#አቡ_ሐሰን_ሙሀና ይሰኛሉ ። ህይወታቸውን ለአላህ የሰጡ ሰዎችን ወደ ጌታቸው እየተጣሩ የኖሩ የዳዕዋ ሰው ናቸው ። ከመኖርያ ቤታቸው በላይ በአላህ ቤት ረጅም ሰዓታትን ያሳልፋሉ ። ሰባት ልጆች አሏቸው ። ወንዶቹም ሴቶቹም ሁሉም የአላህን ቃል ቁርአንን በቃላቸው ሐፍዘዋል። #ትላንት_በመጨረሻዎቹ የረመዳን አስር ቀናት በጋዛ ሰርጥ ፊታቸው እንዲህ ፈግጎ ከጌታቸው ጋር ተገናኙ። የሚያስደስታቸውን የአላህን ስጦታ እንዳዩ ነገር ጥርሳቸው ተፈልቅቆ እየሳቁ ሩሐቸው ከጀሰዳቸው ተላቀቀ። [وُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ مُّسْفِرَةٌ ضَاحِكَةٌ مُّسْتَبْشِرَةٌ] "ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤ ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው" [ሱረቱል ዐበስ 38-39 አላህ ኻቲማችንን ያሳምርልን 1.3K views16:35