Get Mystery Box with random crypto!

﷽ዚክረ መንዙማﷺ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zekr_menzuma — ﷽ዚክረ መንዙማﷺ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zekr_menzuma — ﷽ዚክረ መንዙማﷺ
የሰርጥ አድራሻ: @zekr_menzuma
ምድቦች: ሙዚቃ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.48K
የሰርጥ መግለጫ

የኛን #You_Tube ቻናል ለማግኝት ይሄን ይጫኑ⬇️👇
http://youtube.com/@zikrmenzumaneshidatube
ጥያቄ ወይም አስተተያየት ካላቹ በቦት
@ZEKR_MENZUMA_bot ተጠቅመዉ ያድርሱን✍️
የመውሊድ ሀድራ ቪዲዮ በድምፅ የተቀዳ መንዙማ ያላቹ ላኩልን
{ @ZEKR_MENZUMA_bot }

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-04-29 10:28:59 #ያሰላም የተሰኝዉ ምርጥ የሰርግ ነሺዳ #አልበም
አብዱልከሪም ጀማል

1.ያሰላም





1.8K viewsedited  07:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 09:34:10
#ለድቤ_ፈላጊዉች

የተለያየ አይነት መጠን ያላቸውን ድቤዎችን እንሸጣለን መግዛት ለምትፈልጉ በዉስጥ ያናግሩን ወይም ይደዉሉልን
@ABD_ABD2
ስልክ
#0966807265
ክፍለ ሀገር ላላቹም እንልካለን
አድራሻችን
አዲስ አበባ
#አቶቢስ_ተራ
169 views06:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 05:05:01 ሰልማን አል-ዐውዳ ሚስቱን በመኪና አደጋ በማጣቱ ከሐዘን ጋር ጎጆ መቀለሱን የሰማችው የባለቤቱ ጓደኛ ብዕርን ከወረቀት ጋር አዋህዳ ደብዳቤን ላከችለት
Mahi Mahisho

ንግግሯን እንዲህ ትጀምራለች
"ከሚስትህ ጓደኞች መካከል አንዷ ነኝ የውድ ሚስትህ የኡሙ ሙዓዝ ሞት በእጅጉ አሳዝኖኛል። ያለፍክበትን ሀዘንም ሰምቻለሁ.. ምናልባት ያስታግስህ ዘንድ እነሆ ታሪኬን ፅፌልሀለው። ቀልብህን ከፍተህ አንብበው ...

ስለ ሐዘን የተነገረ ስለ ህመም የተተረከ የመጀመሪው ታሪክ አይደለም። እንደ እኔ የሚወዱትን ሰው አጥተው የሚሰቃዩ፣ ወላጅ ወንድሞቻቸውን ተነጥቀው የሚኖሩ በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች አሉ።

በሂጅሪያ አቆጣጠር በ1431 የረመዳን 27ኛው ቀን ላይ ይጀምራል። በአንድ መኪና ተሳፍረን ዑምራ ለማድረግ ወደተከበረው የአላህ ቤት ልንሄድ ከቤተሰቦቼ ጋር ወስነናል። ወንድሞቼ መኪናቸው ቤት አቁመው መጡ። ስምንት ነበርን.. ወላጆቼ፣ እህቶቼና ወንድሞቼ ሙሉ ቤተሰቡ አብሮን አለ። አባቴ እናቴን ጋቢና ከጎኑ አስቀምጦ መኪናውን ያሽከረክራል።

ሁላችንም ቁርኣንን ይዘናል። ጉዞው ረጅም ሰዓትን ስለሚፈጅ መኪና ውስጥ አኽትመን ልንወርድ አስበናል። ሐረም እስክንደርስ በዚክርና በዱዓ ልናሳልፍ ተስማምተናል። እህቴ እየቀራች ታለቅሳለች። ሌላኛዋም የዕንባ ጎርፍን ከዓይኗ ታፈልቃለች። ተራ በተራ እያየኋቸው
ዕንባቸው የሚፈሰው ለምን እንደሆነ ጠየቅኳቸው..?
"ቁርአንን ሳነብ የአላህ ድምፅ ለኔ ቅርብ ሆኖ አገኘዋለሁ" አለችኝ አንዷ።

እኔም ንግግሯን ሰምቼ በጥልቅ ማስተንተን መቅራቴን ቀጠልኩ። አባቴ እየነዳ ዕንቅልፍ አሸለበው። መኪናው ከተራራው አናት ላይ መንከባለል ጀመረ። ጥልቀት ወደሆነ ሸለቆ እየተንከባለለ ይገለባብጠን ያዘ። ከዛፍ ጋር ተላትሜ ቀረሁ የቀሩት ቤተሰቦቼ ሸለቆው ውስጥ ወደቁ።
የመግሪብ ሰላት አዛን እያለ ነበር። አላፈጠርንም ብዙ ደም ከሰውነቴ በመፍሰሱ ራሴን ሳትኩ። አስታውሳለሁ ስነቃ ባባ እያልኩ መጮኽ ጀመርኩ። እየተንፏቀቅኩ መፈለጉን ተያያዝኩት።

የአካል ስብራትና ጉዳት ቢደርስብኝም ድንጋጤው ህመሜን አስረስቶ በሆዴ እያንከባለለ እነሱ ዘንድ አደረሰኝ። እናቴን መጎተት ጀመርኩ። ሞታ አገኘኋት። አባያዋ ሰውነቷ ላይ እንደ ከፈን ተጠቅልሏል። ከሰውነት አካሏ አመልካች ጣቷ ብቻ ነበር የሚታየው። ሁሉም ተሰትሯል። እህቶቼን ሰውነታቸው ተገልጧል። ልሸፍናቸው ሞከርኩ.. ወደማይቀረው አለም ተሸጋግረው አገኘኋቸው። አመልካች ጣታቸው ለሸሃዳ እንደተቀሰረ ነው። ወንድሞቼም ሞተዋል። እንደምንም እየተሳብኩ እነሱንም እየሳብኩ አንድ ቦታ ሰበሰብኳቸው።

የማታዋ ጨረቃ ምሽቱን አድምቃዋለች። የውሻ ድምፅና ጨለማው ከአየሩ ጋር ተዋህዷል። ወደመኪናው ተመልሼ በእንፉቅቅ አባቴ ጋር ደረስኩ። በህይወት አለ። መላ ሰውነቱ እየደማ ነው። ወደ ደረቴ አስጠግቼ አቀፍኩት። "እዚህ ረጅም ሰዓት አትቆዪ.. ወደ ተራራው ጫፍ ወደ መንገዱ ሂጂና ሰው እንዲረዳሽ ተጣሪ ወንድሞችሽን አድኚ" አለኝ በተቆራረጠ ድምፅ።

የውሻዎቹን ድምፅና ጨለማውን መፍራቴን ነገርኩት። ጭኑን ተደግፌ "እየደማሁ ነው መንቀሳቀስ ከብዶኛል" አልኩት። ወደ ደረቱ አስጠጋኝና አደራ ዲንሽ ላይ አደራ እያለ ሸሃዳ ይዞ ወደማይቀረው ዓለም ተሸጋገረ። ብቻዬን ቀረሁ።

እያለቀስኩ ዱዓና ዚክር ላይ ተጠምጄ ራሴን ሳትኩ። አደጋው ከተፈጠረ ሁለተኛውን ቀን ይዟል። መኪናው ሲወድቅ ማንም አላየንም ነበርና ሊረዳን የመጣ ሰው አላገኘንም። በሶስተኛው ቀን አንድ እረኛ ከብቶቹን አሰማርቶ ሲንጎራደድ ከርቀት ተመለከተን። ለጥበቃዎች አሳውቆ በሄሊኮፕተር የታገዘ የነፍስ አድን ቡድን ወደሆስፒታል ይዞን አቀና።

አምስት ወራት ሙሉ ኮማ ውስጥ ቆየሁ። ስነቃ የሆነውን ነገር አስታወስኩ። ቅዠትና ህልም መስሎ ታየኝ። አባቴን እናቴን ወንድሞቼንና እህቶቼን በአንድ ጀንበር አጣሁ። ክስተተሀ ምናል ባልነቃሁ እኔም እነሱን በተከተልኩ አስባለኝ። ሁለት አመታት በሀገረ ካናዳ ጭንቅላቴ፣ አንገቴ፣ ጀርባዬና ዳሌዬ የደረሰባቸውን ከባድ ስብራት እየታከምኩ ህክምና ላይ አሳለፍኩ። በደም መፍሰስ ምክንያት እናት የመሆንን በረከት አጣሁ። ብዙ ሙከራዎች በዶክተሮች ቢደረጉም አልተሳኩም። ሕይወቴን ወይም ልጆች የማግኘት ፀጋዬን ሊያሳጣኝ የሚችለው ቀዶ ጥገና ምርጫው ከባድ ነበር ግን ሆነ።

አሁን ደህና ነኝ አልሀምዱሊላህ። ወደ ስራዬ ተመልሻለሁ ..ወደ ሪያድ ተዛውሬ ከአዲሱ ህይወቴ ጋር መኖር ጀምሬያለሁ .... ያሸይኽ... በሕይወትህ ውድ የሆነውን ሰው ያጣኸው አንተ ብቻ እንዳልሆንክ እንድታውቅ ታሪኬን አካፈልኩህ።

የእህቶቼ ሰርግ ሁለት ሳምንት ነበር የቀረው። ከመሞሸራቸው በፊት ዑምራ ማድረግ ፈልገን ወደ መካ በማቅናት ላይ ሳለን የአላህ ውሳኔ ቀደመ። አሁንም የሰርግ ልብሳቸው እኔ ጋር ነው። እስክሞት ድረስም አብሮኝ ይቆያል" በማለት ታሪኳን ትቋጫለች።

የቀደምት ታላላቅ ዑለማዎቻችንን እና በህይወት ያሉትን ዑለማዎቻችንን መንዙማዉች እና ስራዎች እንዲሁም አዳዲስ መንዙማውች ልክ እንደተለቀቁ የሚቀርብበት ቻናል በተጨማሪም በዚህ ቻናል
ስለ ወርቃማው ታሪካችን እናወራለን።
ዑለሞቻችንን እናወሳለን፤
ጀግኖቻችንን እንዘክራለን፤
ሳይንቲስቶቻችንን እናነሳለን።
ሰብስክራይብ በማረግ ቤተሰብ ይሆኑ ለወዳጆም ሼር ያርጉ
http://youtube.com/@zikrmenzumaneshidatube

Facebook page
https://www.facebook.com/profile.php?id=100066797534886

Join Tg
https://t.me/ZEKR_MENZUMA
678 views02:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 05:04:08
672 views02:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 19:35:40
#አቡ_ሐሰን_ሙሀና ይሰኛሉ ። ህይወታቸውን ለአላህ የሰጡ ሰዎችን ወደ ጌታቸው እየተጣሩ የኖሩ የዳዕዋ ሰው ናቸው ።

ከመኖርያ ቤታቸው በላይ በአላህ ቤት ረጅም ሰዓታትን ያሳልፋሉ ። ሰባት ልጆች አሏቸው ። ወንዶቹም ሴቶቹም ሁሉም የአላህን ቃል ቁርአንን በቃላቸው ሐፍዘዋል።

#ትላንት_በመጨረሻዎቹ የረመዳን አስር ቀናት በጋዛ ሰርጥ ፊታቸው እንዲህ ፈግጎ ከጌታቸው ጋር ተገናኙ። የሚያስደስታቸውን የአላህን ስጦታ እንዳዩ ነገር ጥርሳቸው ተፈልቅቆ እየሳቁ ሩሐቸው ከጀሰዳቸው ተላቀቀ።

[وُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ مُّسْفِرَةٌ ضَاحِكَةٌ مُّسْتَبْشِرَةٌ]

"ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤ ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው" [ሱረቱል ዐበስ 38-39

አላህ ኻቲማችንን ያሳምርልን
1.3K views16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 11:31:18
#ለድቤ_ፈላጊዉች

የተለያየ አይነት መጠን ያላቸውን ድቤዎችን እንሸጣለን መግዛት ለምትፈልጉ በዉስጥ ያናግሩን ወይም ይደዉሉልን
@ABD_ABD2
ስልክ
#0966807265
ክፍለ ሀገር ላላቹም እንልካለን
አድራሻችን
አዲስ አበባ
#አቶቢስ_ተራ
1.1K views08:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 05:23:53
አንቺም ....

አደባባይ ወጥቶ በማፍጠር ምን አገኘሽ ?

እዛ ሂዶ ፎቶ ተነስቶ ከመምጣት በዘለለ ለእስልምናሽ የጨመረው እሴት ምንድነው?

እናት አባት እህት ወንድም የለሽም? .... ካለሽስ በላጩ ጌታሽ ዘንድ ይበልጥ ተወዳጁ እነሱን ሃድመሽ ምታገኚው አጅር/ምንዳ ወይስ በአደባባይ መጮህ መሳለቁ ?

በረመዷን አንዲቷ ደቂቃ ዋጋ አላት ያቺ ደቂቃሽ ሰዓትሽን ያውም በጨለማ ምን ላይ አዋልሻት ?

አምሽተሽ ከ4-5 ሰዓት መግባትሽን እንደ እኩልነት ማየትሽ ይሄ ነው ኢስላም ላንቺ የዋለው ውለታ ? ወይስ አንቺ እስልምናሽን የምታሳዪበት ማንነትሽን የምትገልጪበት መንገድ ይህ ነው?

ቤተሰብሽን እምቢ ብለሽ ጎደና መውጣትሽን ከምን አንፃር ወደድሽው? .... ከምንስ አንፃር በላጭ ሆነልሽ?

ለእናትሽ አንድ ሲኒ ቡና ቀድቶ መስጠቱ ባልበለጠምን??

አንተም ....

በቻልክ በሆነልህና የእህትህን ነውር ደብቀህ ሰትረህ ባስዋብካት ባሳመርካት ነበር

ለሴት ልጅ ያለህን ንቀት የሆነችን ክፍተት ተጠቅመህ በአደባባይ ልታነውራት ባልተገኘችበት ባልዋለችበት ስሟን ምትጠራት አንተ ከየትኛዎቹ ጡሀራዎች ጎራ ሁነክ ነው ??

ለመሆኑ ባለገች ብለህ የምትጠራት ሴት የምትባልገው ብቻዋን ወይስ ካ'ንተ አይነቱ አደምይ ጋር ነው ??

አንተስ የእህትህን ክብር የምትጠብቀው በየትኛው በተከበረ ስፍራ ተገኝተህ ነው? ... ለመሆኑ አንተ አደባባይ የወጣኸው ልታፈጥር ወይስ ይህቺኑ እንስት ሽተህ??

አንተ ለእህትህ ለእናትህ ለሚስትህ ምን አይነት ወንድ ነህ?

እሷ ልታሳየው ያልቻለችው የኢስላም ክብር ባንተ በኩል ታየ ወይስ ምን ??

የት ውለህ ነው መዋያዋን የጠየቅካት ..? የት አይተሃት ነው የት ነሽን ያስከተልክባት ??

ብቻውን የባለገም ብቻዋን ያባለገችም የለችም
769 views02:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 08:52:17 → የትንሹ ዚና አደገኝነት


#የምላስ_ዚና_አደገኛነት ⇩

ሁሉም የሰውነት ክፍሎች እያንዳንዱ አዲስ ቀን በመጣ ቁጥር ምላስን ይገስፃሉ፤ ያስጠነቅቁታልም፤ አላህን እንዲፈራ፡፡ ዕጣ ፋንታቸው የሚወሰነው በምላስ ላይ ተመሥርቶ መሆኑን በመግለጽ ምላስ አላህን እንዲፈራ ይገስጹታል፡፡ ↝ይህንኑ ነብዩ (ﷺ) እንዲህ በማለት ገልጸዋል፡- «በየቀኑ ጠዋት ጠዋት ሁሉም የአካል ክፍሎች አላህን ፍራ ዕጣ ፋንታችን የሚወሰነው ባንተ ሁኔታ ላይ ነውና እንተ ከተስተካከልክ እኛም እንስተካከላለን አንተ ከጠመምክ እኛም እንጠማለን በማለት ምላስን ይገስፃሉ፤ያስጠነቅቃሉም፡፡» (ቲርሚዚ)

  ለመንቀሳቀስ እጅግ ቀላሉ የሰው ልጅ አካል ምላስ ነው፡፡ ልክ እንደዚሁ ልቅ ከሆነ ብዙ ወለምታ የሚያገጥመው የሰውነት አካልም ቢኖር ይኸው ቁራሽ ሥጋ (ምላስ) ነው፡፡ ከዚህም የተነሳ ለባለቤቱ እጅጉን ጎጂው ነገርም ምላስ ይሆናል፡፡ ወደ ዚናም ስንመጣ ብዙውን ጊዜ ዚና በአንዴ ስለማይከሰት በጅማሮውና በፍፃሜው መካከል የምላስ አስተዋጽኦ ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል፡፡ ስለዚህ ከሞላ ጎደል የትልቁን ዚና መንገድ የሚያመቻቸው ምላስ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ የምላስ ወለምታና መዘዝ ዝሙት ላይ ይጥላል፡፡ ለዚህም ነው መልዕክተኛው(ﷺ)ምላሱንና ብልቱን ከሐራም ነገር ለሚቆጣጠር ሰው ጀነት ሊገባ ዘንዳ ዋስትናን የሰጡት፡፡!

↝ ነብዩ(ﷺ)እንዲህ ብለዋል፡- «እርሱ ያ በሁለት መንጋጋዎቹ መካከል ያለውን (ምላሱን) እና በሁለት ጭኖቹ መካከል ያለውን(ብልቱን) ለሚጠብቅ (ለሚቆጣጠር)ሰው እኔ ለርሱ ለጀነት ዋስ እሆነዋለሁ፡፡»(ሙስሊም)

  በተጨማሪም ነብዩ(ﷺ)ለጀነት ዋስትናን ከሰጧቸው ስድስት ዓይነት ሰዎች መካከል አንዱ በሚናገርበት ጊዜ እውነትን የሚናገርና ብልቱን ከሐራም የሚጠብቅ ሰው ነው፡፡ ይህንኑ አስመልክቶ ዑባዳ ቢን ሣቢት(ረድየላሁ
ዐንሁማ) እንዳስተላለፉት ↝ነብዩ(ﷺ)እንዲህ ብለዋል፡- «እናንተ ለስድስት ሥራዎች ዋስትና ስጡኝ፣እኔም በጀነት ዋስትና እሰጣችኋለሁና፡
①ኛ አማና በተሰጣቸሁ ጊዜ(እማናውን ለባለቤቱ) መልሱ፤
②ኛ ቃል ኪዳን በተጋባችሁ ጊዜ ቃል ኪዳናቸሁን ሙሉት፤
③ኛ በምትናገሩበት ጊዜ እውነታውን ተናገሩ፤
④ኛ ብልቶቻችሁን(ከሐራም ነገር)ጠብቁ፣
⑤ኛ ዓይኖቻቸሁን(ዕይታችሁን)ዝቅ አድርጉ፤
⑥ኛ እጆቻቸሁን(ሌሎችን ከመጐዳትና ኃጢአትን ከመፈጸም)ጠብቁ፡፡»

(በይሀቂ)በተጨማሪም ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል፡- «በአላህ እና በመጨረሻው ቀን የሚያምን ሰው መልካም ነገርን ይናገር አልያም ዝም ይበል፡፡»(ቡኻሪና ሙስሊም)

☞ «ብዙ ሰዎች እሳት የሚገቡት በአፋቸውና በብልታቸው ምክንያት ነው፡፡!»(ቲርሚዚ)

(አላህ የላቀና ይበልጥ አዋቂ ነው)

 የቀደምት ታላላቅ ዑለማዎቻችንን እና በህይወት ያሉትን ዑለማዎቻችንን መንዙማዉች እና ስራዎች እንዲሁም አዳዲስ መንዙማውች ልክ እንደተለቀቁ የሚቀርብበት ቻናል በተጨማሪም በዚህ ቻናል
ስለ ወርቃማው ታሪካችን እናወራለን።
ዑለሞቻችንን እናወሳለን፤
ጀግኖቻችንን እንዘክራለን፤
ሳይንቲስቶቻችንን እናነሳለን።
ሰብስክራይብ በማረግ ቤተሰብ ይሆኑ ለወዳጆም ሼር ያርጉ
http://youtube.com/@zikrmenzumaneshidatube

Facebook page
https://www.facebook.com/profile.php?id=100066797534886

Join Tg
https://t.me/ZEKR_MENZUMA
514 viewsedited  05:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 15:27:02
አላሁ አክበር
-----
የኢትዮጵያው ልጅ ሙሐመድ ኑሩ በሳዑዲ በተካሄደው የቁርኣን ውድድር አንደኛ ወጥቶአል።
1.2K views12:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 10:35:51
#እኝህ ሰወ ሸህ ሆጆሌ ይባላሉ የቤኒሻንጉል ጉምዝ ገዠ የነበሩ ሲሆኑ ከአፄ ሚኒሊክ ጋር 5000 ፈረሶችን ይዘዉ አድዎ የዘመቱ ጀግና ናቸዉ አላህ ይርሀማቸዉ አድዎን ስናስብ ሁሌ ይታወሳሉ
816 views07:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ