> ሕዝቡ ለዳዊት ልጅ መድኀኒት መባል ይገባል እያሉ ህፃናት ይመራሉ ሽማግሌዎች ይከተላሉ ይላል። ከዚያ የነበሩት ሕፃናት ፮ ዓመት ፯ ዓመት የሆናቸው አባት እናታቸው ለበዓል ሲወጡ ተከትለው ወጥተው፡፡ የ፵ ቀን የ፹ ቀን ሕፃናት እናት አባታቸው ለበዓል ሲወጡ
ከናታቸው ጀርባ እየወረዱ የፊቱ ብርሃን ብርሃነ ፀሐይን ሲበዘብዛት አይተው ጌትነቱን ገልጾላቸው አእምሮ ጠባይዕ ቀንቶላቸው
እውቀት ተሰጥቷቸው ሆሣዕና በአርያም
ብለው አመስግነውታል ።

- ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና
በአርያም፦
ከአርያም የተገኘ መድኃኒት አንድም፦ በአርያም የሚኖር ፥ አንድም፦ በልዕልና ጸንቶ የሚኖር መድኃኒት ይህ ነው ማለት ነው።

-> እነዚህ ሁሉ ሲያመሰግኑት ሰምተው ካህናትና ፀሐፍት በቅናት እኒህ ሕፃናት የሚሉትን አትሰማምን? አሉት አዎን ይገባኛል ብዬ ነው አላቸው ከልጆች ሕፃናት ምስጋና አዘጋጀ የተባለውን አላነበባችሁምን? መዝ.8፥2 እኒህ ህፃናት ዝም ቢሉ ደንጋዮች ያመሰግኑኛል ብሎ መለሰላቸው(ሉቃ 19፦40) ደንጋይ እንዲመሰክር ትንቢት ነበርና (ኢያ 24÷26-27, ማቴ.3፥9) ስለዚህ ዓለት የማይለወጥ የእግዚአብሔር ምሳሌ ነው:: (2ሳሙ 22÷2)፡፡

-> መዝሙር ዘሆሳዕና ፦ ወእንዘ ሰሙን

-> ምንባብ ዘቅዳሴ ዕብ 9፥11-ፍም::
1ጴጥ 4፥1-12::
ግ.ሐዋ 28፥11-ፍም

-> ምስባክ " እምአፈ ደቂቅ ወሕጻናት አስተዳሎከ ስብሐተ በእንተ ጸላዒ ከመ ትንስቶ ለጸላዒ ወለገፋዒ " መዝ 8፥2

-> ወንጌል ዮሐ.12፥12-26

-> ቅዳሴ ዘጎርጎርዮስ

አምኃ ሥላሴ / መኩሪያ ተስፋዬ
232 views18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 21:41:16 ✥ በዕለተ ሆሳዕና የተፈጸሙ ድንቅ ምሥጢራት

-> ሆሳዕና የዐቢይ ጾም ስምንተኛ ሣምንት

-> ሆስዕና :- እባክህ አድነን ማለት ነው:: መዝ 117፥25፣ ማር 11÷10፡ ዮሐ 12፥13)

. ሆሳዕና ለወልደ ዳዊት እምሆሳዕናሁ አርአየ ተአምረ ወመንክረ ፡፡ መድኃኒትነት ፤ መድኃኒት መኾን፤ መድኃኒት መባል ላንተ ለዳዊት ልጅ ይገባሃል። ማለት ነው። (ማቴ 21÷9:: ቅዳ ጎር)::

-> ሆሳዕና፤ የበዓል ስም፤ የሰሌን በዓል፤ ሰሌን ይዘው እያመሰገኑ የሚያወዱሰበት ለብሉይ የመጸለት 7ኛ ቀን፤ ለሐዲሱ ግን ከትንሣኤ
በፊት ያለ እሑድ፡፡ (ዘሌ 23፥39-44 /ስንክ መስ3)፡፡

-> በዚህ እለት የእስራኤል ህዝብ የዘንባባ ዝንጣፊ በመያዝ ሆሣዕና በማለት እየጮኹ ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ አጀቡት ትንቢቱ ይፈፀም ዘንድ ውርንጫውን በወይን ግንድ ያስራል ተብሎ እንደ ተፃፈ (ዘፍ49÷1:: ዘካ 9፥9-10:: ኢሳ 40÷10) ያን ጊዜ ጌታ ከደቀመዛሙርቱሰቱን ላከ ‹‹በፊታችሁ ወደ አለ ሀገር ሂዱ አህያዋን ከውርንጭላው ጋር ታስራ ታገኛላችሁ ፈትታችሁ አምጡልኝ) አላቸው

. ሰው ሁሉ ከማዕሰረ ኃጢአት ለመፈታት እንደደረሰ ለማጠየቅ ፈትታችሁ አምጡልኝ አለ።

አንድም፦ ለሐዋርያት የተሰጣቸውን ሥልጣነ ክህነት ያስረዳል (ማቴ.18፥18)

- ምን ታደርጋላችሁ? የሚል ሰው ቢኖር ጌታቸው ይፈልጋቸዋል በሉ አላቸው
. በተፈጥሮ ጌታቸው ነውና (ዮሐ.1፥3)

- ይህ ሁሉ የተደረገው ጻድቅ የባሕርይ አምላክ የዋህ ንጉሥሽ በውርንጫና በአህያይቱ ተቀምጦ ይመጣልና ብላችሁ ለጽዮን ልጅ ንገሯት ብሎ ነቢዩ የተናጋረው ይደርስ ዘንድ ነው:: (ዘካ 9፥9-10:: )

. ልጅ እስራኤል ናቸው ጽዮን ኢየሩሳሌም ናት በሀገሪቱ ሰዎቹን መናገር ነው የአማራ ልጅ ፣ የትግሬ ልጅ እንዲሉ

. አንድም፦ ልጅ አይለወጥም ጽዮን ህግናት እናት ልጆቿን ሠርታ ቀጥታ እንድታሳድግ ሕግም ሕዝቡን ሠርታ ቀጥታ ታኖራለች


-> ደቀመዛሙርትም እንደ ታዘዙት ውርንጫዋን ከእነ አህያይቱ አመጡለት ልብሳቸውን ጎዘጎዙለት

. ኮርቻ ይቆረቁራል ልብስ አይቆረቀርም
የማትቆረቁር ሕግ ሠራህልን ሲሉ ።

. አንድም፦ ኮርቻ ያጽራል ልብስ አያጽርም :: የማታጽር ሕግ ሠራሕልን ሲሉ።

. አንድም፦ ልብስ ከአካል ያለውን ነውር ይሰውራል አንተም ከባቴ አበሳ ነህ ሲሉ

-> በሁለቱም ጌታ በአንድ ጊዜ ተቀመጠባቸው ከደብረ ዘይት እስከ ኢየሩሳሌም 16 ምዕራፍ ነው 14ቱን በእግር ሂዲል ሁለቱን በአህያይቱ ሂዷል ፥ በዕዋል(ውርንጫ) ሆኖ ቤተመቅደሱን 3 ጊዜ ዙራል

. ምሳሌ 14ቱን በእግሩ መሄዱ፤ አሥሩ (10) የአስርቱ ቃላት አራቱ (4) የአራቱ ኪዳናት (ኪዳነ ኖህ፣ ክህነተ መልከ ፄዴቅ፣ ግዝረተ አብርሃም፣
ጥምቀተ ዮሐንስ) ናቸው

በአህያ መቀመጡ ለምን ቢሉ ትንቢቱን ምሳሌውን ለመፈጸም ነው።
. ትንቢቱ አጠፍዕ ሠረገላ እም ኤፍሬም ወአፍራሰ እምይሁዳ (ዘካ.9፥10)

. ምሳሌው ቀድሞ አባቶች ነቢያት ዘመነ ጸብዕ የሆነ እንዲሆነ በፈረስ ተቀምጠው ዘገር ነጥቀው ይታያሉ። ዘመነ ሰላም የሆነ እንደሆነ በአህያ ተቀምጠው መነሳንስ ይዘው ይታያሉና ዘመነ ሰላም ደረስ ሲል ትንቢቱን በአወቀ አናግሮአል ምሳሌውንም አስመስሎአል፡፡

. ምሥጢሩ እንደምነው ቢሉ በአህያ የተቀመጠ ሸሽቶ አያመልጥም አሳዶ አይዝም ከሹኝ አልታጣም ካልሹኝ አልገኝም ሲል ነው::

አንድም፦ ከመ እንተ ዕድግት ነፍስቶሙ እንዲ በንጹሓን ምእመናን አድራባቸው እኖራለሁ ሲል


ዕድግት የእስራኤል ምሳሌ ቀንበር የለመደች እንደ ሆነች እስራኤልም ሕግ መጠበቅ ለምደዋልና ፥ ዕዋል የአሕዛብ ምሳሌ ቀንበር ያልለመደች እንደ ሆነች አሕዛብም ህግ መጠበቅ ያለመዱ ናቸውና።

. አንድም እድግት የኦሪት፣ ዕዋል የወንጌል ዕድግት ቀንበር መሸከም የለመደች እንደሆነ ኦሪትም የተለመደች ህግ ናትና ፥ ዕዋል ቀምበር መሸከም ያልመደች እንደሆነ ወንጌልም ያልተለመደች ሕግ ናትና። አንድም:- ሕግ መጠበቅ ላልለመዱ ለአሕዛብ ወንጌልን አስተምሩ ሲል ነው።

-> እኒህስ አህዮች ከምን የተገኙ ናቸው ቢሉ ለገበያ ብለው ያዘዋቸው የመጡ ናቸው ኋላስ ምን አድርጓቸዋል ቢሉ ኋላማ ምን ያደርጓቸዋል
ለባለቤታቸው መልሷቸዋል ።


የሚበዙ ሕዝብም ልብሳቸዉን በጎዳና አነጠፉ አንተ የተቀመጥክባት አህያ መሬት መንካት አይገባትም ሲሉ

. አንድም :- በኢዩ ልማድ ፦
- ኤልሳዕ ከደቂቀ ነቢያት አንዱን ቀርነ ቅብዑን ይዘህ ሂደህ ኢዩን ቀብተህ አንግሠኸው ፈጥነህና፤ ከሰው ጋራ አትነጋገር ብሎ ላከው ። ቢሄድ ኢዩን ከባልንጀሮቹ ጋራ ሲጫወት ባደባባይ ተቀምጦ አገኘው ብየ መልእክት አለው ። እምኔነኑ እምኅበ መኑ አለው ። ከኛን ነው ከሌላ ቢለው ኀቤከ መልአክ ወዳንተ ተልኬ መጥቻለሁ አለው ። ከእልፍኝ ይዞት ገባ ።
ከመዝ ይቤ አምላከ እስራኤል ቀባዕኩከ ትንግሥ ላዕለ ሕዝብየ እስራኤል ብሎ ቀብቶት ሩጦ ሄደ ።

ኋላ ኢዩ መጣ ። ምን አለህ ንገረን አሉት ። ኢተአምሩኑ ከመ በከ ይዛዋዕ ዝ ብእሲ ይህ ሰው ዋዛ ፈዛዛ እንዲናገር አታውቁምን አላቸው ።
ዕውነቱን ንገረን አሉት። ንገረንማ ካላችሁኝ ትነግሣለህ ብሎ ቀብቶኝ ሄደ አላቸው። እኛስ ሌላ ምን እንሻለን ብለው እኩሌቶቹ አንጽፈዋል ፤ እኩሌቶቹ ጋርደዋልና በዚያ ልማድ ።


ሌሎችም ቀጠል እየቆረጡ ከመንገድ ያነጥፉ ነበር።
-> ሰሌን (ዘንባባ) ነው ያሉ እንደሆነ ፦
. አብርሐም ይስሃቅን ፥ ይስሃቅም ያዕቆብ በወለዱ ጊዜ የሰሌን ቅጠል ይዘው እግዚአብሔርን አመሰግነዋል፡፡(ኩፋ 13፥20-22)
. እስራኤልም ከግብጽ በወጡ ጊዜ እስከ ሰባት ቀን ሰሌን በመያዝና በማክበር እግዚአብሔርን አመስግነዋል (ዘሌ23÷40-42፡፡
ዮሐ12፥13)
. ዮዲት ጠላትዋን ሆሎፎርኒስን ድል ባደረገች ጊዜ ይህንን ሥርዓት ፈጽመዋል፡፡ በዚህ ልማድ በሰሌን አመስግነዋል።

አንድም፦ ሰሌን (ዘንባባ) እሾኻም ነው ትእምርተ ኃይል ትእምርተ መዊዕ አለህ ሲሉ ።

አንድም፦ ዘንባባ ደርቆ እንደገና ህይወት ይዘራል የደረቀ ሕይወታችንን የምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው

አንድም፦ ሰሌን እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል አንተም ባሕርይህ አይመረመርም ሲሉ

- ማስታወሻ ፦ በኢየሩሳሌም ሰሌን (ዘንባባ) የለም (አይበቅልም ነበር) ጌታችን በሕፃንነቱ ወደ ግብፅ በተሰደደ ጊዜ ከመንገድ አግኝቷት ሂደሽ በእስራኤል ደብረ ዘይት ተተከይ ብሎ አዟት ተነቅላ ሂዳ ተተክላለች። ይህም ይታወቅ ዘንድ ዛሬ በእስራኤል በደብረ ዘይት ከተማ ዘንባባ በብዛት ይገኛል። ሕዝቡም ለጌታችን ከዚያ ይዘው ወደ ኢየሩሳሌም መጥተው ነው ያነጠፉለት።


-> ተምር ነው ያሉ እንደሆነ ፦
. ተምር ልዑል ነው ልዑለ ባሕርይ ነህ ሲሉ

አንድም፦ ተምር ፍሬው አንድ ነው (የተምር ዛፍ ፍሬ በውስጡ ያለው ፍሬ አንድ ነው ) ዋህዶ ባሕርይ ነህ ሲሉ

አንድም፦ ተምር ፍሬው በእሾህ የተከበበ ነው
ባሕርይህ አይመረመርም ሲሉ

አንድም፦ የቴምር ዛፍ ፍሬ ጣፋጭ ነው፦ በኃጢአት የመረረውን ሕወታችን የምታጣፍጥልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው።


-> ዘይት (የወይራ ዛፍ ዝንጣፊ) ነው ያሉ እንደሆነ :-
. የወይራ ዛፍ (ዘይት) ጽኑዕ ነው ጽኑዓ ባሕርይ ነህ ሲሉ ።

አንድም፦ ዘይት ብሩህ ነው ብሩሃ ባሕርይ ነህ ሲሉ ። እርሱ በጨለማ ኃጢአት ፣ ኦሪት ይኖር ለነበረ ሕዝብ ብርሃን የሆነ እርሱ ነውና።
353 views18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 23:25:28 ለክርስትና , ለሰርግ የዲኮር ስራዎችን ማሰራት ይፈልጋሉ ?


ለ ሰርግ                            ለ ክርስትና
ለ ልደት                            ለ ቀለበት
ለ ገዓት                             ለ ሽምግልና
ለ ተማሪዎች ምረቃ           ለ ልጆች ልደት
ለ ቤት ምርቃት                   ለ ሆቴል ምረቃ
ለ ስብሰባ አዳራሾች          ለ ቤተሰብ ኘሮግራሞች
ለ ሰርግ ለመኪና ዲኮር
በ ቤተክርስቲያን ስርዓት ለሚፈፀሙ ሰርጎች እና ኘሮግራሞች

ለተለያዮ ዝግጅቶችም ጭምር የተለያዮ የዲኮሪሽን ስራዎችን እንሰራለን እንዲሁም የተለያዮ የዲኮር እቃዎችን እናቀርባለን !
       

     
              ይህን ይጫኑት  ...  ይህን ይጫኑት

█▓▒░        ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻       ▒▓█
█▓▒░         ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻      ▒▓█
█▓▒░         ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻      ▒▓█
█▓▒░        ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻       ▒▓█


Tel .   +251961064953
                 +251703504953
.
341 views20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 18:50:48 ፭. ዕለተ ዓርብ
ዓርብ ስቅለት የዕዳ ደብዳቤያችን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ለመጨረሻ ጊዜ የተደመሰሰበት፤ ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ የወጣንበት ዕለት ስለኾነ ‹የድኅነት ቀን› ይባላል፡፡ ጌታችን ከተያዘባት ሰዓት አንሥቶ አይሁድ ከቀያፋ ወደ ሐና፣ ከሐና ወደ ቀያፋ ሲያመላልሱት አደሩ፡፡ ሲነጋ ከቀያፋ ወደ ጲላጦስ አደባባይ አስረው ወሰዱት (ማቴ. ፳፯፥፩-፶፯)፡፡ አይሁድ ይህን አጥፍቶአል የሚሉት ነጥብ ሳይኖራቸው ነውና ጌታችንን ለፍርድ ያቀረቡት ጲላጦሰ እነርሱ ወደ ተሰባሰቡበት ቦታ ወጥቶ ‹‹ይህን ሰው ወደ እኔ ያመጣችሁበት በደል ምንድን ነው?›› ሲል በጠየቃቸው ጊዜ በቂ ምላሽ አላቀረቡም፡፡
‹‹ክፉ የሠራ ባይሆንስ ወደ አንተ ባላመጣነውም ነበር›› በሚል የሸፍጥ ቃል ሲያጕረመርሙ ጲላጦስ መልሶ ‹‹እኔ ምንም ጥፋት አላገኘሁበትም፤ እናንተወስዳችሁ እንደ ሕጋችሁ ፍረዱበት፤›› አላቸው፡፡ አይሁድም ኦሪት ‹‹ኢትቅትል ብእሴ ጻድቀ ወኀጥአ ኢታኅዩ፤ ጻድቅን ሰው አትግደል፤ ኀጥኡንም ከፍርድአታድን፤›› ትላለችና ‹‹እኛስ ማንንም ልንገድል አልተፈቀደልንም፤›› ብለዋል (ዮሐ. ፲፰፥፳፰-፴፩)፡፡ ይኸውም መንፈስ ቅዱስ ‹‹በሕጋችን ጻድቀ ባሕርይክርስቶስን መግደል አይገባንም ሙሉ በሙሉ ጥፋተኞች ነን፤›› ሲያሰኛቸው ነው፡፡ በኋላም እርሱ ሞቶ ዓለም ይድን ዘንድ ወደ ምድር መጥቷልና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ ጥፋቱ ሞት ተፈረደበት፡፡ ስለዚህም ገርፈው ሰቀሉት፡፡
ጌታችን ሲሰቅልም የሚከተሉት ሰባት ተአምራት ተፈጽመዋል፤
፩. ፀሐይ ጨለመ፤              ፬. የቤተ መቅደስ መጋረጃ ተቀደደ፤         ፯. ሙታን ተነሡ (ማቴ. ፳፯፥፶፩-፶፬)፡፡
፪. ጨረቃ ደም ኾነ፤            ፭. አለቶች ተፈረካከሱ፤
፫. ከዋክብት ረገፉ              ፮. መቃብራት ተከፈቱ፤          
ከስድስት ሰዓት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ጨለማ ኾኖ ከቈየ በኋላ ከዘጠኝ እስከ ማታ እንደ ተለመደው ብርሃን ኾኖአል፡፡ ‹‹ወፍና ሠርክ ይበርህ ብርሃነ ፀሐይ›› እንዲል (ዘካ. ፲፬፥፯)፡፡ በዚህ ዕለት ሰባት መስተፃርራን (ጠበኞች) ታረቁ፤ ተስማሙ፡፡ እነዚህም፡- ሰውና እግዚአብሔር፣ ሰውና መላእክት፣ ሕዝብና አሕዛብ፣ ነፍስና ሥጋ ናቸው (ኤፌ. ፪፥፲፤ ቈላ. ፩፥፳)፡፡ ጌታችን ጠዋት በሦስት ሰዓት ተገረፈ፤ በስድስት ሰዓት ተሰቀለ (ማቴ. ፳፯፥፩-፴፯፤ ሉቃ. ፳፫፥፩-፵፬፤ ዮሐ. ፲፱፥፩)፡፡
በዘጠኝ ሰዓት ጌታችን በውኃው ተጠምቀን፣ ደሙን ተቀብለን የእግዚአብሔር ልጆች እንኾን ዘንድ ከቀኝ ጎድኑ ጥሩ ውኃ፣ ትኩስ ደም አፈሰሰልን (ዮሐ. ፲፱፥፴፬)፡፡ በዐሥራ አንድ ሰዓት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከመስቀል አውርደው ሽቶ እየረበረቡ በድርብ በፍታ ገንዘው ቀበሩት (ሉቃ. ፳፫፥፶-፶፬፤ ዮሐ. ፲፱፥፴፰-፵፪)፡፡ ቅድስት ነፍሱ ወደ ሲኦል ወርዳ ነፍሳትን ነጻ አወጣች (፩ኛ ጴጥ. ፫፥፲፱)፡፡ በዚህ ጊዜ በርሃነ መለኮቱ በሲኦል ተገለጠ፡፡ ስለዚህም ‹‹ንሴብሖ ለእግዚአብሔር›› እየተባለ ይዘመራል፡፡ ከሆሣዕና አንሥቶ ተከልክሎ የነበረው ኑዛዜ ይናዘዛል፤ ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል፡፡
፮.ቀዳም ሥዑር
ቀዳም ሥዑር ይባላል፡፡ በዚች ዕለች ከድሮው በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረችው ቅዳሜ ትባላለች።
ለምለም ቅዳሜ፡- ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት ስለሆነ በዚህ ተሰይሟል፡፡ ቀጤማውንም ምእመናን እስከ ትንሣኤ ሌሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል፡፡በቀዳም ስዑር ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ ቃጭል /ቃለዓዋዲ/ እየመቱ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ የሚለውን ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር፤ ጌታ በመስቀሉ ሰላምን እንደሰጠን እና ትንሣኤውንም እንደገለጠልን በማብሰር፤ ቄጤማውን ለምእመናን ይሰጣሉ፡፡ ምእመናኑም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውል ገጸ በረከት ያቀርባሉ፡፡ ቄጤማውንም በራሳቸው ያስራሉ፡፡ ይህም አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ ያሠሩበትን ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡ 
የቀጤማው አመጣጥና ምስጢርም ከአባታችን ከኖኅ ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ምድር በማየ አይኅ /በጥፋት ውኃ/ በጠፋችበት ወቅት የኖኅ ታማኝ መልእክተኛ ርግብ የውኃውን መጉደል ያበሰረችው ቀጤማ ይዛ በመግባት ነው፡፡ ዛሬም ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች የኃጢአት ውኃ ጐደለ፣ የኃጢአት ውኃ ጠፋ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ነጻነት ተሰበከ ታወጀ በማለት ካህናት ቄጠማ ይዘው ምእመናንን ያበሥሩበታል፡፡
ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል፦ ቅዱስ ቅዳሜ መባሉ ቅዱስ የሆነ እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ከፈጠረ በኋላ በዚህ ቀን ከሥራው ሁሉ ያረፈበት ነው፡፡ በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ሥራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ፣ በነፍሱ ሲዖልን በርብሮ ባዶዋን አስቀርቷታል፡፡ በዚያ ለነበሩት ነፍሳትም የዘለዓለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ከሌሎቹ ዕለታት የተለየ ዕለት ለማለት ቅዱስ ቅዳሜ ተብሏል፡፡
ምእመናን ሆይ፣ በአጠቃላይ ሥርዓተ ሕማሙን፤ ሰሙነ ሕማማት ብለው የተለየ ሥርዓት አውጥተው አባቶቻችን ተግተው ያቆዩልንን ሥርዓተ መላእክት ልንጠብቀውም ልንጠቀምበት ይገባል፡፡ የዕለታቱን ክብርና ስያሜ ከማወቅና ከመረዳት ጋር በዕለታቱ የታዘዙትን ሃየማኖታዊ ግዴታዎችን መወጣት ከሁላችንም ይጠበቃል፡፡
 
                    ወስብሀት ለእግዚአብሔር
703 views15:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 18:50:48 ከዚህም በኋላ እርሱ ከባሕርይ አባቱ ከእግዚአብሔር አብ ጋር ስላለው አንድነትና ክብር ለሐዋርያት ካስተማራቸው በኋላ ‹‹ኢየሱስም ይህን ተናግሮ አትክልት ወደ አለበት ሥፍራ ወደ ቄድሮስ ወንዝ ማዶ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወጣ፤ በዚያም ገባ›› ተብሎ እንደተጻፈ፡፡ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ለጸሎት ወደ አትክልቱ ሥፍራ ሄደ፡፡ የአስቆሮቱ ይሁዳም ይህችን ሥፍራ  ቀድሞ ጌታ ይወዳት እንደነበር ያውቃልና የካህናት አለቆችንና ጸሐፍት ፈሪሳውያንን እንደዚሁም ሌሎች ፋና ጋሻና ጦርም የያዙትን ጭፍሮች አስከትሎ ወደ እርሱ መጣ፡፡ በዚህም ጊዜ ጌታችን ደቀ መዛሙርቱን ‹‹ተነሡ እንሂድ! እነሆ አሳልፎ የሚሰጠኝ ቀርቧል›› አላቸው፤ ከዚያም  ወደ እነርሱ ቀርቦ ‹‹መነሃ ተኀሥሡ ማንን ትፈልጋላችሁ›› አላቸው፤ እነርሱም ‹‹ንሕነሰ ነኀሥሥ ኢየሱስሃ ናዝራዌ፤ ናዝራዊውን ኢየሱስን እንፈልጋለን›› አሉት፡፡ (ዮሐ.፲፰፥፩-፯)ያንጊዜም ይሁዳ ወደ እርሱ ቀርቦ፤ ‹‹መምህር ሆይ ቸር አለህን፤ ሰላም ላንተ ይሁን›› ብሎ ሳመው፤ መሳሙም ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ መካከል የትኛው እንደሆነ ለአይሁድ ለይቶ ለማሳየት የተጠቀመው የጥቆማ ምልክት ነበር፡፡ ምክንያቱም የጌታ መልክና የወንጌላዊው የዮሐንስ መልክ ይመሳሰልባቸው ነበርና ለይቶ ሲያሳያቸው ነው፤ ያንጊዜም ጌታችን ‹‹በስኢምኑ ታገብኦ ለወልደ ዕጓለ እመሕያው፤ የሰውን ልጅ በመሳም አሳልፈህ ትሰጠዋለህን?›› ብሎታል፡፡ (ሉቃ.፳፪፥፵፰)  ከዚህም በኋላ ከእርሱ ጋር የመጡት አይሁድና ጭፍሮቻቸው ጌታ ኢየሱስንም በስድስተኛው ሰዓተ ሌሊት ያዙት፡፡ ወደ ሽማግሌዎችና ወደ ሊቀ ካህናቱ ወደ ቀያፋ ወሰዱት፡፡ ጴጥሮስ ግን ከሩቅ ሆኖ ይመለከት ነበር፤ የነገሩንም ፍጻሜ ያይ ዘንድ ከአንድ ቅጥር ገብቶ ተቀመጠ፡፡ አይሁድም  ‹‹ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፤ በሦስተኛው ቀን እሠራዋለሁ›› ብሏል ብለው ከሰሱት፤ ለዚህም ሁለት የሐሰት ምስክሮችን በክርስቶስ ላይ አመጡ፡፡ ሊቀ ካህናቱም ተነሥቶ ‹‹እንዲህ ሲያጣሉህ አትሰማምን›› አለው፡፡ ጌታችን ግን ምንም አልመለሰለትም፤ ሊቀ ካህናቱም ‹‹ክርስቶስ ተብሎ የተነገረልህ የእግዚብሔር ልጅ አንተ እንደሆንክ ንገረኝ›› አለው፡፡ ጌታችንም ‹‹አንተ አልክ›› አለው፤ ያን ጊዜ ሊቀ ካህናቱ ተናዶ ልብሱን ቀደደው፤ ራሱንም በብረት ዘንግ መቱት፤ ይህም ጊዜ የመከራው ጅማሬ ነበር፡፡ (ማቴ.፳፮፥፷፩-፷፬)
ለ. የምሥጢር ቀን፡- ከሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን መካከል አንዱ የሆነው ምሥጢረ ቊርባን የተመሠረተው በዚች ዕለት ነውና ይህቺ ዕለት የምሥጢር ቀን ተብላ ትጠራለች፡፡  መድኃኒታችን ክርስቶስ በዚች ዕለት ኀሙስ ለዓርብ ምሽት በሁለተኛው ሰዓተ ሌሊት  ኅብስቱን ባርኮ ለዐሥራ ሦስት ከፈተተ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጥቶአቸዋል፡፡ ‹‹እንጀራን አንሥቶ ባረከ፤ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና፡- እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ሥጋዬ ነው አለ፡፡ ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖ ሰጣቸው፤ እንዲህም አለ፡- ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስሰው የሐዲስ ኪዳን ደሜ ነው›› ተብሎ እንደተጻፈ፡፡ ዐሥራ ሦስተኛውን ደግሞ ምንም እንኳን የሚጠቅመው ባይሆንም ለእርሱ የሚቀበለው አድርጎታል፡፡ ‹‹ጥዒሞ አጥዐሞሙ፤ ቀምሶ አቀመሳቸው›› እንዲል፡፡ አንድም አብነት ለመሆን እንደዚሁም ነገ በመልዕልተ መስቀል አሥራ ሦስቱን ሕማማተ መስቀል እቀበላለሁ ሲል ነው፤ ጌታ ይህን አርአያነት ባያደርግልን ኖሮ ዛሬ ካህኑ የጌታን ሥጋና ደም ሳይቀበል አቀብሎ ብቻ በሄደ ነበርና ይህን ሥርዓት ለማስተማር ነው፡፡ (አንድምታ ቅዳሴ ማርያም)
በዚች ዕለት የቅዳሴ አገልግሎት የሚፈጸም ሲሆን የቅዳሴው ሥርዓትም ዝቅ ባለ ድምጽ በለሆሳስ ነው፡፡ የቃጭሉን አገልግሎት የሚተካው ጸናጽል ሲሆን ይህም አይሁድ ጌታችንን ሊይዙት በመጡ ጊዜ ድምጻቸውን ዝግ አድርገው በለሆሳስ እየተነጋገሩ መምጣታቸውን ለማሰብ ነው፤ በቅዳሴውም ጸሎተ ተአምኆ፣ ሥርዓተ ኑዛዜ የማይደረግ ሲሆን ሥርዓተ ቊርባን ግን ይፈጸምበታል፡፡ ይህም የሚደረገው ጌታችን ለእኛ ለሰው ለምእመናን ወገኖቹ የሰጠውን ዘለዓለማዊ ቃል-ኪዳን ለማሰብ ነው፡፡ በዚችም ዕለት ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ቀድመው ራሳቸውን በንስሓ በማዘጋጀት ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ይቀበሉባታል፡፡
ሐ.. የሕፅበተ እግር ቀን፡- በዚች ዕለት በመጀመሪያው ሰዓተ ሌሊት በመጽሐፍ ‹‹ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤ በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበት ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ። ወደ ስምዖን ጴጥሮስም መጣ እርሱም፦ጌታ ሆይ፥ አንተ የእኔን እግር ታጥባለህን? አለው። ኢየሱስም መልሶ፦ እኔ የማደርገውን አንተ አሁን አታውቅም፥በኋላ ግን ታስተውላለህ አለው። ጴጥሮስም የእኔን እግር ለዘለዓለም አታጥበኝም አለው። ኢየሱስም  ካላጠብሁህ ከእኔ ጋር ዕድል የለህም ብሎ መለሰለት። ስምዖን ጴጥሮስም ጌታ ሆይ እጄንና ራሴን ደግሞ እንጂ እግሬን ብቻ አይደለም አለው። ኢየሱስም፦ የታጠበ እግሩን ከመታጠብ በቀር ሌላ አያስፈልገውም፥ ሁለንተናው ግን ንጹሕ ነው፤ እናንተም ንጹሓን ናችሁ፤  ነገር ግን ሁላችሁም አይደላችሁም አለው። አሳልፎ የሚሰጠውን ያውቅ ነበርና፤ ስለዚህ፦ሁላችሁ ንጹሓን አይደላችሁም አለ። እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ፥ እንዲህም አላቸው፦ያደረግሁላችሁን አስተውላችኋልን? እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ። እንግዲህ እኔ መምህርና ጌታ ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል። እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና›› ተብሎ በወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ እንደተጻፈ፡፡ (ዮሐ.፲፫፥፬-፲፭)
ጌታችን ተጠምቆ ተጠመቁ ጾሞም ጹሙ እንዳለን ጸልዮ ጸልዩ፤ ሰግዶም ስገዱ ሲለን እንደዚሁም የደቀመዛሙርቱን እግር አጥቦ እናንተም እንዲህ አድርጉ ብሎ አርአያነቱን ሲያሳየን መምህረ ትሕትናነቱን ሲገልጥልን ነው፡፡ ዛሬም ከፓትርያርኩ ጀምሮ ሊቃነ ጳጳሳቱና ካህናቱ ሁሉም በየመዓርጋቸው የምእመናኑን እግር ዝቅ ብለው የሚያጥቡት የጌታን የትሕትና ሥራ ለማሰብ ነው፡፡
በዚህም ጊዜ ከውኃው በተጨማሪ የወይራና የወይን ቅጠልንም ለሥርዓቱ ማስፈጸሚያነት እንጠቀምባቸዋለን፤ ምሥጢሩም ወይራ ጽኑዕ ነው፡፡ ይህም ክርስቶስ ጽኑ መከራ መቀበሉን የሚያስረዳ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም እኛም የእርሱን መከራ ለመቀበል ዝግጁ ነን ለማለት ነው፡፡ የወይኑ ቅጠል ደግሞ በወይን የተመሰለ ደሙን አፍስሶ ለምእመናን የሕይወት መጠጥ ይሆናቸው ዘንድ መስጠቱን ለማዘከር ሲሆን በዚች ዕለት ጌታችን የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠብ የፈጸመው የኅጽበተ እግር ሥርዓትም ለካህናትና ለምእመናን የትሕትና ሥራን ለማስረዳት መሆኑን ‹‹አንትሙሰ ከመዝ ግበሩ ለቢጽክሙ፤ እናንተም ለባልንጀሮቻችሁ እንዲሁ አድርጉ›› በማለት ነግሮናል፡፡
የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትም በቀኝና በግራ በመቆም ‹‹ሐዋርያቲሁ ከበበ እግረ አርዳኢሁ ሐፀበ›› እያሉ ይዘምራሉ፡፡ ይህ ሥርዓት ከተጠናቀቀ በኋላ ሥርዓተ ቅዳሴው ተከናውኖ ምእመናን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ይቀበላሉ፡፡ (ማቴ.፳፮፥፳፮፣ዮሐ.፲፫፥፲)
537 views15:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 18:50:48                                                            ሰሙነ ሕማማት
ሰሙነ ሕማማት ተብሎ የሚጠራው ወቅት ከዐቢይ ጾም መጨረሻ ከሆሣዕና ዋዜማ ጀምሮ እስከ ትንሣኤ ባሉት ቀናት ውስጥ ያለው ሳምንት ነው፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ ይህንን ወቅት አስመልክቶ  በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ‹‹ውእቱ ነሥአ ደዌነ ወጾረ ሕማመነ፤ እርሱ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ፤ ሕማማችንንም ተሸከመ፤›› በማለት የነገረ ሕማማቱን ምሥጢር አስቀድሞ ተናግሮአል፡፡ በዚህም መሠረት በኋለኛው ዘመን እግዚአብሔር ወልድ ስለኛ ስለ ሰው ልጆች ድኅነት ሲል ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍስዋም ነፍስ ነሥቶ በፈቃዱ ሰው ሆኖ በፈቃዱ መከራ መስቀልን ተቀበለ፡፡ በመስቀሉም ላይ ሳለ በፈቃዱ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጠ፡፡ በዚህም መሠረት እኛም በእርሱ በአምላካችን የሆነበትን መከራ መስቀሉን ሁሉ የምናስብበት ሳምንት በመሆኑ ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ (ኢሳ.፶፫፥፬፣ማቴ. ፰፡፲፯፣ዮሐ.፩፥፳፱)
በዚህ ሳምንት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጅ በሙሉ ያደረገውን ትድግና ቅዱሳት መጻሕፍት በተለይም ግብረ ሕማማት የተባለው የቤተ ክርስቲያናችን መጽሐፍ ነገረ ሕማማቱን መከራ መስቀሉን በሰፊው ይናገርለታል፡፡ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችንም መድኃኒታችን ክርስቶስ አንዳች በደል ሳይኖርበት በሰውነቱ የደረሰበትን
የሰሙነ ሕማማት ዕለታት ስያሜዎች
፩ .ዕለተ ሰኑይ
መርገመ በለስ
፡- ጌታችን የሆሣዕና ዕለት ቢታንያ አድሮ በማግስቱ ከቢታንያ ሲወጣ ተራበ፤ በመንገድም ሲያልፍ ቅጠል ያላት በለስን ከሩቁ ተመለከተ፡፡ ወደ በለሲቱም በቀረበ ጊዜ ከቅጠል በቀር አንዳች ፍሬ አላገኘባትም፡፡ ያንጊዜም ‹‹ከእንግዲህ ወዲህ ለዘለዓለም ከአንቺ ፍሬ የሚበላ አይኑር›› ሲል በለሲቱን ረገማት፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ይህንን ሰሙት፡፡ በዚህም ምክንያት ይህች ዕለት በለሲቱ የተረገመችባት ቀን ናትና መርገመ በለስ ተብላ ትጠራለች፡፡ (ማር.፲፩፥፲፩-፲፬)
በዚህ አገላለጽ በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ስትሆን ፍሬ የተባለ ደግሞ ሃይማኖትና ምግባር ነው፡፡ መድኃኒታችን ክርስቶስ ከእስራኤል ፍቅርን፣ ሃይማኖትን፣ ምግባርን ፈልጎ አላገኘባቸውም፡፡ እስራኤል፦ ሕዝበ እግዚአብሔር፣ የአብርሃም ዘር መባልን እንጂ የአብርሃምን ሥራ በመሥራት በምግባር በሃይማኖት ጸንተው መኖር አይፈልጉምና ደግ ሰው አልተገኘባቸውም፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ በለስ የተባለች ኦሪት ናት፡፡ ኦሪት በዚህ ዓለም ሰፍና ቢያገኛትም አማናዊ ድኅነትን የምታሰጥ ሆና አላገኛትም፡፡ ይሁን እንጂ በእርሷ ድኅነት ባይገኝባትም ‹‹ኦሪትና ነቢያትን ከመፈጸም በቀር ልሽር አልመጣሁም ልፈጽም እንጂ›› በማለት ሕገ ኦሪትን ፈጽሟታል፡፡ ከዚህም ባሻገር በለስ የተባለች ኃጢአት ናት፡፡ የበለስ ቅጠል ሰፊ እንደሆነች ሁሉ ኃጢአት በዚህ ዓለም ሰፍታ ሰፍና አግኝቷታል፡፡ በለስ ሲበሉት ይጣፍጣል፤ ቆይቶ ግን ይመራል፤ ኃጢአትም ሲሠሩት ለጊዜው ደስ ያሰኛል ኋላ ግን ያሳዝናል፡፡ በአንቺ ፍሬ አይገኝ የሚለውም በአንቺ በኃጢአት ፍዳ ተይዞ የሚቀር አይኑር ሲል ነው፡፡ በለሲቱ ስትረገም ፈጥና መድረቋም በአዳም ምክንያት ያገኘን በደል በእርሱ እንደጠፋልን ለመግለጽ ነው፡፡
 ፪. ዕለተ ሠሉስ
ሀ. የጥያቄ ቀን፡- ዕ
ለተ ሠሉስ የጥያቄ ቀን በመባል ይታወቃል፤ ምክንያቱም  በዚች ዕለት ስለ ሥልጣኑ በጸሐፍት ፈሪሳውያን ተጠይቋል፡፡ ጸሐፍት ፈሪሳውያን ያቀረቡለት ጥያቄም ‹‹ከምድራውያን ነገሥታት፣ ከሌዋውያን ካህናት ያይደለ ትምህርት በማስተማር ተአምራት ማድረግ ገበያ መፍታትን በማን ሥልጣን ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ?›› የሚል ነበር፡፡ እርሱም መልሶ ‹‹እኔም አንድ ነገር እጠይቃችኋለሁ፣ እናንተም ብትነግሩኝ በማን ሥልጣን እነዚህን እንደማደርግ እነግራችኋለሁ፣ የዮሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነበረች? ከሰማይ ወይስ ከሰው?›› ብሎ ጠየቃቸው፡፡ እነርሱም ‹‹ከሰማይ ብንል ለምን አልተቀበላችሁትም ይለናል ከሰው ነው ብንልም ሕዝቡ ሁሉ ዮሐንስን እንደ ነቢይ ያከብሩታል እንደ መምህርነቱ ይፈሩታልና ሕዝቡን እንፈራለን›› ተባባሉና ‹‹ከወዴት እንደሆነ አናውቅም›› ብለው መለሱለት፤ እርሱም ‹‹እኔም በማን ሥልጣን እንደዚሁ እንደማደርግ አልነግራችሁም›› አላቸው፡፡ ልቡናቸው በክፋት ሥራና በጥርጥር  ስለተሞላ ነው እንጂይህንንም መጠየቃቸው እርሱ የሚያደርጋቸውን ሁሉ በራሱ ሥልጣን እንደሚያደርግ ሳያውቅ ቀርቶ አልነበረም፡፡ (ማቴ.፳፩፥፳፫-፳፮፣ማር.፲፩፥፳፯-፴፫፣ሉቃ. ፳፥፩-፰)
፫. ዕለተ ረቡዕ
ሀ. ምክረ አይሁድ
፡- ይህቺ ዕለት የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ፈሪሳውያን ጌታ ኢየሱስን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው ምክር የመከሩበት ምክራቸውንም ያጸኑበትና ሰቅለው ይገድሉት ዘንድ የወሰኑበት ቀን በመሆኗ የአይሁድ የምክር ቀን ተብላ ትጠራለች፡፡ ይሁን እንጂ በዚሁ ምክራቸው ወቅት ጌታ ኢየሱስን እንዴት አድርገው እንደሚይዙት በጣም ይጨነቁ ነበር፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ወቅቱ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት ወቅት በመሆኑ በጌታችን ትምህርት የተማረኩ ብዙ ሕዝብ ትምህርቱን ያደንቁ ስለነበር ሁከት እንዳይፈጠር ከመፍራታቸው የተነሣ ነው፡፡ በዚህ ጭንቀትም ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ መካከል አንዱ የሆነው የአስቆሮቱ ይሁዳ በመካከላቸው ተገኝቶ ጌታ ኢየሱስን እርሱ በመሳም አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ለዚህ ተግባሩም ሠላሳ ብር ወረታውን እንዲከፍሉት ከእነርሱ ጋር በመስማማቱና የምክራቸው ተባባሪ በመሆኑ ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸዋል፡፡ (ማር.፳፮፥፩-፭፣፳፮፥፲፬-፲፮፣ማር.፲፬፥፩-፲፩፣ሉቃ.፳፪፥፩)
ለ. የመልካም መዓዛ ቀን፡- ዕለተ ረቡዕ ጌታችን በስምዖን ዘለምጽ ቤት ተቀምጦ ሳለ በመላ ዘመንዋ ራስዋን በዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ ዕፍረት ኃጢአትን ይቅር የሚል መልካም መዓዛ ያለው አምላክ መጣ ስትል ውድ የሆነ ዋጋ ያለው ወይም የሦስት መቶ ዲናር ሽቱን ገዝታ ወደ እርሱ በመምጣትና በራሱ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባችው የመልካም መዓዛ ቀንም ትባላለች፡፡ በዚህም ምክንያት ከኃጢአትዋ የተነሣ መልካም መዓዛ ያልነበራት ማርያም እንተ እፍረት በዚህ በጎ ተግባርዋ መልካም መዓዛ ያለት ሆና ወደቤትዋ ተመልሳለች፡፡ (ማቴ.፳፮፥፮፣ዮሐ.፲፪፥፩-፰)
ሐ. የዕንባ ቀን፡- ይህቺው ማርያም እንተ ዕፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት በዕንባዋ እግሩን እያጠበች በፀጉሯም እግሩን እያበሰች ስለ ኃጢአቷ ሥርየት ተማጽናዋለችና የዕንባ ቀን ትባላለች፡፡ (ማቴ.፳፮፥፮-፲፫፣ ማር.፲፬፥፫-፱፣ዮሐ.፲፪፥፩-፰)
 
፬. ዕለተ ሐሙስ
ሀ. ጸሎተ ሐሙስ፡-
በዕለተ ሐሙስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ የዓለም መድኃኒት የሰው ልጆችንም ልመና የሚቀበል አምላክ ሆኖ ሳለ በዚች ቀን በአትክልቱ ቦታ ገብቶ አይሁድ መጥተው እስከሚይዙት ድረስ ሥጋን የተዋሐደ ፍጹም አምላክ፤ፍጹም ሰው መሆኑን ለማጠየቅ ለአርአያነት ይጸልይ ስለነበረ ይህች ዕለት ጸሎተ ሐሙስ ተብላ ትጠራለች፡፡ (ማቴ.፳፮፥፴፮-፵፮)
616 views15:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 00:06:41 ለክርስትና , ለሰርግ የዲኮር ስራዎችን ማሰራት ይፈልጋሉ ?


ለ ሰርግ                            ለ ክርስትና
ለ ልደት                            ለ ቀለበት
ለ ገዓት                             ለ ሽምግልና
ለ ተማሪዎች ምረቃ           ለ ልጆች ልደት
ለ ቤት ምርቃት                   ለ ሆቴል ምረቃ
ለ ስብሰባ አዳራሾች          ለ ቤተሰብ ኘሮግራሞች
ለ ሰርግ ለመኪና ዲኮር
በ ቤተክርስቲያን ስርዓት ለሚፈፀሙ ሰርጎች እና ኘሮግራሞች

ለተለያዮ ዝግጅቶችም ጭምር የተለያዮ የዲኮሪሽን ስራዎችን እንሰራለን እንዲሁም የተለያዮ የዲኮር እቃዎችን እናቀርባለን !
       

     
              ይህን ይጫኑት  ...  ይህን ይጫኑት

█▓▒░        ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻       ▒▓█
█▓▒░         ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻      ▒▓█
█▓▒░         ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻      ▒▓█
█▓▒░        ►𝗢𝗽𝗲𝗻◄░►𝗢𝗽𝗲𝗻       ▒▓█


Tel .   +251961064953
                 +251703504953
.
819 views21:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ